Wednesday, December 26, 2012

“ቤ/ክናችን አደጋ ላይ ነች፤ አድኑኝ ትላለች”

 

london church
 
የዘመናት ታሪክ ባለቤትና ከትውልድ ወደ ትውልድ በመተላለፍ፤ ወደፊትም ለዘለዓለም የምትኖር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እውነተኛ የክርስቶስ ማደሪያ የምትባለው ዛሬ ኖሮ ነገ ለማይኖረው አምባ ገነንና ዘረኛ አገዛዝ መሣሪያ ሳትሆን ከተበደለውና መብትና ነጻነቱን ከተገፈፈው የኢዮጵያ ሕዝብ ጎን መቆም የቻለች እንደሁ ብቻ ነው። (ሙሉው ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ)
 

የደሞዝ Vs. የጠብሽ* ሰሞን

 

(ማሕሌት ፋንታሁን)
 
two faces


 
የዘወትር የድረገጻችን ተሳታፊ የሆኑ ይህንን ጽሁፍ እንድናነበውና እንድናትመው በላኩልን መሠረት እነሆ ለአንባቢዎቻችን አቅርበነዋል፡፡ በዚሁ አጋጣሚ ለጸሐፊዋ ማሕሌት ፋንታሁን ከፍ ያለ ምስጋናችንን እናቀርባለን፡፡

የደሞዝ Vs. የጠብሽ* ሰሞን

አነጋገራችንን፣ አካሄዳችንን፣ አበላላችንን፣ አስተያየታችንን ባጠቃላይ የምናደርገውን ማንኛውም እንቅስቃሴ ላይ ቀጥጠኛ አስተዋፅኦ ካላቸው ነገሮች አንዱና ዋነኛው በኪሳችን ያለው ገንዘብ ዋነኛው ነው፡፡ ገንዘብ ከምናገኝባቸው አንዱ መንገድ ደግሞ ተቀጥሮ መሥራትና ወር ሲያልቅ የሠራንበትን ክፍያ/ደሞዝ ማግኘት ይገኝበታል፡፡ አብዛኛው በከተማ አካባቢ የምንኖር በዚህ መስመር ውስጥ እንገኛለን፡፡
ደሞዝ ተቀብሎ ቀጣዩን የደሞዝ ቀን እንደ ምፅአት ቀን በጉጉት የማይጠብቅ ካለ ይህ ሰው ከደሞዙ ውጪ ሌላ ተጨማሪ ገቢ አለው ወይም አንድ ቀልድ ላይ እንደሰማሁት በአስማት ነው የሚኖረው ማለት ነው፡፡ ደሞዛችን እዛው እንዳለ ወይም በተወሰነ ጭማሪ… ብቻ ኑሮ ግን በብዙ እጥፍ ጨምሮ መኖር መቻላችን እውነትም አስማተኛ ያስብላል፡፡ እንደየደረጃው ይለያይ ይሆናል እንጂ አብዛኛው ደሞዝተኛ ደሞዝ ከተቀበለ በኋላ ካሉት የተወሰኑ ቀናት ውጪ ለመጪው የደሞዝ ቀን ስንት ቀን እንደቀረው በመቁጠር፤ ቀሪውን ጊዜ በብድር እንዴት እንደሚያሳልፍ በማውጠንጠን፤ የሰቀቀን ኑሮ መኖሩን የተለማመድነው ይመስላል፡፡
የደሞዝ ሰሞንና የጠብሽ ሰሞን እንደየሰው ይለያያል፡፡ በአብዛኛው ደሞዝ ከተቀበሉ ከ10-15ኛው ቀን በኋላ ሰሞነ ጠብሽ ይገባል፡፡ ደሞዝ የተቀበሉ እለትም ደሞዟ ብድር ብቻ ከፍላ የዕለቱለት ጠብሽ የሚጀምርበት አጋጣሚም አለ፡፡ የበዓል ወቅቶች እና ጳጉሜ ወር “የጠብሽ” ወቅትን ከሚፋጥኑ/ከሚያረዝሙ ምክንያቶች ውስጥ ዋነኞቹ ናቸው፡፡ የጳጉሜ ወር ግን ለምን ደሞዝ እንደሌላት ሁሌም ይገርመኛል፡፡ በዛ ላይ የአዲስ ዓመት ወጪ ተጨምሮበት አስቡት፡፡

ኢህአዴግና ኢህአዴግ ተፈራርተዋል

“[ሙስና] የስርዓቱ አደጋ ነው” ርምጃ ግን የለም!!

corruption fight

ሙስና በኢትዮጵያ አሳሳቢ ደረጃ መድረሱን ኢህአዴግ አይክድም። ኢህአዴግ ባለስልጣኖቹ በሙስና ስለመዘፈቃቸው ማመኑን የገለጸው “የመንግስት ሌቦች አስቸገሩኝ” በሚል ነው። አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ “በሙስና የተለከፉ ዋጋቸውን ያገኛሉ” ሲሉ ስልጣን በያዙ ማግስት መዛታቸውን የሚያስታውሱ በስተመጨረሻ “ኢህአዴግና ኢህአዴግ ተፈራርተዋል” የሚል ድምዳሜ ላይ ነው።

“ትልቅ ጫካ ሰርታችሁ የኛንም የናንተንም ሌቦች መደበቅ በመቻላችሁ ሁሉንም መመንጠር ስላልቻልን እየተተራመስን ነው” በማለት ጣታቸውን ወደ ነጋዴው ህብረተሰብ በመቀሰር ሟቹ ጠቅላይ ሚኒስትር በአገሪቱ ያለውን ሙስና አስከፊነት በገለጹበት መድረክ “ስልጣን የመክበሪያ ብቸኛው መንገድ በሆነበት አገር ዘላቂ ሰላም ይኖራል ማለት ዘበት ነው። በኪራይ ሰብሳቢነት እንደ መንግስትም፣ እንደ ባለሃብትም መቀጠል አንችልም። እንደ ሶማሌ ነው የምንሆነው። እንተራመሳለን። በድጎማ እየኖርን ሙስናው ከከፋ አገር የሌለው ባይተዋር እንሆናለን” ሲሉ የጉዳዩን አሳሳቢነትና በኢህአዴግ ስሌት ሙስናው የሚያስከትለውን የመጨረሻ ጣጣ አመላክተው ነበር።

“በሁሉም አቅጣጫ እየታረድን ነው” ሲሉ የፖለቲካውና የሙስናውን መዘዝ ያመለከቱት አቶ መለስ፣ ተፈጥሯል ያሉት ጫካ አይጥና እባብ ብቻ ሳይሆን ዝሆንም እንደሚደበቅበት ሲገልጹ በማግስቱ “ዝሆኖቹን” ይለዩና እሳቸው በሁሉም ችግር ውስጥ የማለፍ ብቃት እንዳለው የሚገልጹት ኢህአዴግ ማንነቱን ያሳያል ተብሎ ሲጠበቅ ሁሉም ነገር ተረት መሆኑ የስርዓቱን ተያይዞ በሙስና መበስበስ አመላካች እንደሆነ አስተያየት ሰጪዎች ይስማማሉ።

Saturday, December 22, 2012

ከሶማሊያውያን የሚበልጡ ኢትዮጵያዊያን ተሰደዋል

ኦሮሞ፣ ኦጋዴን፣ አማራና ትግራይ በደረጃ ተቀምጠዋል

immigrants

የአራት ዓመት ማነጻጸሪያ የቀረበበትን የሪፖርቱ አንያንዳንዱ ክፍል ያስገርማል። የማነጻጸሪያው ማሳረጊያ አስደንጋጭ ነው። መረጃው በአሃዝ፣ በኩኔታ፣ በባህሪው ስደትን ይገልጻል። ትንታኔው በካርታ፣ በስደቱ መነሻና መድረሻ መካከል፣ እንዲሁም በስደት መዳረሻ ላይ የሚያጋጥመውን አፈና፣ ቶርቸር፣ አስገድዶ መደፈር፣ ስቃይ፣ የባህር ሲሳይ የሆኑ ወገኖችን ይጠቅሳል።

በተለይ በምስራቅ አፍሪቃ በኤርትራ፣ በኢትዮጵያ በኬንያ፣ በጅቡቲ፣ በሶማሊያና፣ፑንት ላንድ፣ ሶማሊ ላንድ፣ ስደትና የስደትን አስከፊነት በሪፖርቱ ተዘርዝሯል። አገራችን ኢትዮጵያ በስደት የተለዩዋት ዜጎቿ ቁጥር አገር አልባ ከሆነችው ሶማሊያ የሚልቅበትን ሁኔታ ያመላክታል።

የዓለም የስደተኞች ኮሚሽን ከፍተኛ ኮሚሽርን /UNHCR/ በመጥቀስ የኖቬምበር 2012 ሪፖርቱን ያቀረበው Regional Mixed Migration Secretariat /RMMS/ የተባለው ከኢሚግሬሽን ድርጅት ጋር የሚሠራውና በአውሮጳ ኮሚሽን እና በሌሎች ድጋፍ የሚንቀሳቀስ ድርጅት ከ2009 – 2012 ከኢትዮጵያ ወደ የመን የተሰደዱትን ኢትዮጵያዊያን ቁጥር ከሶማሊያ ጋር በማነጻጸር ያቀርባል። በዚህ ማነጻጸሪያ መሰረት 223ሺህ 770 ወገኖች ወደ የመን በነፍስ ግቢ በነፍስ ውጪ የባህር ጉዞ ወደ የመን አቅንተዋል። በተመሳሳይ ከሶማሊያ 100ሺህ 845 ሰዎች የመን በተመሳሳይ ገብተዋል። እንግዲህ እዚህ ላይ ነው አሳሳቢውና አስደንጋጩ ጉዳይ የሚነሳው።

Wednesday, December 19, 2012

ኢትዮጵያ በጅቡቲ ወደብ መገንባት ጀመረች

"... ህወሓት በሽርክና የሚያስገነባው ቢሆንስ?"

railroad

በጅቡቲ አዲስ የሚገነባው ወደብ ወጪ በኢትዮጵያ እንደሚሸፈን ተገለጸ። ወደቡ በቀጥታ ከትግራይ ከሚነሳው አዲሱ የባቡር መስመር ጋር እንደሚገናኝም ታውቋል። እያደር ይፋ በመሆን ላይ ያሉት ፕሮጀክቶች አቶ ሃይለማርያም አስመራ ድረስ ለመሄድ ያሳዩትን ፈቃደኛነት “ለኢሳያስ የቀረበ የፖለቲካ አይስክሬም” በማለት አስተያየት ሰጪዎች ተናገሩ፡፡

ባለፈው ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ የመሰረት ድንጋይ ለማስቀመጥ ጅቡቲ መጓዛቸውን የዘገቡት ያገር ውስጥ መገናኛዎች ያድበሰበሱት ጉዳይ ይፋ የሆነው ዲሰምበር 18/2012 ለአሜሪካ ሬዲዮ መግለጫ የሰጡት በመቀሌ ዩኒቨርስቲ የአፍሪካ ፖለቲካ ተንታኝና የታሪክ ምሁር የሆኑት ረዳት ፕሮፌሰር አየለ በከሬ ናቸው።

ኢትዮጵያ ኢኮኖሚዋ እያደገ በመሄዱ ተጨማሪ ወደቦች እንደሚያስፈልጓት የጠቆሙት እኚሁ ምሁር በጅቡቲ የሚሰራው አዲሱ የታጁራ ወደብ ወጪ በከፍተኛ ደረጃ የሚሸፈነው በኢትዮጵያ መሆኑን ይፋ አድርገዋል። አዲስ የሚሰራው የባቡር መስመር ግንባታ ሲጠናቀቅ መቀሌ ከታጁር ወደብ ጋር እንደምትገናኝም አመልክተዋል።

ስለ ባቡር ግንባታ ሲያስረዱ መቀሌን፣ ወልዲያን፣ አፋርንና አዋሽን በማቋረጥ የሚያልፈው የባቡር መስመር ከሌሎች የኢኮኖሚ ተግዳሮት በተጨማሪ በዋናነት “አፋርና ትግራይ” ውስጥ የተገኘውን 1.3 ቢሊዮን ቶን የፖታሽ ምርት ወደ ወደብ ለማጓጓዝ መሆኑን ባለሙያው ተናግረዋል።

በከፍተኛ ደረጃ የተገኘውን የፖታሽ ክምችት የማምረት ስራ እየሰራ ያለው የካናዳ ኩባንያ ስራውን አጠናቆ ማምረት ሲጀምር በጅቡቲ ወደብ በነጻ ለመጠቀም አስቀድሞ ስምምነት የፈጸመ መሆኑ በአሜሪካ ሬዲዮ ጋዜጠኛ አዳነች ፍስሃዬ ተጠይቆ በመላሹ ተረጋግጧል። በዚሁ መሰረት የታጁራ ወደብ ግንባታ እንደተባለው በከፍተኛ ደረጃ ለሚመረተው የፖታሽ ምርት በዋናነት ይውላል መባሉ ሚዛን የሚደፋ አልሆነም። ጉዳዩ “አቶ መለስ ትግራይን የኢንዱስትሪ ማዕከል ለማድረግ” አቅደው እንደነበር ካሳበቁት የወ/ሮ አዜብ ንግግር ጋር ይያያዛል የሚል ጥርጣሬም ከወዲሁ ተሰምቷል።

Tuesday, December 18, 2012

MEPs demanded “unconditional release of (Eskinder) Nega”

Sent a letter to the Prime MInister

 

EU-Parliament

16 Members of the European Parliament Call for the Release of Imprisoned Ethiopian Journalist Eskinder Nega

Washington, D.C.: Today, 16 members of the European Parliament issued a public letter to Ethiopian Prime Minster Hailemariam Desalegn expressing their grave concern regarding the continued detention of imprisoned journalist and blogger Eskinder Nega.

Arrested in 2011 and detained without access to an attorney for nearly two months, Mr. Nega was sentenced to 18 years in prison under the country’s broad 2009 Anti-Terrorism Proclamation on July 13, 2012. Mr. Nega’s arrest and prosecution came after he wrote online articles and spoke publicly about the possibility of an Arab Spring-like movement taking place in Ethiopia. After his sentencing, the government initiated proceedings to seize his assets, including the home still used by his wife and young son. An appeal hearing in the case is scheduled for Wednesday, December 19th.

መስፍን ኢንጂነሪንግ 30ሚሊዮን ዶላር አተርፋለሁ አለ

 

በአማራ አረም ለማስወገድ የአንድ ለአምስት ጥርነፋ ተደረገ

mesfin industrial engineering

በኤፈርት ስር ከታቀፉት የህወሃት የንግድ ተቋሞች መካከል አንዱ የሆነው መስፍን ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪያል በመጪዎቹ ሁለት ዓመታት ሰላሳ ሚሊዮን ዶላር ለማትረፍ እንደሚሰራ አስታወቀ። ለሶስት ስኳር ፋብሪካዎች የአገዳ መቀቀያ ገንዳ (ቦይሊንግ ሃውስ) ለመስራት የሁለት ነጥብ ስድስት ቢሊዮን ብር ስምምነት አደረገ። የአማራ ክልል በብሄር ብሄረሰቦች ቀን በዓል ድምቀት ላሳየው “ቁርጠኛነት” ተደነቀ፣ ጣና ሃይቅና አካባቢውን የወረረውን አደገኛ አረም ለማጥፋት የአንድ ለአምስት የጥርነፋ አደረጃጀት ማከናወኑ የአካባቢውን አርሶ አደሮች እንዳስደሰተ ተጠቆመ።

ኢቲቪ ትላንት ይፋ እንዳደረገው ከተቋቋመ አስራ ዘጠኝ ዓመት የሞላው መስፍን ኢንጂነሪንግ ከስኳር ፋብሪካዎቹ ጋር የገባውን ውል በአስራ አንድ ወራት ውስጥ ለማስረከብ ሃያ አምስት ቶን ብረት ከውጪ አስገብቷል። ስራውን አስመልክቶ መግለጫ የሰጡት ምክትል ስራ አስኪያጁ አቶ አማኑኤል ገብረኪዳን “መስፍን ኢንጂነሪንግ አገራዊና ግዙፍ ወደ ሆኑ ፕሮጀክቶች ግንባታ ተዛውሯል” ብለዋል።

መስፍን ኢንጂነሪንግ ቀደም ሲል ሲሰራቸው የነበረውን ስራዎች ለአነስተኛና ጥቃቅን ድርጅቶች በማስተላለፍ በከፍተኛ ፕሮጀክቶች ላይ በማተኮር እንደሚሰራ ያስታወቁት አቶ አማኑኤል፣ ድርጅታቸው አዲስ አበባ ቦሌ ቡልቡላ በ35ሺህ ካሬ ሜትር ላይ ከፍተኛና በአይነቱ ልዩ የሆነ ላቦራቶሪ (ካልቸር ሃውስ) በማስገንባት ላይ እንደሆነ አመልክተዋል።አያይዘውም በቀጣይ ሁለት ዓመታት 30 ሚሊዮን ዶላር ለማትረፍ መታቀዱን ተናግረዋል።

የህወሃት ንግድ ተቋሞች ወደ ከፍተኛ ደረጃ በመሸጋገር በወርቅ ማዕድን ፍለጋ፣ በአስመጪነትና በላኪነት፣ በባንክና በኢንቨስትመንት በከፍተኛ እመርታ ላይ እንደሚገኙ ወ/ሮ አዜብ መግለጻቸው አይዘነጋም። በቅርቡ ወ/ሮ አዜብ ይፋ ባደረጉት መረጃ መሰረት በቀጣዩ አምስት ዓመታት ትግራይን የኢንዱስትሪ ማዕከል ለማድረግ የሚያስችል እቅድ አቶ መለስ በነደፉት መሰረት እንቅስቃሴ እንደተጀመረ ታውቋል።

Monday, December 17, 2012

“ከኢትዮጵያ ስለመጣችሁ ታሰራችሁ”

 

የእስራኤል ወገኖች ኦባንግን “ድረሱልን” እያሉ ነው
 
 
ethiopians in israel
 

አገር ቤት ያሉትን ወገኖች ለጊዜው መታደግ ካልተቻለ ቢያንስ ከማንም ተጽዕኖ ወጪ በስደት የሚኖሩትን ኢትዮጵያዊያኖች ለመርዳት ለሚቀርብ ጥያቄ የሚሰጠው ምላሽ የሚያሳዝን እንደሆነ አቶ ሳሙኤል አለባቸው በእስራኤል የኢትዮጵያን እናድን አንድነት ማህበር ሊቀመንበር ገለጹ። አቶ ኦባንግ ሜቶን ማህበሩ በተለይ መጋበዙን አስታወቁ።

ከሚያሳዝን መከራ ተርፈው እስራኤል ከደረሱ በኋላ እስር ቤት እንዲቆዩ የተደረጉት ታዳጊዎች መፈታታቸውን አስመልክቶ መግለጫ ያሰራጩት አቶ ሳሙኤል በተለይ ለጎልጉል እንደተናገሩት “በተለያዩ አገራት መከራ እየተቀበሉ ያሉትን ወገኖች መታደግ የሁሉም ኢትዮጵያዊ ተቋማትና የፖለቲካ ፓርቲዎች ተግባር ሊሆን እንደሚገባ ጠቅሰው፣ በተግባር ግን ይህንን ማየት” እንዳልቻሉ ተናግረዋል።

አቶ ሳሙኤል አለባቸው

በእስራኤል እየደረሰ ያለውን የወገኖች ስቃይ አስመልክቶ ለቀረበ ጥሪ ምላሽ ለመስጠት የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) ግንባር ቀደም እንደነበር ያስታወሱት አቶ ሳሙኤል “በየአገሩ የተበተኑ ወገኖች እንደሚሉት በእስራኤል ያሉ ኢትዮጵያዊያን በአቶ ኦባንግና በድርጅታቸው አኢጋን ላይ ታላቅ እምነት አላቸው” ብለዋል።

“አቶ ኦባንግን ብቻ ሳይሆን አብረዋቸው ለሚሰሩት ሁሉ ልዩ ክብርና ፍቅር እንዳለን የምንገልጸው ዝም ብለን አይደለም” ያሉት አቶ ሳሙኤል “በጠላት ላይ ትኩረት አድርጎ በህብረት ከመስራት ይልቅ እርስ በርስ በመጠላለፍና ባለመተማመን በሚፈጥሩት ውዝግብ ጊዜያቸውን ከሚያባክኑት የተቃዋሚ ፓርቲዎች ይልቅ ኦባንግ የሚመሩት ድርጅት ውጤታማ ስራ ሲሰራ ይስተዋላል። ይህ እውነት በሁሉም ኢትዮጵያዊ ዘንድ በገሃድ የሚታወቅ ነው…” ሲሉ ተናግረዋል። ከህዝብ በቀረበ ጥያቄ አቶ ኦባንግ እስራኤል እንዲገኙ ጥሪ ማቅረባቸውንም አስታውቀዋል። ያስመዘገቡት ስኬት፣ የህይወት ተሞክሯቸውና ትምህርት ሰጪው ልምዳቸው፣ እንዲሁም የሚመሩት ድርጅት የገነባው ስም ለግብዣው ዋና ምክንያት መሆኑን አስታውቀዋል።

Saturday, December 15, 2012

ኢህአዴግ እያስታመመ ነው

የአቡነ መርቆሪዮስ ጉዳይ አልተቋጨም

peace and unity

 የአቡነ መርቆርዮስ ወደ አገር ቤት መመለስ ከስምምነት ላይ ተደረሰ፡፡ ልዩነት የተፈጠረው መንበራቸውን በመረከባቸው አብይ የቤ/ክርስቲያን ቀኖና ላይ ነው፡፡

ይህ የተገለጸው ከህዳር 26 እስከ ህዳር 30፤ 2005ዓም (December 5 – 9, 2012) በዳላስ ከተማ በቴክሳስ ጠቅላይ ግዛት በአገርቤቱ ሲኖዶስና በአሜሪካ ከሚገኘው ስደተኛ ሲኖዶስ ተወካዮች ድርድራቸው ካጠናቀቁ በኋላ ባወጡት የጋራ መግለጫ ነው፡፡

የጋራ መግለጫው ከመውጣቱ በፊት ፕሬዚዳንት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ አቡነ መርቆሪዮስ ከነሙሉ መንበራቸው አገር ቤት እንዲመለሱ የሚጠይቅና ማረጋገጫ የሚሰጥ ደብዳቤ ልከው ነበር፡፡

“የኔው የራሴ ደብዳቤ ነው” በማለት ለቪኦኤ የአማርኛ ክፍል በቃላቸው ጭምር ያረጋገጡት ፕሬዚዳንቱ ከአፍታ በኋላ “ያለሥልጣኔ ገብቼ የፈጸምኩት ነው” በማለት ደብዳቤውን መሰረዛቸውን አስታውቀው ነበር፡፡ ከጀርባው “እንዲህ ያለ ጣጣ አልመሰለኝም” በሚል ድፍን ምላሽ በመስጠት “የቀድሞ አቋሜን ትቸዋለው” ሲሉ ለቪኦኤ መልስ የሰጡት የመጀመሪያ ሃሳባቸውን በመቃወም ከአቡነ ህዝቅኤል ወቀሳ እንደተሰነዘረባቸው አልሸሸጉም፡፡

Friday, December 14, 2012

ሰብኣዊ መብቶች፣ ሕገ-መንግሥቱ እና መንግሥት

ሰብኣዊ መብቶች፣ ሕገ-መንግሥቱ እና መንግሥት

 
Ethiopian-constitution-sm

አዘጋጅ Zone 9

በሶልያና ሽመልስ

ሰሞኑን የመንግሥት መገናኛ ብዙኃን የማዳመጥ ፍቃደኝነት ካሳያችሁ የብሔር ብሔረሰቦች ቀን ከሕገ -መንግሥቱ መጽደቅ ጋር ተያይዞ ለአንድ ሳምንት እየተከበረ ይገኛል፡፡ በትምህርት ቤቶች እና በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ደግሞ በዓሉ ለቀናት (ለአንድ ሳምንት) እንዲከበር ተወስኗል፡፡ ይህ ሕገ መንግሥቱ የጸደቀበትን ቀን ተከትሎ ለ7ተኛ ጊዜ የሚከበረው በዓል ሕገ መንግሥቱ ያጎናጸፋቸው መብቶች ብሎ ብዙዎቹ ብሔር ብሔረሰብ ላይ ያተኮሩ መብቶችን ሲያነሳ ሌሎቹን ደሞ ከተግባራዊነታቸው አለያይቶ ለብቻቸው ያስተዋውቃቸዋል፡፡

የኢፌድሪ ሕገ መንግሥት በሶስተኛው ምእራፍ መሰረታዊ መብቶች እና ነጻነቶች ብሎ በተለምዶ ሰብአዊ እና ሲቪል መብቶች የምንላቸውን ያስቀምጣል፡፡ በክፍል አንድ በ15 አንቀጾች ሰብኣዊ መብቶች የተቀመጡ ሲሆን በዚሁ ምዕራፍ ክፍል ሁለት ዴሞክራሲያዊ መብቶች ስር16 አንቀጾች ተካተዋል፡፡ በሕገ መንግሥቱ ውስጥ የተካተቱት መብቶች ከጥቂቶቹ (አንቀጽ 39 ለዚህ ምሳሌ ነው) በስተቀር በዓለም አቀፍ ደረጃ ሕገ መንግሥቱን ሰብኣዊ መብቶች ጉዳይ ላይ ትኩረት የሰጠ እና የተለየ ያደርጉታል፡፡

ወደ ተግባሩ ሲመጣ ባለፉት 18 ዓመታት ከጽሑፉ ጋር በፍጹም የማይገናኙ ብዙ የተግባር ጥሰቶችን አንደግለሰብም እንደ አገርም አስተናግደናል፡፡ ከነዚህ መካከል አንዳንዶቹ ግልጽ ጥሰቶች አስተዳደራዊ ይምሰሉ እንጂ በባሕሪያቸው በሕገ መንግሥቱ የተቀመጡትን የሰብኣዊ መብት ድንጋጌዎች በግልጽ የሚቃረኑ ከመሆናቸውም ባሻገር በተለያዩ የመንግስት አካላት በመጣሳቸው እንደቁምነገር እንደማይቆጠሩ ያሳያል፡፡

የተናቁ አንቀጾች

በምዕራፍ ሦስት ክፍል አንድ በሰብኣዊ መብት ክፍል ከተደነገጉት ዐሥራ አምስት (15) አንቀጾች መካከል ቢያንስ ዐሥራ ሁለቱ በግልጽ በተደጋጋሚ በመንግስት ተጥሰዋል፡፡ ከነዚህ መካከል አንዳንዶቹ ድንጋጌዎች ሊያከብሩዋቸው በሚገቡ የመንግስት አካላት ዘንድ እንደ ቅንጦት ሲቆጠሩ ሌሎቹ ደግሞ በአፈጻጸም ወለምታ ይታሻሉ፡፡

የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር የተሳካ ድርጅታዊ ኮንፈረንስ አካሄደ፣ “አለም አቀፍ ኮሚቴ” የሚባል እንቅሰቃሴ አለመኖሩን ገለጸ

የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር የተሳካ ድርጅታዊ ኮንፈረንስ አካሄደ፣ “አለም አቀፍ ኮሚቴ” የሚባል እንቅሰቃሴ አለመኖሩን ገለጸ

 
arbegna ginbar conference

ከኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር የተሰጠ መግለጫ

የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር ጎጠኛው የወያኔው ስርዓት በአገራችንና በህዝባችን ላይ ሲያደርስ የነበረውና እያደረሰ ያለው ግፍ ለስልጣን በበቃበት መንገድ መውረድ አለበት ብሎ ጠብመንጃውን ካነሳና መፋለም ከጀመረ አመታትን አስቆጥሯል።

የትጥቅ ትግል መራርና ከፍተኛ ቁጥር ያለው የሰው ህይወት የሚጠይቅ ቢሆንም አያቶቻችን ያለምንም ዋጋ ውድ ህይወታቸውን ለአገርና ለህዝብ ፍቅር በመክፈል ያቆዩልንን የአርበኝነት አደራ ለመወጣት ከምንጊዜውም በበለጠ አጠናክረን የቀጠልንበት ደረጃ ላይ እንገኛለን ።

በመሆኑም ይህን የአገርና የህዝብ ታሪካዊ አደራ ለመወጣት ብሎም ትግሉን በተፋጠነ መልኩ ለመቀጠል ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ መጠቀም ይኖርብናል ሲል ሰሞኑን ያካሄደው ድርጅታዊ ኮንፈረንስ ውሳኔ አስተላልፏል። ከህዳር 28-30/2005 ዓ/ም የተካሄደው ድርጅታዊ ኮንፈረንስ ብዛት ያላቸው ድርጅታዊ አጀንዳዎችን የዳሰሰ ሲሆን፡ በዋናነት ወታደራዊ እንቅስቃሴው ድርጅቱ በ 2005 ዓ/ም አቅዶት የተነሳውና በያዝነው አመትም በአመርቂ ድሎች የጀመረ ቢሆንም ይበልጥ ሊጠናከር የሚችልበትንና ከፍተኛ ውጤት ሊመዘገብ የሚችልበትን ሂደት ተወያይቷል።

የሰንደቅ ሙሉ ዘገባ

 

 
ሰንደቅ ጋዜጣ ረቡዕ ታህሳስ 3 /2005 ዓ.ም
አንድነት ፓርቲ ሹም ሽር ያደርጋል
አቶ ስዬ አብርሃ ማስጠንቀቂያ ሊሰጣቸው ይችላል
 
በዘሪሁን ሙሉጌታ
 

የአንድነት ለፍትህና ለዴሞክራሲ ፓርቲ (አንድነት) ብሔራዊ ምክር ቤት በመጪው እሁድ በሚያካሂደው መደበኛ ስብሰባ በአራት ቁልፍ አጀንዳዎች ላይ ውይይት በማድረግ በፓርቲው አጠቃላይ እንቅስቃሴ ላይ ድክመት ባሳዩ አመራሮች ምትክ ሌሎች እንደሚመርጥ ለም/ቤቱ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ገለፁ።

በተመሳሳይ ለአንድ ዓመት ትምህርት ለመማር ወደ አሜሪካ የሄዱት የፓርቲው የብሔራዊ ም/ቤት አባል የሆኑት አቶ ስዬ አብርሃ ም/ቤቱን ለአንድ ዓመት አስፈቅደው ቢሄዱም በተደጋጋሚ ጊዜያት በም/ቤቱ ስብሰባ ላይ አለመገኘታቸው የም/ቤቱን አባላት አሳስቧል። በፓርቲው ሕገ-ደንብ መሠረት በፓርቲው የብሔራዊ ም/ቤት ስብሰባ ላይ ለሦስት ተከታታይ ስብሰባዎች አለመገኘት ከም/ቤቱ አባልነት የሚያሰርዝ መሆኑ እየታወቀ አቶ ስዬ አብርሃ ያለበቂ ምክንያት በፓርቲው እንቅስቃሴ ውስጥ አለመገኘታቸው በአንዳንድ የም/ቤቱ አባላት ዘንድ ቅሬታ ፈጥሯል።

ፓርቲው ባስቀመጠው የአምስት ዓመት የስትራቴጂ እቅድን ከመተግበር ባለፈ በፓርቲው ሊቀመንበር የተዋቀረው የካቢኔ አባላት ሁሉም በሙሉ ኃይላቸው የፓርቲውን የዕለት ተዕለት ተግባር ማከናወን ባለመቻላቸው ከፍተኛ የስራና የአፈፃፀም ድክመት መታየቱ የም/ቤቱን አባላት በሰፊው ያወያያል ተብሎ ይጠበቃል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ ቀደም ሲል ከፓርቲው በክብር ተሰናብተው የነበሩት ኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራሁ እና የቀድሞው የአዲስ አበባ ወጣቶች ፌዴሬሽን ስራ አስፈፃሚ አባል የነበረው እና “ባለራዕይ የወጣቶች ማኅበር” ሊቀመንበር ወጣት ሐብታሙ አያሌው የፓርቲውን የአባልነት መስፈርቶች ሳያልፍ የፓርቲው ከፍተኛ የስልጣን አካል ወደሆነው የብሔራዊ ም/ቤት አባል ቢሆኑም ወደ አመራርነት ሊመጡ የሚችሉበት ሁኔታ እንደሚፈጠር ከም/ቤቱ አካባቢ የሚወጡ መረጃዎች እየጠቆሙ ነው።

አንድነት ስየን ሊሰርዝ ወይም ሊያስጠነቅቅ ይችላል

 

የተሃድሶው ጅማሬ ይሆን?
 
 
udj
 
በነባር አመራሮች ሲንከባለል የኖረው “የቅንጅት ወራሽ” አንድነት ፓርቲ ኃላፊነቱንና አመራሩን ለተተኪ ሳያስረክብ መቆየቱ በአብዛኛው ትችት ሲያሰጥ መቆየቱ ይታወሳል፡፡ በተለይም አቶ ስየ አብርሃ ፓርቲውን በተቀላቀሉ ማግስት በከፍተኛ ኃላፊነት መሰየማቸው አልተወደደለትም ነበር፡፡ በአንድነት ፓርቲ ውስጥም እስከመከፋፈል የዘለቀ ልዩነት መፍጠሩ የቅርብ ጊዜ ትዝታ ነው፡፡
አሁን የረገበ የሚመስለው የፓርቲው የውስጥ ልዩነት፤ በወቅቱ “ዝም አንልም፤ መርህ ይከበር” የሚሉት ኃይሎች የወሰዷቸውን ጽንፈኛ አቋሞች ብዙዎች የሚደግፉት ባይሆኑም ያነሱትን ጥያቄ አግባብነት ግን ይቀበላሉ፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ ይሁን በሌላ የፓርቲው ተቀዳሚ ምክትል ሊመንበር የነበሩት ዶ/ር ያዕቆብ ኃይለማርያም “እኛ የማማከር አገልግሎት መስጠት አለብን፤ አመራሩን መያዝ ያለበት አዲሱ ትውልድ ነው” በማለት ራሳቸውን በቅሬታ ከፓርቲው ማግለላቸው ይታወሳል፡፡
በአሁኑ ሰዓት አሜሪካ የሚገኙት ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳም ከፓርቲው ጋር ያላቸው ግንኙነት በይፋ በሚታወቅ ደረጃ ላይ አይገኝም፡፡ እርሳቸውን ተከትለው ወደ አሜሪካ የመጡት አቶ ስየም በተየያዩ የአሜሪካ ግዛቶች በፓርቲው ስም ንግግር ሲያደርጉና የራሳቸው እምነት ሲያንጸባርቁ የሚታዩትን ያህል ወ/ት ብርቱካን ከአንድነት ጋር በተቆራኘ ጉዳይ መድረክ ላይ አለመታየታቸው ከፓርቲው ጋር ያላቸውን ግኑኘነት ግልጽ እንዳልሆነ አመላካች ነው፡፡ ወ/ት ብርቱካን ወደ አሜሪካ ከመጡበት ጊዜ ጀምሮ በአጠቃላይ ከትግሉ ጎራ እንዳልራቁ ቢናገሩም ሲመሩ የነበሩትን ፓርቲ በተመለከተ ዝምታን መምረጣቸው የዳያስፖራውን የፖለቲካ ትግል ይመራሉ ብሎ ተስፋ በጣለባቸው ደጋፊያቸው ዘንድ ይፋ ያልወጣ ግን በብዛት ያነጋገረ ጉዳይ ነው፡፡

ሱዛን ራይስ የቤንጋዚው መዘዝ ሰለባ ሆኑ!

 

ራሳቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚ/ር እጩነት አገለሉ
 
 
susan rice
 
በተባበሩት መንግሥታ የአሜሪካ አምባሳደር የሆኑትና በፕሬዚዳንት ኦባማ ለሚቀጥሉት አራት ዓመታት የውጭ ጉዳይ ሚ/ር መስሪያቤትን እንዲመሩ ሊታጩ ይችላሉ የተባሉት ቀዳሚ ተወዳዳሪ ሱዛን ራይስ ራሳቸውን ከእጩነት አግልለዋል፡፡ ጉዳዩ ለፕሬዚዳንቱ የፖለቲካ ክስረት፤ ምርጫውን ሲቃወሙ ለነበሩት የሪፓብሊካን ፓርቲ አመራሮች እና በአሜሪካ ለሚገኙ ኢትዮጵያውን ታላቅ ድል ሆኗል፡፡
በቅርቡ በተጠናቀቀው የአሜሪካ ምርጫ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ለሁለተኛ ጊዜ መመረጣቸውን ካረጋገጡ በኋላ በውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት ሱዛን ራይስ ሂላሪ ክሊንተንን እንደሚተኩ በሰፊው መነገር ተጀመረ፡፡ የፕሬዚዳንቱ ቀዳሚ እጩ መሆናቸው ብዙ ቢነገርላቸውም ከተቃዋሚዎቹ የሪፓብሊካንና ሌሎች ጉዳየኞች የተቃውሞ ድምጽ ለመስማት ግን ብዙም ጊዜ አልወሰደም፡፡
ክሪስቶፈር ስቲቨንስ
መስከረም 1፤ 2005ዓም በሊቢያ ቤንጋዚ ከተማ የአሜሪካ ቆንስላ እና አምባሳደር ላይ የደረሰውን ጥቃት አስመልክቶ ሪፓብሊካኑ የመቃወሚያ ክሳቸውን ማሰማት ጀመሩ፡፡ በወቅቱ በደረሰው ጥቃት በሊቢያ የአሜሪካ አምባሳደር የነበሩት ክሪስቶፈር ስቲቨንስ እና ሌሎች ሦስት አሜሪካውያን የቆንስላው ሠራተኞች ተገድለው ነበር፡፡
ግድያው ከተፈጸመ ጥቂት ቀናት በኋላ በአሜሪካ በሚገኙት አምስት ዋና ዋና የቴሌቪዥን ጣቢያዎች በመቅረብ ድርጊቱ የአሸባሪዎች ጥቃት ሳይሆን በካሊፎርኒያ የተሠራ ጸረ-እስላማዊ ቪዲዮ ምክንያት የተጫረ ነው በማለት አምባሳደር ራይስ ለኦባማ አስተዳደር መከላከያ አቀረቡ፡፡ ምርጫ ሊካሄድ ሁለት ወር ሲቀር የተከሰተው ይህ ድርጊት የምርጫ ፉክክር ውስጥ ለነበረው የኦባማ አስተዳደር ከፍተኛ የፖለቲካ ኪሣራ እንደሚያመጣ የተገመተው አስቀድሞ ቢሆንም የአምባሳደሯ መከራከሪያ ሁኔታውን ሊያለዝብ ችሎ ነበር፡፡

Wednesday, December 12, 2012

ይድረስ ለሟች የቀድሞው ጠ/ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ (ጉዳዩ-ስልጣን እንዲያስረክቡ ስለመጠየቅ)

ይድረስ ለሟች የቀድሞው ጠ/ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ (ጉዳዩ-ስልጣን እንዲያስረክቡ ስለመጠየቅ)

Zenawi-Burial

ሲመረን እና ስናመር!!!

ግልጽ ፖስት ይድረስ ለሟች የቀድሞው ጠ/ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ ጉዳዩ-ስልጣን እንዲያስረክቡ ስለመጠየቅ

አቶ መለስ – እኔ በፍጹም እርሶን ካረፉበት የመቀስቀስም ሆነ የማስቸገር እቅድ የለኝም ነበር፡፡ ነገር ግን አሁን ሳስበው የቅርብ ወዳጀችዎም እረፍት ስላልሰጦት እኔም ይህንን መልእክት ባስተላልፍ ቅር አይሎትም ብዩ ተነሳሁ፡፡ መቼም ባሉበት ሆነው ከፓርቲዎ እስከ ሚዲያው ድረስ ስምዎ ሲነሳ መዋሉ በስቅታ ሳይገሎት አይቀርም፡፡ አኔና እርሶ ያን ያህል አንተዋወቅም (ሆሆይ በየት በኩል………..)፡፡ እንኳን አሁን ሞተው ቀርቶ ኖረውም ቢሆን እኔን አንዲትዋን ህዝብ የሚሰሙበት ምንም አይነት አመል አልነበሮትም፡፡ እነደው ድንገት ከሞት በኋላ ባለው ህይወት ተቀይረው ከሆነ ለእርሶ ባይሆን ለሰዎችዎ ይጠቅም ይሆናልና እባክዎ ጆሮዎን ያውሱኝ፡፡

እንግዲህ እለእርስዎ የሚወራውን ስመለከተው በቅርቡ “አቶ መለስ ገነት ገብተዋል፡፡ ስማቸወም ለመለስኤል ተብሏል” የሚል የኢቲቪ ዜና ይመጣል ብዩ እየተሳቀቅኩ እገኛለሁ፡፡ በመሆኑም እንዲህ አይነቱ የእርሶንም በህይወትም ሆነ በሞት የሚያስችግር ነገር አሁንም ካሉበት ሆነው አንድ ይሉልኛል ብዩ ይህንን መልእክት ለጠፍኩ፡፡ ለመሆኑ በዜናው በሬዲዮኑ ጋዜጣው እና ሌላው ሁሉ ላይ እርሶ ሲያወሩ እንደሚውሉ አውቀዋል፡፡ እርሶ ያልተናሩበት ቲቪ፣ ያላወሩበት ሬዲዮ፣ የሌሉበት ስብሰባ ከጠፋ ሰነበተ፡፡ በህይወት እያሉ ከመሩት (አንደኛውን እሱ ይሻል ነበር) በላይ ከሞቱ የመሩት እየበለጠ ተቸግረናልና እባክዎ ስልጣኖን ያስረክቡልን፡፡ የተፈጥሮ ግዴታ ከወንበሮ ቢያነሳዎትን ሰልጣኖን ለመረከብ የሚችል ስለጠፋ ከሞት በኋላም አለማረፎ በጣም አሳዝኖኛል፡፡ እርሶን ብቻ ነውና የሚሰሙት “እበካችሁ ራሳችሁን ችላችሁ ምሩ፣ ራሳችሁን ሁኑ፣ ምንም ሆነ ምን የራሳችሁን ታሪክ ለመጻፍ እድሉን ተጠቀሙበት” በሉልን፡፡ እንዴት ነው ነገሩ? ለሰርሶም ስም ቢሆን “በህይወት እያለ 21 አመት ከሞተ በኋላ —–አመት የገዛ መሪ” መባል ለስሞ ጥሩ አይደለም፡፡ (እነዲሁም ቢኖር ስልጣኑን አይለቅም ነበር የሚለው ሃሜት ማጠናከር ይሆንቦታል፡፡)

የኦነግ አባል ሆነዋል” በሚል በተከሰሱት በቀለ ገርባ፣ ኦልባና ለሊሳ፣ ወልቤካ ለሚን ላይ ተፈረደባቸው

የኦነግ አባል ሆነዋል” በሚል በተከሰሱት በቀለ ገርባ፣ ኦልባና ለሊሳ፣ ወልቤካ ለሚን ላይ ተፈረደባቸው

 
Free Bekele Garba and Olbana Lellisa

የመንግስት ከፍተኛ ፍርድ ቤት 4ኛ ወንጀል ችሎት “ህጋዊ የፖለቲካ ፓርቲን ሽፋን በማድረግ የአሸባሪቡድን የሆነው ኦነግ አባል ሆነዋል” በሚል በተከሰሱት በአቶ በቀለ ገርባ የክስ መዝገብ ውስጥሚገኙ ግለሰቦች ላይ ፍርድ መስጠቱን የዜና ዘጋቢዎች ከአዲስ አበባ አመለከቱ። በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አስተማሪው አንደኛ ተከሳሽ አቶ በቀለ ገርባን ጨምሮ ኦልባና ለሊሳ ፣ ወልቤካ ለሚ ፣ አደም ቡሳ ፣ ሀዋ ዋቆ ፣ መሀመድ ሙሉ ፣ ደረጀ ከተማ ፣ አዲሱ ሞክሬና ገልገሎ ጉፋ የቀረበባቸው ክስ “የኦሮሚያ ክልልን ከፌዴሬሽኑ ለመገንጠል ፣ የአሸባሪ ቡድን የሆነው ኦነግ አባል በመሆንና ኬኒያ ድረስ በመሄድ ወታደራዊ ስልጠና በመውሰድ” የሚሉ መሆናቸውን ዘጋቢዎች ጠቁመው ፍርድ ቤቱ ውሳኔ ከመስጠቱ አስቀድሞ ተከሳሾቹ ለፍርድ ቤቱ የተለያዩ የፍርድ ማቅለያዎችን ማቅረባቸውን ዘግበዋል። በዚህም መሠረት በመንግስት አቃቤ ሕጎች “የአሸባሪነት ክስ” በቀረበባቸው ላይ አንድም ጊዜ በነጻ ፈትቶ የማያውቀው በሚል የሚተቸው ፍርድ ቤቱ በተከሳሾቹ ላይ የሰጠው ፍርድ የሚከተለው ነው። 1ኛ. አቶ በቀለ ገርባ – በ8 ዓመት እሥር 2ኛ. ኦልባና ለሊሳ – በ13 ዓመት እስር 3ኛ. ወልቤካ ለሚ – በ7 ዓመት እስር 4ኛ. አደም ቡሳ – በ3 ዓመት እስር፣ 5ኛ. ሀዋ ዋቆ – በ8 ዓመት፣ 6ኛ. መሀመድ ሙሉ- በ 10 ዓመት እስር 7ኛ. ደረጀ ከተማ – በ8 ዓመት እስር፣ 8ኛ. አዲሱ ሞክሬ – በ10 ዓመት እስር 9ኛ ገልገሎ ጉፋ – በ12 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ወስኗል። በተጨማሪም ተከሳሾቹ ከሁለት እስከ አራት ዓመት ለሚደርስ ጊዜም ህዝባዊ መብታቸው ፍርድ ቤቱ መሻሩም ታውቋል። በቀለ ገርባ በተለይ ከአቶ ቡልቻ ደመቅሳ በኋላ የኦፌዴን ፓርቲን ጥሩ ተፎካካሪ ያደርገዋል ተብሎ የሚጠበቅ መምህር ነበር ሲሉ የሚያውቁት ይናገራሉ። መኖሪያ ቤታቸው ውስጥ ተደብቆ ተገኘ በተባለው መትረየስ እና ባዶ ሠንሰለት ምክንያት “የተንኮል ድርጊቶችን ግዙፍ በሆነ ዓይነት ማሰናዳት ወንጀል” በሚል ክስ ጭምር የተከሰሱት 9ኛው ተከሳሽ ገልገሎ ጉፋ ከ1984 እስከ 2002 ዓ.ም የኦነግ አመራር አካል የነበሩ ሲሆን በ2002 ዓ.ም ግን ከሌሎች ከኦነግ አባላት ጋር ሆነው እጃቸውን ለመንግሥት ሲሰጡም የኦነግን ዓላማ ኮንነው ሃገር ቤት የገቡ መሆናቸው ይታወሳል።

 

ከአእምሮ ባርነት ነጻ እንውጣ!

 

(መክብብ ማሞ)

emancipation from mental slavery

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በተደጋጋሚ የተሃድሶን አስፈላጊነት በሚያወጡት ርዕሰአንቀጽ ላይ አስነብበውናል፡፡ ባለፈው ጊዜ “ከፖለቲካ ተሃድሶ በፊት [የእውቀት] ተሃድሶ በአስቸኳይ!!” በሚል ርዕስ የተሃድሶን ጥቅምና አስፈላጊነት አስታውቀውናል፡፡ በቅርቡ ደግሞ “የተሃድሶ ያለህ!!!” በማለት በድጋሚ የሰሚ ያለህ ብለውናል፡፡ እኔም ይህንን በሙሉ ልብ የማምንበትን ሃሳብ በማንሳታቸው ላመሰግናቸው እወዳለሁ፡፡ በዚሁ ርዕስ ዙሪያ “ከአእምሮ ባርነት ነጻ እንውጣ” በሚል ሃሳቤን እንደሚከተለው አቅርቤአለሁ፡፡

ከአእምሮ ባርነት ነጻ እንውጣ

የሰውን ልጅ “ሰው” ከሚያሰኙት መካከል ማንነቱን የሚወስኑት የአካላዊ፣ የአእምሯዊና የመንፈሣዊ ኃይላት ውጤት መሆኑ በዋንኛነት ተጠቃሽ ነው፡፡ እነዚህ ዕድገታቸውን በተመጣጠነ መልኩ ካልተጠበቀ የሰው ልጅ “ሰው” ተብሎ ቢጠራና ራሱንም “ሰው ነኝ” እያለ ቢኖርም ከ“ሰው”ነት ተራ የወጣ ለመሆኑ ራሱ ምስክር ነው፡፡

የእነዚህ ኃይላት ተመጣጥነው አለማደግ ሰውን ለብዙ ዓይነት ችግር ይዳርጉታል፡፡ ተምሮ ለድንቁርና፤ ባለጸጋ ሆኖ ለመንፈሣዊ ድህነት፤ ነጻ ሆኖ ለባርነት፤ … ይዳርጉታል፡፡ ከባርነትም የአእምሮ ባሪያ መሆን ትልቁ ጭቆናና ውርደት ነው፡፡

የአእምሮ ባሪያ የሆነ ነጻነቱን የሚጎናጸፍበት በርካታ መንገዶች ቢኖሩም የዕውቀት ተሃድሶ ማድረግ ቀዳሚው ነው፡፡ የዕውቀት ተሃድሶ ለማድረግ ትምህርት ቤት መግባት አያስፈልግም – እዚያ የሚሰጥ ትምህርት አይደለምና፤ የዲፕሎማና የዲግሪ ክምችት አይሻም – በሥርዓተ ትምህርት ውስጥ የተቀረጸ ኮርስ አይደለምና፤ … የዕውቀት ተሃድሶ ለማድረግ ከሁሉ በላይ ቅንነት እና እውነተኛነት ያስፈልጋል፡፡

አልአሙዲ ያጠሩትን መሬት ተነጠቁ

 

huda mexico bldg

 የሼክ መሐመድ ሁሴን አልአሙዲ ኢንቨስትመንት ላይ ጥያቄ ያላቸው ጥቂት አይደሉም። የራሳቸውን ህንጻ ከመጨረስ ይልቅ በኪራይ አንድ ህንጻ የሚያሰራ ገንዘብ ለዓመታት ሲከፍሉ ማየትና መስማት የተለመደ ነው። የንግድ ሰዎች ይህንን ዝንባሌያቸውን ከነጋዴ የሚጠበቅ እንዳልሆነ ይናገራሉ። በዙሪያቸው ተሰባስበው ያሉትም ቢሆኑ አመቺ ቦታ ሲያገኙ በዚሁና በሌሎች ጉዳዮች ያሟቸዋል።

ናኒ ህንጻ

ጊዮን ሆቴል አጠገብ የተሰራው የናኒ ህንጻ ሲጀመር የተወለደ ህጻን አስራ ሁለት ዓመት ሲሞላው ነው ያለቀው። ከጊዮን ሆቴል ፊትለፊት ለአስራ ሁለት ዓመት ለህንጻው መጋዘን ሆኖ ሲያገለግል የነበረው የአዲስ አበባ ስታዲየም የመኪና ማቆሚያ ተገቢው ክፍያ ሳያገኝ ቢኖርም የሳቸውን ፎቶ በስታዲየም ውስጥ ለመለጠፍ ቀዳሚ ነው። አሁን መለስ መጡና አሳነሷቸው እንጂ ስታዲየሙ የእርሳቸው የሚመስልበት አጋጣሚም ነበር።

Tuesday, December 11, 2012

አያልቅበት የወንጀለኞች መንግስት

 
(ሉሉ ከበደ)
ሀገራችን በየጊዜው የስርዓቱ መገለጫና በስልጣን ላይ ያሉት ግለሰቦች ውለኛ ባህሪ ነጸብራቅ የሆኑ ርካሽና አደገኛ እርምጃዎች፤ ሲወሰዱ ማየት እንግዳ ነገር አይደለም። ሀያ አንድ አመት። አሁን የባሰው ነገር የኢትዮጵያን ህዝብ ቁርጠኝነትና ቁጣ ለመፈታተን ወያኔ ህዝባዊ ሰሜትን የሚአነቁር ስራ ባለመታከት እየሰራና ወንጀልም እየፈጸመ መቀጠሉ ነው።
"ራእዩን.. ራእዩን" እያሉ፤ ኢትዮጵያን የማጥፋት ተልኮውን ሳያስጨርሳቸው እግዜር ስላነሳው ሰው እያንቃረሩ፤ የኢትዮጵያን ምድር በሞተ ሰው ፎቶ ማበስበሳቸው እንዳለና እንደቀጠለ ሆኖ፤ የአጼ ሚኒሊክን እና የአቡነቤጥሮስን ሀውልት አናፈረሳለን ያሉት ነገር የጀግናው ኢትዮጵያዊ አሉላ አባነጋን መታሰቢያ ትምህርት ቤት ስም ለውጠው ለአንድ የባንዳ ልጅ ለቀንደኛው የኢትዮጵያ ጠላት ስያሜውን መስጠታቸው፤ የኢትዮጵያን ህዝብ የመናቅ የማዋረድ የብልግና ስራ እና ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን የማጥፋት ተልኮ ቀጣይ እንቅስቃሴ በመሆኑ የሚገርም ነገር አይደለም።
የሚገርመው ነገር ሰማንያ ሚሊዮን ህዝብ ምን አስኪያደርጉት፡ ምን እስኪያሳዩት እንደሚጠብቅ ነው። ተነስቶ የሚያስቆማቸው ህዝብ እስከሌለ ድረስ፤ ጠራርጎ የሚያጠፋቸው ጀግና እስከሚነሳ ድረስ ድሉ የነሱ ነው ይቀጥሉበት።
አንድ የኢሳት ቴሌቭዢን አድማጭ " .. ሰው ሁሉ ወደ ሴትነት ተቀየረ እንዴ?...በኢትዮጵያ ወንድ የለም እንዴ?.." ብሎ በአንክሮ የጠየቀው አንጀቱ አሮ ኖሯል።
የዜጎችን ሰብዓዊ መብትም በተመለከተ በኦሮሚያ ክልል ላፍቶ ውስጥ ችግሩን በህዝብ ላይ እንዲያባብሱ ከሚያሰማሯቸው የወያኔ ቅጥረኞች አንዱ "የጸጥታና የፍትህ ሀላፊ" የሚል ትልቅ ማእረግ የተሰጠው ሰው፤ በዛሬዋ አለም ውስጥ ወደር የማይገኝለት ወንጀል እንዲፈጽም ታዞ ነበር። ሁለት ድሆች አርሶ አደር ባልና ሚስት፤ እርቃናቸውን ባደባባይ አቁሞ (ስርዓቱ ለሂሁ አይነት ተልኮ ያጎናጸፈውን ስልጣን በመጠቀም) እኒያን ንጹሀን ኢትዮጵያውያን ለሰው ልጅ አእምሮ የሚከብድ ጸያፍ ድርጊት እንዲፈፅሙ አድርጓል።በዓለም ላይ ያለፉም ሆነ ያሉ የፋሺሽት የጭካኔ አገዛዞች፤ ባይሆን ይገላሉ እንጂ ወንድን ልጅ ከነሚስቱ ባደባባይ እርቃናቸውን እንዲቆሙ አድርገው፤ የባልየውን ብልት በገመድ አስረው፤ ሚስትን "ጎትቺ… ሳሚ" ብለው፤ አስገደዱ የሚል ታሪክ የተጻፈ የለም።ይህ በኢትዮጵያ የተፈጸመ፤ ወያኔ ያቀነባበረው በአለም ላይ "መንግስት አለ" በተባለበት አገር የተፈጸመ የመጀመሪያ አስደንጋጭ ጸያፍ ድርጊት ነው። ይህ ድርጊት "ህዝቡ ያምጽብናል ወይስ እስከመጨረሻው እንደፈራን ይገዛልናል? " የሚለው የህውሀት ድብቅና ተለምዷዊ ጥያቄ ነው። የድንቁርና ድፍረት ድርጊት ነው።የኢትዬጵያን ህዝብ ወኔ ለመለካት ከሚያደርጉአቸው የማያቋርጡ እኩይ ተግባራት አንዱ ነው። ይቀጥላልም።

ወርቁ ካዶላ የሚያጌጥበት ሌላ!

 

ክፍል ሁለት (አሥራደው ከፈረንሳይ)
 
gold 1
 
ከሁለት ወር በፊት “የለገደንቢ ወርቅ ሽያጭ ድራማ!! ወርቃችን እንዴት አላሙዲ እጅ ገባ?” በሚል ርዕስ ላቀረብነው ጽሁፍ የድረገጻችን የዘወትር ተሳታፊ አሥራደው ከፈረንሣይ “የአላሙዲ ኪስ በወርቅ ሲታጨቅ፤ አዶላ ኑሮ በጭንቅ!” በሚል ርዕስ የመጀመሪያውን ክፍል ጽሁፋቸውን አስነብበውን ነበር፡፡ በዚህ የክፍል ሁለት ጽሁፋቸው ደግሞ ባለፈው ያነሱትን ጉዳይ በመዳሰስ እንደሚከተለው አቅርበውታል፡፡
ወርቁ ካዶላ የሚያጌጥበት ሌላ!
በመጀመሪያው ክፍል መጣጥፌ፤ ቡችላው ማነው? ለምንስ ቡችላ ተባለ? በሚል ጥያቄ ነበር የተለየኋችሁ :: የወርቁ ቡችላ በምስሉ የሚያዩትን ይመስላል፤ ቡችላ የተባለበት ምክንያት ተለቅ ያለ የወርቅ ፍንካች በመሆኑ ነው::
እናም:
አዶላ ወርቅ ነው፤ አዶላ ማርና ወተት ነው፤ አዶላ የዱር አራዊትና አዕዋፍ በአንድላይ ሆነው የሚዘምሩበት፤ ዛፎች እጅ ለእጅ ተያይዘው በንፋስ አጃቢነት ጎንበስ ቀና እያሉ የሚሰግዱበት፤ ሰማይና ምድር መሳሳማቸውን ሳያበቁ በማለዳ፤ ጉሬዛዎች በዛፎች ላይ ሆነው ከወዲያ ወዲህ እየተንጠላጠሉ፤ በወፎች ዝማሬ ታጅበው፤ ከደኑ መሃል በሚፈልቀው ውብ የዕጣን ሽታ እየታጠኑ፤ ለፈጣሪያቸው ምስጋናውን በሽብሸባ የሚያቀርቡበት፤ ምድራዊ ገነት ነው::
አዶላ እንደሚወራው ምድራዊ ገሃነም አይደለም፤ ይልቁንም የገብስ ቆሎውን እያዘገነ፤ የገተሜ ጠጁን በብርሌ እያንቆረቆረ፤ በቆራሰማ የታጠነ ወተቱን እያስጎነጨ፤ እጅ የሚያስቆረጥም ክትፎውን በቆጮ ጠቅሎ እያጎረሰ፤ በአትክልትና ፍራፍሬው ሆድን እያንሸራሸረ፤ ለዛ ያላቸው ገጠመኞቹን በጆሮ እያንቆረቆረ የሚያስተናግድ ደግ ሕዝብና ምድር እንጂ!
አዶላ ፍቅር ነው፤ አንዱ ቢያጣ ከሌላው ተካፍሎ የሚበላበት፤ ሰው ለሰው የሚኖርበት፤ ሰው ሰው የሚሸት የሰው ልጆች ጠረን !
ደሞም አዶላ ተስፋ ነው፤ ዛሬ ቢያጡ ነገ ለማግኘት ተስፋ ሳይቆርጡ፤ የሕይወት ዑደቱ እንዳይቋረጥ፤ ዛሬን በነገ ተክቶ የወደፊቱን ሕይወት ለመኖር፤ የሚያልሙበት የተስፋ ምድር ::

Monday, December 10, 2012

ስለ “አንቀጽ 39” ማንን እናመስግን?

 

(ርዕሰ አንቀጽ)

 

article 39

 በዋዜማ ዝግጅቶች ሲታጀብ ከርሞ፣ ቅዳሜ የተከበረውን “የብሄር ብሄረሰቦች” ቀንን አስመልክቶ የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን የተለያዩ አስተያየት ሰጪዎችን በማሳተፍ “አንቀጽ 39 ለዘላለም ይኑር” ብሎናል። እኛም ለዚህ ውለታ ማንን ማመስገን እንዳለብን ለመጠየቅ ተገደድን። ለመልካሙና “የህዝቦች አብሮ የመኖር አለኝታ” ስለሚባለው አንቀጽ 39!

የሶማሌ ብሄር አባል ናቸው። አቶ አብዱላሂ አብዱራሂም ይባላሉ። ዘጠነኛውን “የብሄር ብሄረሰቦች” ቀን አስመልክቶ አስተያየት እንዲሰጡ ተጋብዘው በቴሌቪዥን ብቅ አሉ “… አቅማችሁ ካደገ በኋላ፣ ልጆቻችሁን አስተምራችሁ አቅም ስታዳብሩ ለአንቀጽ 39 ትደርሱበታላችሁ…” እንዳሉዋቸው አቶ መለስን ጠቅሰው ተናገሩ። ትዝታቸው መሆኑ ነው።

ወዲያው አቶ መለስ በወቅቱ እንገነጠላለን ያሉትን የሶማሌ ህዝቦች ሰብስበው ሲናገሩ ታዩ።እንዲህ አሉ “አስራ ዘጠኝ ዓመት የታገልኩበት አላማ እንዳይቀለበስ እፈልጋለሁ። አይቀለበስም ብዬ ቃል ስገባ እናንተን ለመደለል አይደለም። ምክንያቱም ስለመብቱ ምን አልባትም ከናንተ በላይ አስባለሁ። ምንም የሚያሰጋ ነገር የለም። ከልቤ ስለማምንበት ነው” ሌላ አስተያየት ሰጪ ተከተለ። ተከተለች። “አንቀጽ 39 ለዘላለም ይኑር” ተባለ።

Saturday, December 8, 2012

Selling Ethiopian Children’s and the truth about the so called adoption agency

 

Selling Ethiopian Children’s and the truth about the so called adoption agency

A recent documentary was shown on Danish tv about an adoption case that gone wrong. The director had hoped to show a story of nice Danish people doing a great job helping the poor little Africans but what she ended up filming was something quite disturbing. for most of us Ethiopians heart touching.


 

Thursday, December 6, 2012

ኢህአዴግ ኦነግን እያሰበ አስመራ ላይ አነጣጥሯል!

 

ሃይለማርያም ኢሳያስን አነጋግራለሁ ማለትና የኦህዴድ ዕጣ
hailemariam isayas olf
 
ኢህአዴግ ከወትሮው በበለጠ አስመራ ላይና አስመራን ተገን ያደረጉ ተቃዋሚዎች አስመልክቶ የተንጠለጠሉ ጉዳዮችን አንድም በሰላማዊ መንገድ፣ አለያም በሃይል ለመቋጨት ፍላጎት እንዳለው ከተለያዩ ምንጮች ይሰማል። ይህንኑ መረጃ የሚያጠናክሩ መግለጫዎችና ዜናዎችም በቀጥታና በተዘዋሪ እየተደመጡ ነው። ድርድሩ የሚካሄደው ኦነግን ጨምሮ ከተለያዩ ድርጅት አመራሮች ጋር በተናጠል ስለመሆኑ ለስርዓቱ ቅርብ የሆኑ ሰዎች ጠቁመዋል።
ኢተፋ ጎበና
ኦነግንና ኢህአዴግን ለማስማማት ከላይ ታች የሚሉት የአገር ሽማግሌዎች የሚባለውን ቁጥሩ በውል የማይታወቅ ኮሚቴ የሚመሩት ፕ/ር ኤፍሬም ይስሃቅን ጨምሮ የቀድሞው የኦነግ አመራር አባቢያ አባጆቢር፣ የኢትዮጵያ መካነ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን ፕሬዚዳንት የነበሩት ቄስ ኢተፋ ጎበናና ከሳቸው ጋር የሚሰሩት ኮሚቴዎች፣ በአሜሪካ የወንጌላዊት ሉትራን ቤ/ክ የአፍሪካ ብሔራዊ አገልግሎቶች ዳይሬክተር የሆኑት ዶ/ር ገመቺስ ቡባ ደስታ ከፊት ለፊት ረድፍ የተቀመጡ አሸናጋዮች መሆናቸው ብዙም የተሰወረ አይደለም።
አባቢያ አባጆቢር
ቄስ ኢተፋ ጎበናና ዶ/ር ገመቺስ “እርቅ ከፍትህ ጋር” የሚል የጸና እምነት ያላቸው ሲሆን “ትግል በቃኝ” በማለት አገር ቤት በመግባት ግጭትን በማስወገድ ላይ መሰረት አድርጎ የሚሰራ ተቋም ከዶ/ር ያዕቆብ ሃይለማርያም ጋር የመሰረቱት አባቢያ አባጆቢርና ፕ/ር ኤፍሬም ይስሃቅ የሚመሩት የአገር ሽማግሌዎች ቡድን እርቅ ላይ ስለሚከተለው መሰረታዊ እምነቱ በግልጽ የሚታወቅ ነገር የለም። የቅንጅት አመራሮች እንዲፈቱ በማድረግ ረገድ “ወርቃማ ገድል ፈጽሜያለሁ” የሚሉት ፕሮፌሰር ኤፍሬም በተለያዩ አካላት ተቃውሞ የደረሰባቸውና የ“ኢህአዴግ አፈ ቀላጤ” በሚል የሚያወግዟቸው ጥቂት አይደሉም።

Wednesday, December 5, 2012

ሉዓላዊነትና መብት

 

(ፕ/ር መስፍን ወልደ-ማርያም)
sovereignity and rights
 

ሶርያ አሮጌ አገር ነው፤ ታሪኩ ረጅም ነው፤ ከሶርያ ጋር ሲወዳደር አሜሪካ ሕጻን ነው፤ ነገር ግን ለብዙ ወራት በሶርያ ውስጥ የሚካሄደውን ጦርነትና በቅርቡ በአሜሪካ የተደረገውን ምርጫ ስንመለከትና ስናነጻጽራቸው፣ የሶርያ ሕዝብ እርስበርሱ ሲጨራረስ አሜሪካኖች በጥቂት ቀናት ውስጥ ሐዝቡ ድምጹን ሰጥቶ ምርጫው ተጠናቅቆ በሰላም የሥልጣን ርክክብ ተደረገ፤ ዕድሜ የመብሰል ምልክት ላይሆን እንደሚችልና ፍሬ-አልባ እንደሚሆን መረዳት እንችላለን፤ ከርሞ ጥጃ እየሆኑ ዕድሜ መቁጠር፤ በሶርያ የሚካሄደው ጦርነት ግን አንድ ሰው፣ በሺር አላሳድ፣ እስቲሞት ድረስ መጋደሉና አገር መፈራረሱ ይቀጥላል፤ ዓለምም፣ የተባበሩት መንግሥታትም፣ የአረብ ማኅበርም ሁሉም ከንፈሩን እየመጠጠ የሶርያን ሕዝብ ስቃይ ያያል፤ የፍልስጥኤማውያንንም ስቃይ እንዲሁ፡፡

ለምን አንዲህ ይሆናል? ምክንያቱ ሉዓላዊነት የሚባል ነገር ነው፤ ሉዓላዊነት ምን ማለት ነው? በመሠረቱ ሉዓላዊነት ሦስት ሀሳቦችን ያዘለ ይመስለኛል፤ አንዱ ሥልጣን ነው፤ ሁለተኛው ከበላዩ ሌላ ሥልጣንን የማይቀበል ነው፤ሦስተኛው አጥር ነው፤ በኋላ አንደምናየው ሥልጣንም፣ የበላይነትም አጥር አለው፤ ለወጉ ሉዓላዊነት ማለት ራስን ችሎ ከውጭ ድጋፍ ሳይፈልጉ መቆም ነው፤ ከውጭ ምንም ዓይነት የበላይ ሥልጣንን አለመቀበል ነው፤ በአገሮች መሀከል ተደጋግሞ የሚሰማው በራሳችን የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ አትግቡብን እየተባለ መከላከያ የሚሰጠው ከሉዓላዊነት መሠረት በመነሣት ነው፤ በዚህ ዓይነት መልኩ ብዙ ጊዜ ሥራ ላይ ቢውልም በሉዓላዊነት ሀሳብ አጠቃቀም ላይ የተለያዩ አመለካከቶች አሉ፡፡

Tuesday, December 4, 2012

ሰማያዊ ፓርቲ የአቡነ ጴጥሮስን ሀውልት መፍረስ ተቃወመ

ሰማያዊ ፓርቲ የአቡነ ጴጥሮስን ሀውልት መፍረስ ተቃወመ

ኢሳት ዜና:-ፓርቲው ባወጣው መግለጫ ማንኛውም ልማት ወጪን ቆጣቢ ሆኖ መሰራት እንዳለበት የሚታመን ቢሆንም በዋጋ ሊተመኑ የማኢችሉ ቅርሶችን በማጥፋት ግን ወጪን ለመቀነስ ማሰብ የእብደት አስተሳሰብ ነው ብሎአል።

የፓርቲው ሊቀመንበር አቶ ይልቃል ጌታሁን ከኢሳት ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ ኢህአዴግ ከፍ ብሎ ለመታየት ባለው ፍላጎት የተነሳ ከዚህ በፊት የተሰሩትን ስራዎች ሁሉ ለማሳነስ እንደሚሞክር ገልጠው፣ የአቡነ ጴጥሮስን ሀውልት ለማፍረስ ቀድሞውን ነገር መታሰብ አልነበረበትም ብለዋል

የመንግስት ባለስልጣናት የአቡነ ጴጥሮስን ሀውልት ለማፍረስ ሲወስኑ አጥር እንደማፍረስ አድረገው እንደቆጠሩት የተናገሩት አቶ ይልቃል ፣ ህዝብ ባይጮህ ኖሮ መልስ ለመስጠትም አይፈልጉም ነበር ብለዋል

የግራዚያኒ ሀውልት ጣሊያን ውስት ሲሰራ በዛው ሳምንት የአቡነ ጴጥሮስ ሀውልት መፍረሱ የታሪክ ምጸት ነው በማለት የመንግስትን የታሪክ አረዳድ አቶ ይልቃል ተችተዋል

ይህ በእንዲህ እንዳለ ሉሲ በመጪው የፈረንጆች አመት አጋማሽ ላይ ወደ ኢትዮጵያ እንደምትመለስ መንግስት አስታውቋል።

የህወሀት/ኢህአዴግ ንብረት የሆነው ፋና ብሮድካስቲንግ እንደዘገበው የ5 ዓመታት ቆይታ ለማድረግ ወደ አሜሪካ ያመራው የሉሲ ቅሪተ አካል በመጪው የፈረንጆች ዓመት አጋማሽ ላይ ወደ ኢትዮጵያ ይመለሳል።

በሳቅ ፍርስ አሉ

 

laughing lion
 

በሳቅ ፍርስ አሉ

አገራቸውን በመክዳት

ወገናቸውን ለመጉዳት

ያልነበረ ሕግ ጥሰው

በነስብሐት ነጋ – በነ መለስ ተከሰው

ሽብርተኛ ሲባሉ

‘በሳቅ ፍርስ አሉ’ አሉ፡፡

ሽ-ሽ-ት በሚል ርዕስ ላቀረብነው የአብዲ ሰኢድ ግጥም ግሩም የሆነ ምላሽ በመስጠት ጨዋታው ሞቅ ደመቅ ላደረጋችሁት dawit፣ ሽማግሌው፣ በለው፣ yeKanadaw kebede እና ዱባለ እጅግ ከፍ ያለ ምስጋናችን ይድረሳችሁ፡፡

በዚህ የግጥም ጨዋታችን የዘወትር ተሳታፊ የሆኑት የካናዳው ከበደ (yeKanadaw kebede) “ለሚቀጥለው የግጥም ጨዋታ አድርጓት” ብለው “በሳቅ ፍርስ አሉ” በሚል ርዕስ “አሸባሪ” በመባል ተከስሰው በእስር የሚማቅቁት ወገኖቻችንን በተመለከተ የላኩልንን ግጥም ነው ላሁኑ ጨዋታችን ያቀረብነው፡፡ እስካሁን ግጥም ስናቀርብ የነበረው ከሌሎች ቦታዎች ነበር አሁን ግን የካናዳው ከበደ የራሳቸውን ግጥም በመላክ ጨዋታው ከኛው ለኛው እንዲሁን ስላደረጉ በጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ ስም ከልብ እናመሰግናለን፡፡ ሌሎቻችሁም እንዲሁ ለጨዋታ የሚሆን እጥር ምጥን ግጥም ከላካችሁልን በደስታ የምናስተናግድ መሆናችንን እንገልጻለን፡፡

 

 

Monday, December 3, 2012

ህወሓት ደብረጽዮንን ቀጣይ ጠ/ሚ/ር ያደርጋል!

 

የአሁኑ ምደባ ለመለስ ቀርቦ ነበር
debretsion gebremichael
 
ከአቶ መለስ መለየት በኋላ ወደ አደባባይ የወጡት ዶ/ር ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል ቀጣዩ ጠቅላይ ሚኒስትር ሊሆኑ እንደሚችሉ ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ ግምታቸውን ሰጡ። አገር ቤት ተቀምጠው በኢህአዴግ ላይ የሰላ ትችት በማሰማት ቀዳሚውን ስፍራ የያዙት በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የፍልስፍና መምህርና እንደ ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም የአደባባይ ምሁር በመባል የሚታወቁት ዶ/ር ዳኛቸው ከአዲስ አድማስ ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ይፋ እንዳደረጉት ለግምታቸው ምክንያት ሰጥተዋል።
አቶ መለስ በህይወት እያሉ የስልጣን ክፍፍሉን በሶስት ለመመደብ መታሰቡን ሰምተው እንደነበር ያስታወሱት ዶ/ር ዳኛቸው፣ ሃሳቡ ከስምምነት ላይ ሊደረስ ባለመቻሉ ተግባራዊ ሊሆን እንዳልቻለ አመልክተዋል። አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ማንም ይሁን ማን ከዚህ ቀደም እንደነበረው ስልጣኑ በአንድ ሰው ላይ ተጭኖ ሊቀጥል እንደማይችል ከስምምነት ላይ በመደረሱ አሁን የተደረገው ምደባ ተግባራዊ ሊሆን እንደቻለ በማመልከት ስለቀጣዩ ጠ/ሚኒስትር ግምታቸውን አኑረዋል።
“በእኔ ግምት” አሉ ዶ/ር ዳኛቸው የወደፊቱን ሲተነብዩ “… ህወሃት የጠቅላይ ሚኒስትርነቱን ቦታ ለመያዝ በሁለት መንገድ እየሄደ ነው፡፡” ሕወሓት አሁንም ቢሆን ስትራቴጂካዊ ቦታ ላይ መቀመጡን ያመለከቱት ዶ/ር ዳኛቸው ህወሃት ቁልፍ ቦታዎችን መያዙን ለቀጣዩ ዋና ስልጣን መንደርደሪያ አድርጎ እንደሚጠቀምበት ጠቁመዋል።

Sunday, December 2, 2012

የጁነዲን መጨረሻ አልታወቀም

 

junedin sado1
 
ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም የኢትዮጵያን ታላቅ የሥልጣን መቀመጫ ሲረከቡ “ለተደረገልን ምደባ አመሰግናለሁ” ማለታቸውን ተከትሎ የከፍተኛ ባለሥልጣናት ሹመት “ምደባ” የሚል ስያሜ አግኝቷል። ትላንት ለተወካዮች ምክር ቤት በቀረበ የሽግሽግ ምደባ አቶ ጁነዲን ሳዶ ከምደባ ተዘለው ከሃላፊነታቸው መነሳታቸው ይፋ ሆኗል።
የሲቪል ሰርቪስ ሚኒስትር የነበሩት አቶ ጁነዲን ሳዶ ወንበራቸውን ለአቶ ሙክታር ከድር እንዲያስረክቡ ተደርጓል። ኦህዴዱ አቶ ሙክታር የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርነት ማዕረግ ታክሎላቸው አቶ ጁነዲን ሲመሩት የነበረውን የሲቪል ሰርቪስ ተቋም እንዲመሩ ሲደረግ አቶ ሃይለማርያም ስለአዲሱ ተሿሚ አቶ ሙክታር ቁርጠኛነትና ብቃት ሲያብራሩ ስለ አቶ ጁነዲን ከሃላፊነት መነሳት ግን ያሉት ነገር የለም።
አድሃና ሃይለ
ለዚህም ይመስላል የመድረክ አባል ብቸኛው ተቃዋሚ አቶ ግርማ ሰይፉ “ህዝብ የማወቅ መብት አለው” በማለት ስም ሳይጠሩ አቶ ጁነዲን የተነሱበት ምክንያት እንዲገለጽ “የተከበረውን” ፓርላማ የጠየቁት። ሚኒስትሮች ሲሾሙ መልካም ነገራቸው የሚገለጸውን ያህል ከስልጣን ሲነሱም ምክንያቱና በደላቸው ለህዝብ ሊነገር እንደሚገባው ሲጠይቁ መረጃው በፓርላማ ውስጥ ላሉት ሁሉ ጠቃሚ እንደሚሆን በማመላከት ነበር።

Saturday, December 1, 2012

ህወሃት አረጋግቶ አገገመ

 

ብቸኛው ተቃዋሚ የንግድ ሚኒስትሩን ሹመት ኮነኑ

Assigned EPRDFist

 

ኢህአዴግ “አረጋግቶ አገገመ” ከተባለው አዲሱ “ምደባ” መካከል የንግድ ሚኒስትር ተብለው በተሰየሙት ላይ ብቸኛው የፓርላማ ተወካይ አቶ ግርማ ሰይፉ ጠንካራ መከራከሪያ በማቅረብ ተቃወሙ። አቶ ግርማ የሚሾሙ ብቻ ሳይሆን የሚነሱ ባለስልጣናት ከሃላፊነታቸው የተነሱበት ምክንያትም ለህዝብ መቅረብ እንዳለበት አሳሰቡ። አቶ ሃይለማርያም ተቃውሞውን “መክረንና ገምግመን ያደረግነው ነው” ሲሉ ተከላከሉ። አቶ ግርማ ብሩ (አሁን አምባሳደር) ሲመሩት የነበረውን ሚኒስቴር መ/ቤት “ስያሜና ምልክት መለየት የማይችል” በማለት አንቋሸሹት።

ጠ/ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ አገሪቱን በመሩበት ሶስት ወራት ካቢኒያቸውን በደንብ መገምገማቸውን በግምት በመግለጽ ተቃውሞ ያቀረቡት አቶ ግርማ ሰይፉ በምደባው በተወሰነ ደረጃ እንደሚስማሙ ተናግረዋል። የንግድ ሚኒስትሩ አቶ ከበደ ጫኔን ምደባ የተቃወሙት በማስረጃ ነው። የዓለም ባንክ ለንግድ ምዝገባ የማያመቹ አገሮችን ዝርዝር ጥናት ይፋ ሲያደርግ ኢትዮጵያ ከ185 አገሮች የ165ኛ ደረጃ ማግኘቷን፣ ለዚህም የዳረጉት ቀደም ሲል በተጠባባቂ ሚኒስትርነት ለረዥም ጊዜ ያገለገሉት አቶ ከበደ ጫኔ በመሆናቸው አዲሱ ሹመት እንደማይገባቸው አቶ ግርማ በተቃውሞ ተናግረዋል። በተጨማሪም ህዝብ የማወቅ መብት ስላለው ከፍተኛ ባለሥልጣናት ከሃላፊነታቸው ሲነሱ ምክንያቱ ይፋ ሊሆን እንደሚገባው ማሳሰቢያ አቅርበዋል።

አዲሱ የስልጣን ክፍፍልና አመክንዮው

 

(በዳዊት ተሾመ)

muktar debretsion tedros

እንደ መግቢያ

ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ ለረጅም ጊዜ ሲጠበቅ የነበረውን የካቢኒያቸውን ሽግሽግና አዲስ ተሿሚ ሚኒስትሮቻቸውን ትላንት (ህዳር 20፣ 2005 ዓ.ም) በፓርላማ በመገኘት አሹመዋል:: አዲሱ ካቢኔም ሶስት ም/ጠ/ሚኒስትሮች ሲኖሩት የአራት ሚኒስቴሮችን ሽግሽግም ያካተት ነው:: የቀድሞ ሲቪል ሰርቪስ ሚኒስትር ሚኒሰቴር አቶ ጂነዲ ሳዶ ከሃላፊነት በማንሳት በአቶ ሙክታር ከድር ተተክተዋል:: የጤና ጠብቃ እና የንግድ ሚኒስትር ሚኒሰቴር ዲኤታ የነበሩት ዶ/ር ከሰተብርሃን አድማሱና አቶ ከበደ ጫኔ እንደየቅደምተከትል ለሚመሯቸው ተቋሞች ሚኒስቴር ሆነዋል:: የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ሆነው ሲያገለግሉ የነበሩት ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሀኖም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው ተሹመዋል፡፡

በምክትል ጠቅላይ ሚኒስተር ማዕረግ የተሾሙት የሚከተሉት ናቸው:: ዶ/ር ደብረጽዮን ገብረ ሚካኤል የኢንፎርሜሽንና ኮሙዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እና የፋይናንስና የኢኮኖሚ ዘርፍ አስተባባሪ፣ የሲቪል ሰርቪስ ሚኒስትሩ አቶ ሙክታር የመልካም አስተዳደር ማሻሻያ ዘርፍ አስተባባሪ እንዲሆኑ ሲደረግ በመስከረም ወር ከጠ/ሚ ሃይለማርያም ጋር የተሾሙት የትምህርት ሚኒስትር ሚኒሰቴሩ አቶ ደመቀ መኮንን የማኅበራዊ ዘርፍ አስተባባሪ እንዲሆኑ ተሹመዋል:: በዚህም የተነሳ በምስራቅ አፍሪካ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ኢትዮጵያ ሶስት ም/ጠ/ሚኒስትሮች ይኖሯታል ማለት ነው::

የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሰራዊት ወታደራዊ ጥቃት ፈፀመ

 

Ethiopian People Patriotic Frontበሰሜን ጎንደር መተማ ልዩ ስሙ ዘባጭ ባህር በተሰኘ ስፍራ ህዳር 20-2005 ከወያኔው የመከላከያ ሰራዊት ቅጥረኛ ጋር የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር አገር አድን ሰራዊት ባካሄደው ውጊያ 13 /አስራ ሶስት/ የእብሪተኛው ቡድን ታጣቂዎች በመግደልና 17 /አስራ ሰባት/ በማቁሰል እንዲሁም ተተኳሽ መሳሪያዎችን በመማረክ ከፍተኛ ድል ተቀዳጅቷል።

በእለቱ በተካሄደው ውጊያ የወያኔው ታጣቂ ኃይል ተጨማሪ ሰራዊት በአካባቢው ያዘመተ ሲሆን፡ አርበኛው ሰሞኑን በተከታታይ እየወሰደ የሚገኘው ድንገተኛ ወታደራዊ ማጥቃት እርምጃ የህዝቡን ትኩረት ከመሳቡም ባሻገር በኢትዮጵያውያን ዘንድ የፀረ-ወያኔ ትግል መነሳሳት አብይ ሚና እየተጫወተ መሆኑን በርካቶች እየገለጹ መሆኑም እየተገለጸ ነው።

የፖለቲካ ትግል የመጨረሻ አማራጭ የሆነው የትጥቅ ትግልን መፍትሄ አድርጎ ለአመታት ያህል የጊዜ፣ የእውቀት፣ የጉልበት ብሎም የህይወት መስዋዕትነት እየከፈለ የሚገኘው የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ኢትዮጵያን ከጎጠኛውና መሰሪው ኃይል የመከላከል አኩሪ ጥረቱን ዛሬም እንደ ትላንቱ ሳያሰልስ የሚገፋበት መሆኑን አስታውቋል።

ሰራዊቱ የተለመደውን ጀብድ በፈፀመበት አካባቢ የሚገኙ ነዋሪዎች የግንባሩን ሰራዊት እየተቀላቀሉ መሆኑን የገለጸው የድርጅቱ ወታደራዊ መምሪያ ግንባሩ በተከታታይ የወሰደውንና እየወሰደ የሚገኘውን ወታደራዊ ማጥቃት የመላውን ኢትዮጵያ ህዝብ ድጋፍ የሚጠይቅ እንደመሆኑ መጠን ለሁለንተናዊ የአርበኝነት ትግሉ የተቻለውን በማበርከት ከስርዓት ለውጡ ተጠቃሚ የሚሆንበት አገር ለመገንባት መነሳት ይገባዋል የሚለውን መልዕክት ያስተላለፋል።

 

 

የዛሬ ኅዳር 21 የችሎት ውሎ

* አቃቤ ሕግ ባለፈው ሳምንት በመደናበር የዛሬውን ችሎት ደግሞ በሽወዳ ፈጽሞታል
* ሕግ የማይገዛቸው የኢትዮጵያ ቴሌቪዥንና ዛሚ ኤፍ.ኤም ‹‹ሕግ ይግዛችሁ›› ተብለዋል
* ልደታ አካባቢ ፌዴራል ፖሊሶች ‹‹እስላም ማየት አስጠላን›› ሲሉ ውለዋል


የዛሬ ኅዳር 21 የችሎት ውሎ

ባለፈው ሳምንት ገልጸነው እንደነበረው ዛሬም መሪዎቻችንን ከሕዝብ እይታ ለመሰወር ፖሊስ በደረቅ ሌሊት ነበር ከቃሊቲ ወደ ልደታ ፍርድ ቤት ያመጣቸው፡፡ ሌቱ እስኪነጋና የችሎት ሰዓት እስኪጀምርም በፍርድ ቤቱ ግቢ ውስጥ በፖሊስ ጥበቃ እንዲቆዩ ተደርጓል፡፡ ችሎቱ ከተሰየመ በኋላም የመሪዎቻችን ጠበቆች የኢትዮጵያ ቴሌቪዥንና ዛሚ ኤፍ.ኤም ጣቢያዎች ደንበኞቻችን በተጠረጠሩበት ወንጀል ጥፋተኛ ሳይባሉ ጣቢያዎቹ ግን በተቃራኒው ከፍተኛ የስም ማጥፋት ስራ ላይ ስለተሰማሩ እዚህ ችሎት ውስጥ ካሉ ይውጡልን ብለው ጠይቀዋል፡፡ ዳኛው ችሎቱ ለማንም ክፍት በመሆኑ ይህን ሊያዙ እንደማይችሉና ጣቢያዎቹ የተባለውን ተግባር እየፈጸሙ ከሆነ ግን ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ አዘዋል፡፡

ቀጥሎ በቀጥታ የባለፈውን ሳምንት የጠበቆች የመጀመሪያ መቃወሚያ፤ መቃወሚያ ለማቅረብ ቀጠሮ አስይዞ ወደ ነበረው ችሎት የተገባ ሲሆን አራቱ ጠበቆችም በመተጋገዝ መቃወሚያቸውን ለፍርድ ቤቱ አቅርበዋል፡፡ የመሪዎቻችንና ወንድሞቻችን ጠበቆች አንስተውት ለነበረው አንኳር እና ጠንካራ የተብራራ መቃወሚያ ሲያደምጥ አቃቤ ሕግ ባለፈው ሳምንት ችሎት በመደናገጥ እና በመደናበር ስሜት ውስጥ እንዳልታየ ዛሬ ደግሞ ችሎቱ ላይ ‹‹መቃወሚያው የተብራራ አይደለም›› የሚል ምላሽ ሰጥቷል፡፡ መሪዎቻችን የተከሰሱት ከሕግ ውጪ እንደሆነ፣ በዋነኝነት የተከሰሱበትና በ2001 የጸደቀው የጸረ ሽብር ሕጉ ሕገ መንግስታዊ ድንጋጌዎችን የጣሰ ነው፣ ክሱ የሕግ ትርጓሜ ጉዳዮችን ስለሚያስነሳ መታየት ያለበት ሕጋዊ ስልጣን በተሰጠው ፌዴሬሽን ም/ቤት ነው፣ ይህ ፍ/ቤት ይህንን ክስ የማየት ስልጣን በሕግ አልተሰጠውም እና ደንበኞቻችን በነጻ ይሰናበቱልን የሚሉ መከራከሪያዎችን ከአገሪቱ እና ከአለም አቀፍ ሕግጋት ጋር ተዋድደው የቀረበለት አቃቤ ሕግ፤ ምላሽ ለመስጠት ሳምንት ያህል ተዘጋጅቶም ሊሰጥ የቻለው ምላሽ ‹‹ይሄ ፍርድ ቤት አያየውም ካላችሁ ለምን እዚህ መጣችሁ?›› ብሎ መሪዎቻችንን እና ጠበቆቻቸውን ግራ በገባው ሽወዳ መጠየቅ ነበር፡፡ አቃቤ ሕግ መሪዎቻችንን በግድ ከቤታቸው ወስዶ እንዳሳሰራቸውና ከሶም (ለምን መጣችሁ ባለበት) ፍርድ ቤት እንዳቀረባቸው እንኳ በውል አያውቅም፡፡