Tuesday, December 4, 2012

በሳቅ ፍርስ አሉ

 

laughing lion
 

በሳቅ ፍርስ አሉ

አገራቸውን በመክዳት

ወገናቸውን ለመጉዳት

ያልነበረ ሕግ ጥሰው

በነስብሐት ነጋ – በነ መለስ ተከሰው

ሽብርተኛ ሲባሉ

‘በሳቅ ፍርስ አሉ’ አሉ፡፡

ሽ-ሽ-ት በሚል ርዕስ ላቀረብነው የአብዲ ሰኢድ ግጥም ግሩም የሆነ ምላሽ በመስጠት ጨዋታው ሞቅ ደመቅ ላደረጋችሁት dawit፣ ሽማግሌው፣ በለው፣ yeKanadaw kebede እና ዱባለ እጅግ ከፍ ያለ ምስጋናችን ይድረሳችሁ፡፡

በዚህ የግጥም ጨዋታችን የዘወትር ተሳታፊ የሆኑት የካናዳው ከበደ (yeKanadaw kebede) “ለሚቀጥለው የግጥም ጨዋታ አድርጓት” ብለው “በሳቅ ፍርስ አሉ” በሚል ርዕስ “አሸባሪ” በመባል ተከስሰው በእስር የሚማቅቁት ወገኖቻችንን በተመለከተ የላኩልንን ግጥም ነው ላሁኑ ጨዋታችን ያቀረብነው፡፡ እስካሁን ግጥም ስናቀርብ የነበረው ከሌሎች ቦታዎች ነበር አሁን ግን የካናዳው ከበደ የራሳቸውን ግጥም በመላክ ጨዋታው ከኛው ለኛው እንዲሁን ስላደረጉ በጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ ስም ከልብ እናመሰግናለን፡፡ ሌሎቻችሁም እንዲሁ ለጨዋታ የሚሆን እጥር ምጥን ግጥም ከላካችሁልን በደስታ የምናስተናግድ መሆናችንን እንገልጻለን፡፡

 

 

No comments:

Post a Comment