Wednesday, July 31, 2013

የሳውዲዋ ልዕልት የመብት ገፈፋ ክስና የኢትዮጵያዊቷ ጉብል አበሳ . . .


ነቢዩ ሲራክ (የማለዳ ወግ. . . )

princess


የሳውዲ ንጉሳውያን ቤተሰብ አባል የሆኑት የ42 አመት እመቤት በምድረ አሜሪካ በቤት ሰራተኛቸው መብት ገፈፋ ተከሰው ለፍርድ ቀርበዋል። ልዕልቷ ኬንያዊዋን የቤት ሰራተኛቸውን በአነስተኛ ክፍያ ከ16 ላላነሱ ሰአታት በመክፈል እና የኬንያዊቷን ሰራተኛ ፖስፖርት ለባለቤቷ ባለመስጠታቸው ተከሰው በምድረ አሜሪካ ለወህኒ ከተዳረጉበት በ5 ሚሊዮን ዶላር ዋስ ቢፈቱም ዛሬም ፍርድ ቤት መቅረባቸውን ሰምተናን። ይህንን ዜና ሳነብ ያን ሰሞን ” ጋዜጠኛ ነህ አሉ እርዳኝ? ” ብላ ከወደ ደማም በተንቀሳቃሽ ስልኬ እየደወለች የምታነባዋ ኢትዮጵያዊት እህት ፍዳ አስታወስኩ !
ዛሬ ረፋዱ ላይ ያነጋገርኳት ይህች እህት የሚደርስባት ግፍ ሳያንስ የተሰደደች የምትገፋበትን የወር ደመወዟን ላለፉት በርካታ ወራት እንዳልተሰጣት ገልጻልኛለች ። ዛሬ በጣሙን ከፍቷት እያለቀሰች ከገባችበት ስቃይ እታደጋት ዘንድ ተማጽናኛለች! አቅሙ ኖሮኝ ምንም ልረዳት ባልችልም አበሳዋን ግን እነግራችኋለሁ! ይህች ግፉዕ ደራሽ ያጣችው እህት በኮንትራት ከኢትዮጽያ ከመጣች አመት የደፈነችው በያዝነው ወር መሆኑን ገልጻልኛለች። ከመጣች ቀን አንስቶ ለ16 ላላነሱ ሰአታት እንድትሰራ ስትገደድ ግልምጫ እርግጫና ስድቡን ችላ እንዳሳለፈች እያሳልፈችው ቢሆንም የማትቋቋመው ፈተና ገጥሟታል! የጋብቻ ቃል ኪዳን አስራ ሰርታ ራሷን ለመለወጥ የመጣችው እህት በአሰሪዎቿ ቤተሰቦች ጥቃት ተማራለች! ሚስት በቅናት ተነሳስታ ቁም ስቅሏን የምታሳያት ሳይበቃ የአሰሪዎቿ ሁለት ጎረምሳ ልጆች በየተራ ” እንድፈርሽ !” ብለው የሚያደርሱባትን ትንኮሳ መቋቋም አለመቻሏን እንባ እያዘራች ምርር ብላ እያለቀሰች አጫውታኛለች !
ይህች እህት ወደ ፍትህ አካል የሚያቀርባት ፣ ከገባችበት የመከራ ህይዎት የሚገላግላት የመብት አስከባሪ አካላት አጥታለች ። ኤጀንሲዋን አነጋግራ ” በርረሽ ወጥተሽ እጅሺን ለፖሊስ ስጭ!” ከማለት ያለፈ መፍትሔ አልሰጧትም። አጣብቂኝ የገባችው እህት መፍትሔ ታገኝ ዘንድ የሪያድ ኢንባሲ ሃላፊዎችን ተንቀሳቃሽ ስልክ ሳይቀር ሰጥች ለማረጋጋት የሞከርኩት ቢሳካም ወደ ሃላፊዎች ስልክ ደውላ ከችግሯ ይታደጓት ዘንድ ብትማጸናቸውም ተስፋ ከመስጠት አልፈው የሰሩት ስራ አለመኖሩን እንባ እያዘራች ስታጫውተኝ አሁን አሁን የኢንባሲው ሃላፊዎች ስልክ ስትደውል እንኳ ሊመልሱላት እንዳልቻሉ አጫውታኛለች ። እኔ እስከ ዛሬ ረፋዱ ድረስ ሃላፊዎችን ደውየ ለማነጋገር ያደረግኩት ሙከራ ስልካቸውን ስለማያነሱ ጥረቴ አልተሳካም !
ይህን ግፍ የሳውዲ ህግና መንግስትም አይደግፈውም! ይህ መሰሉን ግፍ በሰራተኛ ላይ መፈጸም ከባድ ቀጣት ቢኖረውም ህግ ፊት የሚያቀርባት ቀርቶ ከገባችበት መቀመቅ የሚያወጣት የሃገሯ ተወካዮችን አጥታ ኑሮን በመከራ እየገፋች መሆኑን ባደረግነው ውይይት ተረድቻለሁ! የሚያሳዝነው ይህች እህት ከዚህ ሁሉ ጭንቀት በኋላ ምን ልትሆን እንደምትችል አላውቅም! ግፉ ከቀጠለ በሚፈጠር ግጭት ምን ሊፈጠርባት እንደሚችል መገመት ይከብዳል! ጎረምሶቹ በጉልበት እንድረፈርሽ ሲሏትም ሆን ሚስት በቅናት ተነሳስታ በምታደርገው የመልስ ጥቃት እንድትጠነቀቅ አበክሬ ከመምከር ባለፈ ምንም ማለት አልቻልኩም! የሳውዲዋ ንግስት ፈጸመችው በተባለው እኛ የአረብ ሃገር ነዋሪዎች መብት ረገጣውን ለምደነው “እዚህ ግባ የማይባል !” የምንለው ጥፋት በነጻዋ አሜሪካ መድር መብት ነክተዋልና ቁም ስቅላቸውን እያዩ ነው ፣ የእኛዋ እህት ደግሞ የግፍ ግፍ እየተፈጠረባት የሃገሯ መንግስ ተወካዮች እንኳ ድረሱልኝ ተብለው ተጠርተው ሊደርሱላት ባለመቻላቸው በሳውዲ ምድር አበሳዋን እያየች ትገኛለች ! የነገን ግን እንጃ. . .
ለሁሉም እኔ ያየሁ የሰማሁትን ተናግሬያለሁ ! ጀሮ ያለው ይስማ . . .!
ቸር ያሰማን !

መረጃ በጨዋታ፤ በዱባይ ኤንባሲያችን ሆኗል አሉ “ገዳይ”


burj_khalifa_aka_burj_dubai-wide
መረጃ በጨዋታ፤ በዱባይ ኤንባሲያችን ሆኗል አሉ “ገዳይ”

ዱባይ ሆይ የእህቶቻችን ሀገር እንደምን ነሽ… ለመሆኑስ እህቶቻችንን እንዴት ናቸው…በሻርጃ እና አቡዳቢ ጉያዎችሽ የደበቅሻቸው ጎረምሶችሽ በዚህ ሰዓት ምን እያሏቸው ይሆን… “ማዳሞችሽስ” ስንቷን የሀገሬ ሴት እየገላመጡ ስነቷንስ እያመናጨቁ ይሆን…
በፌስ ቡክ የመልዕክት ሳጥኔ አንድ መልዕክት መጣ፡፡ እንዲህ ይላል “በዱባይ ኤንባሲያችን እየሆነ ስላለው ነገር ልነግርህ ነበር” እኔስ ማነኝ፤ እስቲ አምጪው አልኳታ፤
በዩናይትድ አረብ ኢምሬት ዱባይ ኢትዮጵያ ኤንባሲ አሰራሩ ከይሲ ቢባል ይቀላል፡፡ እህቶቻችን ፓስፖርት ለማሳደስ ወይም ለአንድ ጉዳይ ወደ ኤንባሲ ደጃፍ ልክ ሲደርሱ የድሮ ቀበሌ አቀባበል ይደረግላቸዋል፡፡ ቀበሌ ትዝ ይልዎታል ወዳጄ… ዘበኛውም ሊቀመንበሩም እኩል ሰው የማመናጨቅ ስልጣን የተሰጣቸው ቦታ እኮ ቀበሌ ነው፡፡ (በነገራችን ላይ አሁን ግን ቀበሌ ተሸሽሏል፡፡ እኔ ሽሮሜዳን ትቼ “ልነካው” የነበረ ሰሞን ቀበሌ የሄደ ሰው የሚደረግለት እንክብካቤ… እንደው ያ ደህንነት ወዳጄ “ወግሞ” ባይዘኝ ኖሮ ለቀበሌያችን ፀባይ መሻሻል ስልስ እዛው ብኖር እመርጥ ነበር፡፡)
እናልዎ ዱባይ ያለው ኤንባሲያችን መጀመሪያ ሲገቡ የሚቀበልዎ፤ ከድሮ ቀበሌ በበለጠ ደረጃውን ያልጠበቀ ማመናጨቅ አቅርቦ ነው፡፡ ከዛ ለምንም ጉዳይ ይሂዱ የመጀመሪያው ጥያቄ ቦንድ ግዢ የሚል ነው፡፡ በጣም ስናጋንነው ኤንባሲ የሚሰራ ሰው ሰላም ለማለት የሄደች እንኳ ቦንድ ግዢ መባል አይቀርላትም፡፡
ከዛ በተጨማሪ ደግሞ “የኮሚኒቲ አባልነት” የሚባል ነገር አለ፡፡ አባል ያልሆነ ሰው በኤንባሲው በኩል ምንም ግልጋሎት አያገኝም፡፡ እንደውም አሟሙቆ ማውራት ምን ጠቅማል ብለን እንጂ… የኤንባሲው ሰራተኞች “አባል ያልሆነ ሰው ባል እንኳ እንዳታደርጉ” ተብለዋል አሉ፡፡
ቀልዱ ቀልድ ነው… ይቺ ወዳጄ በቃለ ምህላ እንደነገረችኝ፤ (መቼም ምላ አትዋሸኝም) አንዲት ኢትዮጵያዊት በኤንባሲዋ በኩል የሆነ ግልጋሎት ከፈለገች የኮሚኒቲ አባል ለመሆን ከሚከፈላት አምስት መቶ ድርሃም ውስጥ መቶ ሰማኒያውን “ሆጭ” አድርጋ መክፈል አለባት፡፡
ታድያ የሀገራችን ኤምባሲ በዱባይ ሆኗል አሉ ገዳይ ብንል ምን ውሸት አለብን ይባላል…
እንደውም ይሄንን ያጫወትኩት አንድ ወዳጄ ይሄማ ኤምባሲ ሳይሆን “ካዚኖ” ነው ብሎኛል፡፡ (መጣች እንግዲህ የዲያስፖራ ቃል… “ካዚኖ” ቁማር ቤት ነው፡፡ ቁማር ቤትስ ምንድነው… የሚል ካለ፤ ትንሽ ሰው የሚጠቀምበት ብዙ ሰው የሚከስርበት ተቋም ማለት ነው፡፡)
ስለዚህ እንላለን በዱባይ ካዚኖአችን ፈርሶ ኤንባሲያችን ይሰራ!

Tuesday, July 30, 2013

“ጴጥሮስ ያቺን” ቃል!


abunepetros1


ፋሺስቶች ያገራችንን አርበኞች ሽፍታ ቢሏቸው እውነት እንዳይመስላችሁ፡፡ ሸፍታ ማለት ያለ አገሩ መጥቶ የሰውን አገር የሚወር ይህ በመካከላችሁ መጥቶ የቆመ አረመኔው የኢጣሊያ ፋሺስት ነው፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ለእርሱ እንዳይገዛ ውጉዝ ነው፡፡ የኢትዮጵያ መሬት እንዳትቀበለው የተገዘተች ትሁን፡፡” አቡነ ጴጥሮስ፡፡
ዛሬ ሐምሌ 22 ቀን ጀግናው ሰማዕት አቡነ ጴጥሮስ በግፍ የተገደሉበት ቀን ነው፡፡ እኒህ ታላቅ አባት ለሰማዕትነት ያበቃቸው ዋናው ምክንያት በወቅቱ ለተጠየቁት ቀላል ለሚመስል ጥያቄ “ቃሌን አልክድም” ብለው በመቆማቸው ነበር፡፡
ፋሺስት ኢጣሊያ አገራችንን ወርሮ ሕዝቡን ባስጨነቀ ጊዜ አቡነ ጴጥሮስ ከአርበኛው ጋር በመቆም የጣሊያንን ሠራዊት በድፍረት ሲቃወሙና አርበኛውንም ሲደግፉ ቆይተዋል፡፡ ሆኖም ከጊዜያት በኋላ በፋሺስቶች ቁጥጥር ሥር ከዋሉ በኋላ ጣሊያኖች ራሳቸው በሰየሟቸው ዳኞች ፊት አቡኑን ለፍርድ በማቅረብ ከላይ ሲታይ በጣም ቀላል የሚመስል ጥያቄ ያቀርቡላቸዋል፡፡ የጥያቄው ዓላማ አቡኑን የጣሊያን ተገዢ ለማድረግ ብቻ ሳይሆን በወቅቱ የነበረውን ሕዝባዊ ዓመጽ ለማብረድ ቢቻልም ደግሞ የብዙሃኑን ድጋፍ ለማግኘት የታሰበበት ነበር፡፡
ስለዚህም የግራዚያኒ ዳኞች አቡነ ጴጥሮስን ለፍርድ ባቀረቧቸው ጊዜ የጠየቋቸው “ሊቀጳጳሱ አቡነ ቄርሎስ እንዲሁም ሌሎች የጣሊያንን የበላይነት ተቀብለዋል፤ እርስዎም እንዲሁ ተቀብለው ሌሎችም እንዲቀበሉ ቢያደርጉ ይሻላል፤ ብቻዎን ማመጽ ምንም አይሰራልዎትም፤ ይህንን ቢያደርጉ ምን ይመስልዎታል …” የሚል እንድምታ ነበረው፡፡ … አቡኑም “ከመሞት መሰንበት” በማለት የቀረበላቸውን ምክር አዘል አስተያየት መቀበል አላቃታቸውም፡፡ ሆኖም ለእምነታቸውና ለሕዝባቸው የገቡትን ቃል ከሚክዱ ሞትን እንደሚመርጡ በድፍረት ለዳኞቹ መለሱላቸው፤ እንዲህም አሉ፤
“አቡነ ቄርሎስ ግብጻዊ ናቸው፤ ስለኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊያን የሚገዳቸው ነገር የለም፡፡ እኔ ግን ኢትዮጵያዊ ነኝ … ስለ አገሬና ስለ ቤተክርስቲያኔ እቆረቆራለሁ … እኔን ለመግደል እንደወሰናችሁ አውቃለሁ፡፡ በእኔ ላይ የፈለጋችሁትን አድርጉ” የሚል ነበር፡፡ (ጳውሎስ ኞኞ “የኢትዮጵያና የኢጣሊያ ጦርነት” አ.አ. 1980፤ ገጽ 157)

Saturday, July 27, 2013

Dr. Wondimu says Semhal Meles deposits $5 billion

July 26, 2013

የመለስ ዜናዊ የመጀመሪያ ልጅ ሰመሃል መለስ ኒው ዮርክ ውስጥ በሚገኝ አንድ ባንክ ውስጥ 5 ቢሊዮን ዶላር በ2011 ኣስገብታለች። ይህን ያሉት እንግሊዝ አገር እሚገኙት ምሁር እና የመንግስት ተቃዋሚ የሆኑት ዶክተር ወንድሙ መኮንን ናቸው። ዶክተር ወንድሙ የቼኩን ኮፒ አያይዘው ለእንግሊዝ ፓርላማ ሃውስ ኦፍ ኮመንስ አቅርበዋል። ሙሉውን እዚህ ያገኛሉ
Semehal Meles Zenawi, the daughter of the late Ethiopian Prime Minister Meles Zenawi
Semehal Meles Zenawi, the daughter of the late Ethiopian Prime Minister Meles Zenawi, “has deposited $5 billion in one of the banks in New York”, said Dr. Wondimu Mekonnen, an academic and opposition figure, during a recent presentation at the House of Commons in the U.K.
Celebrity Net Worth site said Meles Zenawi got a net worth of $3 billion.
Semehal Meles Zenawi, the daughter of the late Ethiopian Prime Minister Meles Zenawi
Wondimu also showed and distributed to the members of the House who attended his presentation, what he called a “copy of the cheque of the money” she lodged.
Celebrity Net Worth site said Meles Zenawi got a net worth of $3 billion. What a shame! That is wrong guys. Absolutely wrong. I have got a copy of a cheque signed by Semhal Meles Zenawi, the daughter of Meles Zenawi himself, depositing in one of the New York banks $5 billion. I have got and I will give you the copy. Don’t ask me how it came into our possession but that is a fact.

Friday, July 26, 2013

ETHIOPIA: LEGALLY CORRUPT

July 24, 2013

by Wondimu Mekonnen

Introduction

The simplest definition of state corruption is the self-enrichment of government officials through the use of the power bestowed on them and state mechanism. In Ethiopia, the TPLF is a mafia type gang that is running its own Mafiosi economic empire, not the country as a legitimate caring government.
The country itself is up for sale, as long as there are buyers out there. That is why people in Gambella were to evicted and their land sold to Indian and Arab, Turkish, Pakistani Billionaires. Recently, the Ethiopian Government refused to cooperate with the World Bank when it was asked to investigate whether the World Bank violated its own policies by funding, in which thousands of people were allegedly relocated to make way for agricultural investors. The British Government actually knowingly or unknowingly funded a programme that evicted the tribes of the Lower Omo Valley in south west Ethiopia – chief among them the Mursi, the Nyangatom, the Bodi and the Daasanach, who depend on a combination of flood retreat cultivation on the banks of the Omo River, rain fed cultivation further back from the river, and cattle on the grass plains, again to make way for foreign agricultural investors. The land of the Amaras, Afars, Oromos and all over the country is up for a grab. Even Egypt secured herself 20, 000 acres of farmland. To imagine this, one acre is about 1 football stadium field. The money from the sale of land, in hard currency goes straight either to the pockets of individuals of those in powers or to the coffers of regime’s private money making institutions, such as the “The Endowment Fund for the Rehabilitation of Tigray”, EFFORT.

ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ባለቤት ሰርካለም ፋሲል ከአገር ወጣች


EMF – ጋዜጠኛ ሰርካለም ፋሲል በትላንትናው እለት ከኢትዮጵያ መውጣቷ ታወቀ። ጋዜጠኛ ሰርካለም በ1997ቱ ግርግር ወቅት፤ ከቅንጅት መሪዎች እና ሌሎች የነጻ ፕሬስ ጋዜጠኞች ጋር በእስር የቆየች ሲሆን፤ ወንድ ልጇን ናፍቆት እስክንድርን የወለደችውም በቃሊቲ እስር ቤት ውስጥ በነበረችበት ወቅት መሆኑ ይታወሳል።
Eskinder, serkalem and Nafekot
Eskinder and Serkalem with their son Nafekot, right after they released from Kaliti prison in 2007,
አሁን ሰርካለም ፋሲል በተለይ ከአገር ለመውጣት የተገደደችው በባለቤቷ እስክንድር ነጋ ላይ በደረሰበት ህገ ወጥ እስር ሲሆን፤ በተለይም ከዚህ በኋላ ልጃቸው ወደ አሜሪካ መጥቶ እንዲማር በመወሰናቸው ጭምር ነው። ከሁለት ሳምንት በፊት  በኢ.ኤም.ኤፍ. ባቀረብነው ዘገባ ላይ እስክንድርን በቃሊቲ ያነጋገረችው ተባባሪያችን የእስክንድርን ነጋን ቃል እንዲህ በማለት ነበር የገለጸችው። “በ እስር ላይ ባለሁበት ባሁኑ ወቅት እጅግ አስቸጋሪ እና አስጨናቂ የሆነብኝ፤ የልጄ እና የባለቤቴ ጉዳይ ነበር። አሁን ግን ከአሜሪካ ኤምባሲ ቪዛ ስላገኙ፤ ከጥቂት ሳምንታት በኋላ ሰርካለም እና ልጄ ወደ አሜሪካ ይሄዳሉ። የነሱ ወደዚያ መሄድ ለኔ ትልቅ የህሊና እረፍት ይሰጠኛል።” ብሎ ነበር።
በዚህም መሰረት ሰርካለም ፋሲል የውጭውን አለም ስትቀላቀል፤ 132ኛ ኢትዮጵያዊ ጋዜጠኛ ትሆናለች ማለት ነው።

“ለዚህ (መንግሥት) ታላቅ ክብር አለኝ”


ሃይሌ! ወደ ፓርላማ?
haile gebreselasse


የዛሬ 10 ወር የሻለቃ ሃይሌ ገ/ሥላሴ ወደ ፖለቲካ የመምጣት ሁኔታን አስመልክቶ ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ሃተታ አቅርቦ ነበር፡፡ (እዚህ ላይ ይመልከቱት) ሰሞኑን አትሌቱ ወደ ፖለቲካው የመግባት ፍላጎቱንና “በምርጫ” ለመወዳደር መፈለጉ ብዙ እየተባለበት ይገኛል፡፡ ከዚህ አንጻር አሁን ላለው ሁኔታ ግንዛቤ ይሰጣል በማለት ከዚህ በፊት ያቀረብነውን ሃተታ በድጋሚ አትመነዋል፡፡

“ለኢትዮጵያ የጥምር መንግስት ያስፈልጋታል” በማለት በ1997 ምርጫ አጥብቆ ሲከራከር የነበረውና በአሁኑ ወቅት በከፍተኛ ደረጃ ኢንቨስትመንት ውስጥ የገባው ሻለቃ ሃይሌ ገብረስላሴ በኢትዮጵያ ቀደም ሲል ከነበሩት መንግስታትና ትውልዶች ይልቅ አሁን ላለው ትውልድ ከበሬታ እንዳለው በመግለጽ አስተያየቱን ሰነዘረ። የክብር ሪኮርዶቹን በሙሉ ለቀነኒሳ ያስረከበው ሃይሌ በእጁ የሚገኘውን ብቸኛ ሃብቱን (የህዝብ ክብር) እያሟጠጠ መሆኑ እየተገለጸ ነው።
ሃይሌ ይህንን የተናገረው መስከረም 12 ቀን 2004 ዓ ም ከተለያዩ አስተያየት ሰጪዎች ጋር በመንግስት ቴሌቪዥን (ኢቲቪ) አስተያየት በሰጠበት ወቅት ነበር። የቀድሞውን ስርዓትና ትውልድ “ድንጋይ ዳቦ በነበረበት፣ ፍራፍሬ ከጫካ ያለምንም ድካም ከሚሰበሰብበት” ዘመን ጋር ያወዳደረው ሃይሌ፣ “የአሁኑ ትውልድ” በማለት ያሞካሸውን ስርዓት ከተፈጥሮ ጋር ጦርነት በማካሄድ ለውጥ ማስመዝገበ መቻላቸውን አስምሮበታል።
“የባለ ራዕዩ መሪ” አቶ መለስ ገድል ለመዘከር በተዘጋጀ ቅንብር ላይ  በተደጋጋሚ አስተያየት ሲሰጥ የታየው ሃይሌ “አሁን የት ነው ያለነው?” በማለት ጠይቆ “አሜሪካ ኤምባሲ ቪዛ ለማግኘት ነው የምንጋፋው? አውሮፓ ሄደን እዛው ለመቅረት ነው…” በማለት ስደትን መርጠው ከአገራቸው የሚወጡትን ሸርድዶ አልፏል። አሁን ባለው የኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ለስደት የሚዳርግ ጉዳይ የለም ወደ ማለት አዝምሞ ተናግሯል። ሃይሌ ይህን ይበል እንጂ በተቃራኒው እስረኞች እንዲፈቱና የፖለቲካ እርቅ እንዲሰፍን እሰራለሁ ከሚሉት ፕሮፌሰር ይስሃቅ ጋር በሽምግልና እያገለገለ መሆኑ በአገሪቱ ውስጥ የሚታው እስርና እንግልት ከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱን የሚጠቅሱ አስተያየት ሰጪዎች የሃይሌን አስተያየት “ለንብረት ዋስትና የሚከፈል የንግግር ቫት” በማለት አጣጥለውታል።
ከኤርትራ ጋር ከተደረገው በቀር በኢትዮጵያ ይህ ነው የሚባል ጦርነት እንዳልተካሔደ ኢህአዴግን የሰላም አባት አስመስሎ ሃይሌ አመልክቷል። በዚሁም ምክንያት ቀደም ሲል ለጦርነት ይውል የነበረው የአገሪቱ በጀት ሙሉ በሙሉ ወደ ልማት ዞሯል ብሏል። የኢህአዴግ ተወካይ መስሎ አስተያየት የሰጠው ሃይሌ “ይህ አሁን የታየው ለውጥ በአስርና አስራ አንድ ዓመት ውስጥ የታየ ነው። አሁን ባለው አካሄድ ከአስር ዓመት በኋላ እንደርሳለን?” ሲል የራሱን ትንቢት አስቀምጧል።

በሀገራችን በአስደንጋጭ ሁኔታ በመስፋፋት ላይ ያለው ግብረሰዶማዊነትና ሴራው


(ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው)

one-man


ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ አስቀድሞ የተናቁና የተዘነጉ አንዳንድ ዘመን አመጣሽ ከባዕድ የገቡ ችግሮች እጅግ አሳሳቢ አደጋ እየጋረጡ እንደመጡ በተለይ በዚህ ወቅት በግልጽ ዕየታዩ ነው፡፡ ነገር ግን ሁኔታው ቀስ እያለ የሞቀና እያላመደ የተባባሰ የመባባስም ባሕርይ ስላለው የህልውና አደጋ የመጋረጥ ደረጃ (boiling point) ሲደርስ ሁሉ እዛ ደረጃ መድረሱን ሳናስተውለው በፍላት ኃይሉ ተቀቅለን ልንፈራርስ የምንችልበት አጋጣሚ ሰፊ ሆኗል፡፡ ይሄንን አዚማም የችግሩን ባሕርይ ከወዲሁ የተረዱ ግለሰቦችና አንድ ማኅበር በሀገራችን ግብረሰዶማዊነትና የጋረጠውን አደጋ፣ የደረሰበትን አሳሳቢ ደረጃ ለሕዝብ የማሳወቅ እንቅስቃሴ በዜግነታቸው ለሀገራቸው ወይም ለሕዝባቸው የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት ከመወጣት አንጻር ማንም ምንም ሳይላቸው ለሀገርና ለሕዝብ ባላቸው ፍቅር በግል ተነሣሽነት ብቻ በመንቀሳቀስ አቅማቸው የፈቀደላቸውን ያህል አስመስጋኝ ሥራን በማከናወን ላይ ይገኛሉ፡፡ በዚህ አጋጣሚ ይህ እንቅስቃሴ የሁላችንንም ንቁ ተሳትፎ የግድ የሚጠይቅ ነውና ሀገሬ ሕዝቤ ማንነቴ የምትሉ ሁሉ ሳትዘናጉና ሳይመሽ ተመሳሳይ ተግባር ለመሥራት ትተጉ ዘንድ በጥብቅ ማሳሰብ እወዳለሁ፡፡
ግብረሰዶም ማለት ምን ማለት ነው? ግብረሰዶም ማለት የሰዶም ሥራ ማለት ነው ሰዶም የሰዶማውያን ሀገር ናት ሰዶም በጥንት ዘመን ከ4ሺ ዓመታት በፊት በዮርዳኖስ ሸለቆ ከተቆረቆሩ ከተሞች አንዷ ነች፡፡ ቢጤዋ ጎሞራም እንዲሁ በዚህ ሸለቆ በሰዶም አቅራቢያ የተቆረቆረች ከተማ ነበረች እነዚህ ሁለት ከተሞች ተቃጥለው ከጠፉ በኋላ በአሁኑ ሰዓት በጨው ባሕር ተሸፍነው እንዳሉ ይገመታል፡፡
የእነዚህ ሁለት ከተሞች ሰዎች ታሪክ በመጽሐፍ ቅዱስ በዘፍጥረት 19፡1-22 ተቀምጧል፡፡ ባጭሩ ስናስቀምጠው ግን የሰዶምና የገሞራ ሰዎች ተፈጥሮና ሃይማኖት ከሚፈቅዱት ወይም ከሚያዙት ተስማሚ ከሆነው የተቃራኒ ፆታዎች የወሲብ ተራክቦ የተለየና አጸያፊ በሆነ የተመሳሳይ ፆታ ወሲባዊ ተራክቦ የረከሱ የጎደፉ በዚህ አጸያፊ ግብራቸውም እግዚአብሔርን ያስከፉ ያሳዘኑ በአመፃ ሥራ ያበዱ ርኩስ መንፈስ የሰለጠነባቸው የነገሠባቸው እግዚአብሔርም በዚህ ኃጢአታቸው ተቆጥቶ ከሰማይ እሳትና ዲንን አዝንቦ ያጠፋቸው የሁለት ከተሞተ ሰዎች ናቸው፡፡ ከዚያ ጊዜ ጀምሮም የዚያ አጸያፊ የተመሳሳይ ፆታ ወሲባዊ ግንኙነት መጠሪያ ሊሆኑ ቻሉ፡፡
ከዚያም በኋላ በሙሴ ሕግ ይሄንን ኃጢአት የሚፈጽሙ ሁሉ ያለ ምሕረት ይገደሉ ነበር፡፡ ዘሌዋዊያን 20፡10፣ ዘዳግም 23፡17 ሰዎች እግዚአብሔር መፍራትና ማምለክ ሲተው ለጣዖታትም ሲሰግዱ የዚህ ዓይነት ርኩስ መንፈስ እንደሚያድርባቸው መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራ፡፡ በመሆኑም ከመጽሐፍ ቅዱስ እንደምንረዳው ይሄ ኃጢአት በአሕዛብና በእስራኤል የተለመደ ነበር፡፡ በዚህ ዘመን ግን ግብረሰዶማዊያን የሌሉበት አንድም ሀገር እንደሌለ ይነገራል፡፡

በኦሮሚያ 10 ተጠርጣሪ ሙሰኞች በቁጥጥር ሥር ዋሉ


በሚሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ ተመዝብሯል

owwce


  • ተጠርጣሪዎቹ ሽፈራው ጃርሶ የሚመሩት ቦርድ ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች ናቸው
ከሙስና ጋር በተያያዘ የተጠረጠሩ አሥር የኦሮሚያ ክልል ውኃ ሥራዎችና ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ባለፈው ሰኞ በቁጥጥር ሥር ዋሉ፡፡
ኮሚሽኑ በቁጥጥር ሥር ካዋላቸው ከእነዚህ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በተጨማሪ፣  ሌሎች 15 የሥራ ኃላፊዎችን በቁጥጥር ሥር ለማዋል የፍርድ ቤት ማዘዣ አውጥቶ ፍለጋ መጀመሩን ምንጮች ገልጸዋል፡፡
ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ሥር የዋሉት የኮንስትራክሽን ዕቃዎች ግዥና የመንግሥትን የፋይናንስ ሕግ ባልተከተለ መንገድ ኪራይ ፈጽመዋል በሚል ጥርጣሬ መሆኑን፣ የክልሉ ሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን አስታውቋል፡፡ ኮሚሽኑ ለአንድ ዓመት ባካሄደው ጥናታዊ ምርመራ በዚህ የሙስና ወንጀል መንግሥትን በሚሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ እንዳሳጣው ለጉዳዩ ቅርበት የኮሚሽኑ ምንጮች ገልጸዋል፡፡
በቁጥጥር ሥር የዋሉት የክልሉ ውኃ ሥራዎችና ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ቢፋ በዳዳ፣ ምክትላቸው አቶ ጎዳና ዳባ፣ የፋይናንስ ቡድን መሪ አቶ ተሾመ አዱኛ፣ አቶ ተክሉ ተፈራ፣ የማኔጅመንት ኮሚቴ አባላት ወ/ሮ መስከረም ኤጀርሳ እና አቶ ግርማ ቂጣታ፣ የመጋዘን ኃላፊዋ ወ/ሮ ራሔል አሰፋና የክፍያ ሰነድ አዘጋጅዋ ወ/ሪት ሳምራዊት ግርማ፣ የጨረታ ኮሚቴ አባላት አቶ ዘለቀ ጎንፋና አቶ ዱላ ማሞ ናቸው፡፡
የኦሮሚያ ክልል ውኃ ሥራዎችና ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ ከተመሠረተ ሁለት አሥርት ዓመታትን ያስቆጠረ የክልሉ ግዙፍ የልማት ድርጅት ነው፡፡
ኢንተርፕራይዙ በኦሮሚያ ክልልና በሌሎች ክልሎች የሚካሄዱ የመስኖ ግድቦችና የመጠጥ ውኃ ፕሮጀክቶችን ግንባታ ሲካሄድ ቆይቷል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ መንገዶችንና ስታዲየሞችን ከመገንባቱም በላይ፣ በፌዴራል መንግሥት የሚመራውን ለደዴሳ ስኳር ፋብሪካ አገልግሎት የሚውል ግድብ በደዴሳ ወንዝ ላይ በመገንባት ላይ ይገኛል፡፡

Thursday, July 25, 2013

ከ “ድርጅታዊ ምዝበራ መጽሃፍ” ላይ የተወሰደ ማስታወሻ


July 23, 2013
በገለታው ዘለቀ
በቅርቡ ለንባብ የበቃው “ድርጅታዊ ምዝበራ” የተሰኘው  መጽሃፍ ደራሲ ዶክተር ኣክሎግ ቢራራ ጎንደር ተማሪ በነበሩበት ወቅት በኣንድ ነገር ተመስጠው ነበር። ይህ ምናባቸውን የገዛው ነገር በጎንደር ውስጥ እድሜው የትየለሌ የሆነ የኣንድ የዋርካ ዛፍ ተፈጥሮ ነበር። ይህን ዋርካ ባዩት ቁጥር ምናባቸው ተዛምዶን ይፈጥራል። ግዙፉ ዋርካ ዙሪያውን ያሉትን ቅርንጫፎችና ቅጠሎች ይዞ ዝንት ዓለም ይኖራል። ከምድሪቱ የሚያገኘውን ኣስፈላጊ ነገር እያመላለሰ ልጆቹን ያስተናግዳል። ቅጠሎቹም የራሳቸውን ድርሻ ይወጣሉ። ብዙ ቅርንጫፎችና ቅጠሎች እያሉ ግን ኣንድ ዋርካ ይባላሉ። ብዙ ሆነው እንደ ኣንድ ደሞ ኣንድ ሆነው እንደ ብዙ ናቸው። የበቀለባት ምድር ደግሞ እናት ትሆናለች። ዶክተር ኣክሎግ በዚህ ዋርካ ተፈጥሮ እየተደመሙ የኢትዮጵያን ብዙህ ተፈጥሮና ኣንድነት ያመሳስላሉ። ያን ዋርካ እያሰቡ ብዙሃዊትን ኢትዮጵያ በዚህ መጽሃፋቸው “ኢትዮጵያ ዋርካ ናት” ይሏታል። በዚህ በኢትዮጵያ ብዙህነትና ኣንድነት እምነታቸው ላይ የጸና ኣቋም እንዳላቸው  ከጽሁፋቸው በሚገባ የልባቸውን መረዳት ይቻላል። ይህ የጸና ኣቋማቸው ደሞ የጎሳ ተኮር ፌደራሊዝምን እና ኢፍትሃዊ እድገትን ኣምርረው እንዲታገሉት ያደረጋቸው ይመስላል። በዚህ መጽሃፋቸው የዚህችን ብዙህ ኣንዲት ኢትዮጵያን  ኣጠቃላይ ይዞታዋን ጥልቀት ባለው ሁኔታና በስፋት ይተነትናሉ፣ህመሟን ጉዳቷን ሁሉ ይመረምራሉ፤ መፍትሄውንም ይጠቁማሉ ኣማራጭ የፖሊሲ ኣቅጣጫዎችን በጠቆም ህክምናውንም ያሳያሉ።
Review of Dr. Aklog Birara's new book in Amharic
“ድርጅታዊ ምዝበራ” ይዞት የተነሳው ጭብጥ ኣንድ ብቻ ኣይደለም። የኢትዮጵያን ፖለቲካዊ ኢኮኖሚ(political economy) ጉዳይ እንደ ዋና ማጠንጠኛ ኣድርጎ የሰብኣዊ መብት ኣያያዟን፣ ታሪኳን፣ ኣጠቃላይ ማህበራዊ ጎኗን ሁሉ ይዳስሳል። ጸሃፊው ዶክተር ኣክሎግ የተለያዩ ጭብጦችን ይዘው  ሲጓዙ ኣምርረው የሚከራከሩላቸው ዋና ዋና ሁለት ጉዳዩች ግን ይታዩናል። እነዚህ የዚህ መጽሃፍ ምሰሶዎች  የሰብኣዊ ልማት(Human Development) ጉዳይና የፍትሃዊ እድገት ጉዳይ ናቸው። ፍትሃዊ እድገት ለዋናው እምነታቸው ለሰብኣዊ እድገት ዋና መንገድ(means) በመሆኑ እንደ ኣንድ ዋና ጭብጥ ኣጥብቀው ይዘውት ይታያል። በመጽሃፉ ውስጥ በሃይል የተተቹት የጎሳ ፌደራሊዝም ጉዳይ፣ የሙስና ጉዳይ የ ኣድሎና ሌሎች ጉዳዩች ሁሉ ለነዚህ መጽሃፉን ውስጥ ውስጡን ለሚከነክኑት  ሁለት የመጽሃፉ ወገኖች እንቅፋት ወይም ኣሜኬላ ተደርገው በመታየታቸው ነው።
ዶክተር ኣክሎግ በዚህ መጽሃፋቸው ውስጥ

በቃኽኝ


መሠረት አባተ ኖርዌይ ጁላይ 2013 

ለሥልጣኑ መሰንበት እንቅልፍ የለሹ የኢህአዴግ መንግሥት የመረጠው ሕዝብ ትዝ የሚለው ¨ሃገር-አቀፍ የምርጫ¨ ጊዜ 
ሲደርስ ብቻ ነው። ይህንኑ የኢህአዴግ ባህርይ ባለፉት የተለያዩ ሃገራዊ ምርጫዎች መዳረሻ ጊዜዎች ላይ ተፍ-ተፍ 
የሚልባቸውን ሥልቶች ማስታወስ ብቻ በቂ ነው። በ1997 ዓ.ም የምርጫ ወቅት የዜጐች ቁርጠኛ ውሣኔና ቁጣ በምርጫው 
ውጤት ላይ ያደረሰውን አሉታዊ ሁኔታዎች ያስበረገገው ኢህአዴግ ከዛ ዘመን ጀምሮ ከተከሰተው ድብቅ ባህርያቱ አንዱ 
ፈሪነቱ ነው። 

የህዝቡ ቁጣና ውሣኔ ውስጣዊ ድንጉጥነቱን ለአደባባይ ካበቃው በኋላ የኢህአዴግ የማስመሰል ትወና ረቀቅ ማለቱና 
ጭካኔው ማየሉ የባሰ ሆኗል፡፡ በከፍተኛ የመኖሪያ ቤት ችግር እየተሰቃየ ያለውን ሕዝብ ቀልብ ለመሣብና የሕዝብ ድምፅ 
አይበገሬ ኃይል እንዳለው በተመሠከረበት በ1997 ምርጫ ባለድል ለመሆን የጋራ ቤቶች ተጠቃሚ ላደርጋችሁ ነው በሚለው 
ምልጃው በመሣብ የተመዘገበው ዜጋ በጉጉት ካለበት ችግር ለመላቀቅ በማሰብ ተመዝግቦ ቤቱንም ሣያገኝ ስምንት ዓመት 
ካለፍ በኃላ ወቅት ጠብቆ ከች የሚለው ኢህአዴግ አዲስ የመኖሪያ ቤት ምዝገባ ብሎ አወጀ ለነባሮቹ ቅድሚያ እሰጣለሁም 
አለ ችግር እንዲያምኑት ያስገደዳቸው ዜጐች የምዝገባ ካርዳቸውን ይዘው ነባር ተመዝጋቢ ነኝ ብለው ቢቀርቡም ከመረጃ 
ቋቱ ውስጥ ስምህ ስምሽ የለም ተብለው በእነርሱ የምዝገባ ቁጥር የሌሎች የሥርዓቱ አፋሽ አጐንባሾች ስም ተተክቶ 
ሲያገኘው ዜግነቱን ጠልቶ በምሬት አቤቱታውን በግልም በህብረትም ቢያቀርብ ከፈለክ በአዲሱ ምዝገባ ተመዝገብ 
(ተመዝገቢ) ከሚል የንቀት ምላሽ ባሻገር ጉዳዬ ብሎ የሚጥፈው ሹም አላገኘም። 

በአሁን ወቅት ፖለቲካው የበላይነቱን ጠብቆ ለማቆየት ድርጅቱን በገንዘብ አቅም ለማፈርጠም በእራሱ ሥር ካሉ ግዙፍ 
የንግድ ተቋማቱ ዝርፊያ ተጨማሪ ለቤት ቁጠባ በሚል ሰበብ ዜጐች ከዕለት ጉርሣቸው እየነጠቁ በሚያስረክቡት ገንዘብ ነዶ 
ቋቱን በመሙላት ላይ ይገኛል። ‘ሌባ እናት ልጇን አታምንም’ እንዲሉ በሥሩ ካለው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ውጭ የዚህ 
ተግባር ተሣታፊ እንዳይሆኑ በሩን በመዝጋት የግል ባንኮችን ህልውና ከስጋት ውስጥ ከቶታል። በዚህም የእነርሱን ሃገራዊ 
የዕድገት ድርሻም በማቀጨጭ ላይ ይገኛል።

ዜና መጽሐፍ፤ ፕሮፌሰር መስፍን የግጥም መጽሐፍ እነሆ አሉን!


እንጉርጉሮዜና መጽሐፍ፤  ፕሮፌሰር መስፍን የግጥም መጽሐፍ እነሆ አሉን!
በመጀመሪያም፤
እኒህ ሰውዬን የሚያክል ብርቱ መቼም ኢትዮጵያችን ያላት አይመስለኝም፡፡ ሁሉም ነገር ይቅርና ጎረምሶቹን ፖለቲከኞች እና ምሁሮች በሚያስከነዳ ትጋት፤ በየወቅቱ ሀሳባቸውን ሳይታክቱ በመፃፍ ያጋሩናል፡፡ በየአመቱም የመፅሀፍ በረከታቸውን ያድሉናል፡፡ በእውኑ እንደርሳቸው ያለ ማን አለ… ብለን በማድነቅ ዜናችንን እንጀምራለን!
ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማሪያም “ዛሬም እንጉርጉሮ” በሚል ርዕስ አዲስ የግጥም መፅሀፍ ማሳተማቸውን ከወደ ፊኒፊኔ የደረሰን ወሬ ያስረዳል፡፡ ፕሮፍ እንዲህ ይሉናል፤
“እንጉርጉሮ በመሰረቱ የግል ነው ለአንባቢ የተዘጋጀ አይደለም ማለት ነው፡፡ አንድ ሰው ከገዛ ራሱ ስሜት ጋር የሚያደርገው ትግል ነው፤ ራሱ፤ ራቁቱን እውነቱን የሚያይበት መስተዋት ነው፤ ቢሆንም የሰው ሁሉ መሰረታዊ ስሜት አንድ አይነት በመሆኑ ተመሳሳይ አጋጣሚ ተመሳሳይ ስሜት ሊፈጥር ይችላል፤ ከዚያ በቀር አንድ ሰው የጠቅላላ ህብረተሰቡ ደስታ እና ምቾት፤ ስቃይ እና ጭንቀ፤ ተስፋ እና ምኞት ተካፋይ መሆኑ በጥልቅ ከተሰማው በእምነት የግል በሆነ መንገድ ያንን ጥልቅ የሆነ ስሜት እንደ ህብረተሰቡ ሆኖ ሊያስተጋባ ይችላል፡፡ የእኔ ሙከራ ተሳክቶ እንደሆነ እና አንዳልሆነ መፍረዱ የአንባቢዎች ፈንታ ነው፡፡”
ታድያ የፈራጅነት ሚና ሰጥተውን ያበረከቱልንን ይቺን የግጥም መጽሐፍ ገዝተን፤ ግጥም አድርገን ብንጠጣት እና ብንፈርዳቸው ምን ይለናል፡፡ ምንም!
በመጨረሻም፤
በውጪ ሀገር ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ዛሬም እንጉርጉሮ እንዴት እንደምናገኛት ጠይቄ እነግራችኋለሁ፡፡

የሰማያዊ ፓርቲ እንቅስቃሴ የወያኔን ቁንጮዎች ስጋት ላይ ጥሏል

July 25, 2013

ህዝብን ለማስፈራራት በታቀደ መለኩ እንደተለመደው የወያኔ ባለስልጣናት በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ እጅግ ስላሰጋቸው የሰማያዊ ፓርቲ እንቅስቃሴ የሚከተለውን አስፍረዋል፣
ye semayawi party selamawi self
የሰማያዊው ፓርቲ ጥቁር ተግባራት
ሰማያዊ ፓርቲ በጠራው ሕዝባዊ ሰልፍ ላይ ያቀረባቸው ጥያቄዎች የተሰላፊዎች ጥንቅርና መሰረታዊ ዓላማ በእጅጉ አነጋጋሪ ለሆኑ ጉዳዮች መነሻና መንደርደሪያ ሆነውኛል።
ሰማያዊ ፓርቲ ከአንድነት ፓርቲ ባለመስማማትና በልዩነት ራሳቸውን ያገለሉ፣ መርህ ይከበር በሚል ተሰባስበው የነበሩ ግለሰቦች የመሰረቱት ፓርቲ ነው፡፡ ወደ ኋላ ስንመለስም በ1997 ዓ.ም ቅንጅትን ከመሰረቱትና የከሸፈውን አመጽ በማስተባበርና በመምራት ከፊትና ከኋላ የነበሩ፤ ዛሬ ደግሞ የቀድሞውን ማንነታቸውን ሳይለቁ በአዲስ መልክና በአዲስ ኮፍያ ለመንቀሳቀስ እየሞከሩ ያሉ ናቸው፡፡
አንድ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲ ሕገ መንግስቱ በሰጠው መብት በሰላምና በሕጋዊ መንገድ ሕጉንና ስርዓቱን አሟልቶ መንቀሳቀስ ይጠበቅበታል፡፡ ሰማያዊም ፓርቲ ሆነ ሌሎቹ ተቃዋሚ ፓርቲዎች በውጭ ከሚገኘው ጽንፈኛና አክራሪ ኃይል ጋር በመቀናጀት በአረቡ ዓለም የታየውን አብዮት ወደ ኢትዮጵያ እናመጣለን በሚል ለረዥም ጊዜያት ውስጥ ውስጡን ሲንቀሳቀሱ ቆይተዋል፡፡ ሆኖም እውነቱን የተረዳው ሕዝብ በአንድም ሆነ በሌላ መልኩ ይህንን ሊቀበላቸው አልፈቀደም፡፡

Wednesday, July 24, 2013

ስለ ቂሊጦ ዝም አልልም!


ቂሊጦስለ ቂሊጦ ዝም አልልም!
በቂሊጦ እስር ቤት በርካታ ወንድሞቻችን በጸረ ሽብር አዋጁ ተገን በኦነግ ስም ታስረው መከራቸውን እያዩ ነው፡፡ አሁን በቅርቡ የምግብ ማቆም አድማ አድርገው የነበሩት እነዚህ ወንድሞቻችን የርሃብ አድማ ሲያደርጉ የመጣላቸው ሀኪም አይደለም፡፡ ልዩ ሀይል የሆነ ወታደር ነው እንጂ…  ልብ በሉልኝ፤ በርሃብ ለደከመ ሰውነት ገራፊ ወታደር!!!
ይሄ አይነቱን ጭካኔ ሰይጣን እንኳን አድርገው ቢባል “አረ ፈጣሪ ምን ይለኛል” ብሎ መፍራቱ አይቀርም፡፡ ፈጣሪን መፍራት የተሳናቸው ሰዎቻችን ግን በድፍረት እንዲህ ጨከኑ…
በብረት ክርችም ካሰሩ በኋላ በርሃብ የደከሙ ሰዎችን መደብደብ ጀግና ያስብል ይሆን…!  ወይስ “ጀግንነቱን ቀድመን ተብለናል እስቲ ደግሞ በእርኩሰት ሳጥናኤልን አንብለጠው” ብለው እየተወዳደሩ ነው…! ግራ ገብቷቸው ግራ አጋቡንኮ…
እንደሰማነው ገድል ከሆነ… (መሆኑን ግን አንጃ…) ህውሃት ያኔ ጫካ እያለች የሚታኮሷትን  ወታደሮች የያዘቻቸው እንደሆነ  እንክብካቤዋ በጦርነት ሳይሆን በፍቅር የማረከች ነበር የምትመስለው ብለው ድርሳን ፀሀፊቿ እና ኢቲቪዋ ነገሮናል፡፡
ታድያ ያኔ ሲታኮሷት የነበሩ ሰዎችን ስትንከባከብ የነበረች ድርጅት ዛሬ ከትምህርት ቤት እና ከሰላማዊ መስሪያ ቤት የሰበሰበቻቸው ሰዎች ላይ እንዲህ መሆኗ … አብዳ ነው ተናዳ….!?
“እስቲ ጠይቁልኝ ይቺን ሰው በሰው…
አያያዟ ሁሉ እንደማሆን ነው… ”
(እስቲ ተቀበል…)
እውነቱን ለመናገር ይሄ መካሪ ማጣት ነው፡፡ በዚህ ርግጫ መሰል ርምጃ፤  በእስር ላይ ያሉትን ፀጥ ማሰኘት ይቻል ይሆናል፡፡ በውጪ ያሉትን ግን ያበረታል፡፡ የበረቱት ሲታሰሩ ደግሞ ሌሎች ይበረታሉ፡፡ እነርሱም ሲታሰሩ ሌሎች ይበረታሉ… ያ ማለት ምን ማለት እንደሆነ… ከተረሳ የህዳሴው ዋዜማ የሚለውን ቪዲዮ ድጋሚ መመልከቱ ሳይበጅ አይቀርም…!
ለማንኛውም በቂሊጦ የሚገኙ ወንድሞቻችን እየደረሰባቸው ላለው ስቃ የህዝ ለህ እያሉ ነው…! እኔ ስለ እነርሱ ዝም አልልም….  ኪቦርድ ያለህ በኪቦርድህ ድምጽ ለህ በድምፅህ አግዘኝ…. ስለ ወንድሞቼ እጮሃለሁ…!
ኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡ….!!!

Tuesday, July 23, 2013

ሰበር ዜና፣ አዲስ አበባ ከተማ በግድግዳ ጽሁፎች (ግራፊቲ) ተሸፍና አደረች

July 23, 2013

ድምፃችን ይሰማ
ሰኞ ሐምሌ 15/2005

እሁድ ምሽት ለሰኞ አጥቢያ በአዲስ አበባ የተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ ቦታዎች የሙስሊሙን ህብረተሰብ ጥያቄዎች በሚያንጸባርቁ ጥቅሶች ተጽፎባቸው አደሩ፡፡ በከተማዋ የተለያዩ መንገዶች፣ የመንገድ አካፋዮች እና አጥሮች ላይ መንግስት ሕገ መንግሰቱን እንዲያከብርና በእምነት ጣልቃ መግባቱን እንዲያቆም የሚጠይቁ ጽሁፎች በትላልቅ ቁመት ለህዝብ በሚታይ መልኩ ተጽፈው የተገኙ ሲሆን ይህ በተጻፈባቸው ቦታዎችም ሰዎች ሁኔታውን በትኩረትና በግርምት ሲመለከቱ እንደነበር ታውቋል፡፡
Ethiopian Muslims protest, Addis Ababa1
በካዛንቺስ፣ በጦርሀይሎች በውንጌት አስኮ መንገድ እንዲሁም ገና በውል ባልታወቁ ቦታዎች ደምጻችን ይሰማ፣ ኮሚቴው ይፈታ፣ ሕገ መንግስቱ ይከበር፣ ጥያቄያችን ይመለስ፣ በእምነታችን ጣልቃ አትግቡብን የሚሉ ጽሁፎች ተጽፈው የታዩ ሲሆን በካባቢው የሚገኙ የወረዳ አስተዳደሮችም በተፈጠረው ነገር በመደናገጥ ጽሁፎቹን ለማጥፋት ጥረት እያደረጉ ይገኛል፡፡ የጎዳና እና የግድግዳ ጽሁፎች በአለም የታወቁ የመቃወሚያ ዘዴዎች በመሆናቸው ህብረተሰቡ መልእክቱን ለሚመለከተው አካል ለማድረስ የሚጠቀምባቸው ናቸው፡፡

ሰበር ዜና: ኢህአዴግ አንድነት ፓርቲን የሚያወግዝ ሰላማዊ ሰልፍ ጠራ

July 23, 2013

በደቡብ ወሎ ዞን በሚገኘው ኩታበር ወረዳ አንድነት ፓርቲ ሐምሌ 7 ቀን 2005ዓ.ም. በደሴ ያካሄደውን ህዝባዊ የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ በመቃወም ህዝቡ ሰላማዊ እንዲወጣ ኢህአዴግ እያስገደደ መሆኑን ምንጮቻችን በተለይ ለፍኖተ ነፃነት ገለፁ፡፡
የኩታበር ወረዳ ነዋሪ ሰልፍ እንዲወጣ የተደረገው ነገ ረቡዕ ሐምሌ 17 ቀን 2005 ዓ.ም. ጠዋት መሆኑም ታውቋል፡፡ በተለይ ሰፊ የማስፈረሳሪያና የቅስቀሳ ስራ እየተካሄደ ያለው በወረዳው ቀበሌ 05፣06 እና 07 መሆኑንም ምንጮቻችን ጨምረው ገልፀዋል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ የኢህአዴግ ካድሬዎች ገበሬውን በግድ ከአቅሙ በላይ የዘር ማዳበሪያ ውሰዱ እያሉ ከፍተኛ ገንዘብ ከማስከፈላቸው በተጨማሪ ለአልማ(ለአማራ ልማት ማኀበር)፣ለአባይ፣ ለመሬት ግብር እየተባሉ ከፍተኛ ዋጋ በመጠየቃቸው እና ነዋሪዎቹ አቅማቸው እንደማይፈቅድ ሲናገሩ ወደ እስር ቤት እየተወሰዱ በመሆኑ ቤት ንብረታቸውን ጥለው ከአካባቢው እየተሰደዱ እንደሆነም ተጠቁሟል፡፡ ማዳበሪያና ዘር አንወስድም ያሉ ገበሬዎችንም መሬታችሁ ይነጠቃል በሚል የወረዳው አስተዳዳሪ አቶ ደምሴን ጨምሮ የወረዳው ሹማምንት እያስገደዱ እንደሆነ ነዋሪዎቹ በተለይ ለፍኖተ ነፃነት ገልፀዋል፡፡
ስለጉዳዩ የዝግጅቱ ክፍሉ የወረዳውን አስተዳደር አቶ ደምሴን እና የወረዳውን ግብርና ጽህፈት ቤትና የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ኃላፊዎችን ለማናገር ጥረት ቢደረግም አልተሳካም፡፡
ምንጭ፣ ፍኖተ ነጻነት
Millions of voices for freedom - UDJ

Monday, July 22, 2013

ሀገራችን ኢህአዴግ አክራሪነትን እንደሚያሰሰጋት ተሰጋ!


1004887_10201012302803720_363214582_n
ሀገራችን ኢህአዴግ አክራሪነትን እንደሚያሰሰጋት ተሰጋ!

ይቺ ጨዋታ ፍትህ ጋዜጣ አዲስ ታምስ መጽሄት ከዛም ልዕልና ጋዜጣ ባደረጉት መተካካት አሁን ተራውን ለተቀበለችው አዲሲቱ ፋክት መፅሄት የተላከ ነው፡፡ እስቲ የድረ ገፃችን አንባቢዎች ደግሞ ከተመቻቸው ያንበቧት ተብላ የተለጠፈች ናት!
ርዕሴ እንዳይረዝምብኝ ሰግቼ ነው እንጂ፤ “ሀገራችን ኢህአዴግ አክራሪነት እንደሚሰጋት  ተሰጋ (ድርብ ሰረዝ) ሁላችንም ይሄንን ጉዳይ እንዋጋ (አሁንም ድርብ ሰረዝ) ኋላ ይቆጨናል ሲያስከፍለን ዋጋ…(ቃል አጋኖ)  ብለው ደስ ይለኝ ነበር፡፡
እንግዲህ ጥናት አትኚዎች እና ምርምር አድራጊዎች ከፈለጉ ተመራምረው የምለውን “ፉርሽ” ያድርጉት እንጂ የእኔ አነስተኛ ጥናት ግን በአሁኑ ሰዓት ሀገሪቷን በጣም እያሰጋት ያለ አንድ አደገኛ ነገር እንዳለ አመላክቶኛል፡፡ እርሱም ኢህአዴግ አካራሪነት ነው፡፡
በተደጋጋሚ ኢህአዴግዬ እንደነገረችን ሀገራችን የኃይማኖት አክራሪነት ያሰጋታል ተብለናል፡፡ አረ ምን መባል ብቻ በዚህ የተነሳ የተለያዩ እርምጃዎች እና እርግጫዎች እየተወሰዱብን አይደል እንዴ…
እኔ ሳስበው (አረ ምን እኔ ሳስበው ብቻ ሁላችንም እንደምናውቀው … የሀይማኖት አክራሪነት ለአንድ ማህበረሰብ ከባድ ችግር ነው፡፡ ሀይማኖተኞች እምነታቸውን ለራሳቸው በቅጡ ማመናቸው ብቻ አልበቃ ብሏቸው “ሌላ እምነት የሚያምን የተረገመ ነው” ብለው ማሰብ ሲጀምሩ ጦሱ ያኔ ይጀምራል፡፡ ይህ ችግር እጅግ ሲበረታ ውጤቱ በአለማችን ላይ ያየናቸውን በርካታ አሰቃቂ ጉዳቶች መንስኤ ወደ መሆን ያመራል፡፡ ይሄ ደግሞ ያማርራል፡፡ ይደብራልም፡፡ እዝች ላይ ምልክት ያድርጉልኝ….
አረ ቆይ ወዳጄ እስቲ በቅጡ ሰላምታ እንሰጣጥ … እንዴት አሉልኝ… ጤናዎ እንዴት ነው… ከዶክተር ቴውድሮስ ወዲያ የመጡት ጤና ጥበቃ ሚኒስትር እንዴት ናቸው… ምንውሳ ድምጻቸው ብዙ አይሰማም…! አንገታቸውን ደፍተው እና ድምፃቸውን አጥፍተው ለእኛ ጤና እየደከሙ ስለሆነ ነው… ይበሉ እና እስቲ ያስደስቱኝ በሞቴ!
ዶክተር ቴውድሮስ አድሃኖምን ካነሳን አይቀር እኒህ ሰውዬ “ፖዘቲቭ” ሆነው ተገኙ የሚባለው ነገር እንዴት አዩት…
ይሄን ጊዜ እርስዎ በልብዎ …ታድያ ለአንድ የኢህአዴግ አባል ፖዘቲቭ መባል ብርቅ ነው እንዴ… ብለው፤ አምባ ገነንነት ፖዘቲቭ፣ ሙስና ፖዘቲቭ፣ ኢመልካም አስተዳደር ፖዘቲቭ፣ ጉራ መቸርቸር ፖዘቲቭ፣ መሬት መቸርቸር ፖዘቲቭ፣ ትዕቢት ፖዘቲቭ፣ ማን አለብኝነት ፖዘቲቭ፣ ኪራይ ሰብሳቢነት ፖዘቲቭ… አባል ሰብሳቢነት ፖዘቲቭ ኡ ኡ… ደከመኝ… ፖዘቲቭ… እያሉ ሲደረድሩት ታየኝ፡፡

Saturday, July 20, 2013

ከፍተኛ የሙስና ወንጀል ሲጋለጥ


July 19, 2013
ከኢየሩሳሌም አርአያ
ወ/ሮ አዜብ መስፍን ከአቶ ገ/ዋህድ፣ አቶ ነጋና ምህረተአብ ጋር በመመሳጠር በሶስት መርከብ ስሚንቶ አስጭነው አገር ውስጥ በማስገባት ከፍተኛ የሙስና ወንጀል መፈፀማቸውን ምንጮች አጋለጡ። በተከለከለ ፍራንኮ ቫሉታ ፈቃድ አገር ቤት የገባው ስሚንቶ በመቶ ሚሊዮን የሚቆጠር ትርፍ አዜብና ግብረአበሮቻቸው እንደዛቁበት ያረጋገጡት ምንጮቹ፣ አያይዘውም ጉዳዩ በደህንነት ሹም አቶ ጌታቸው አሰፋ እጅ እንደገባ አስታውቀዋል። በሕገወጥ መንገድ የውጭ ምንዛሪ በከፍተኛ ደረጃ በመመደብና አስፈላጊውን ትእዛዝ በመስጠት እንዲሁም የጥቅም ተካፋይ በመሆን ግንባር ቀደም ሚና የተጫወቱት አዜብ መስፍን ከዚህ ድርጊታቸው በተጨማሪ ከዚህ ቀደም ከስሚንቶው ጋር በተያያዘ ተመስርቶ የነበረውን ክስ እንዲቋረጥ ማድረጋቸውን የጠቆሙት ምንጮች፣ ይህና ሌሎች ተያያዥ የወንጀል ድርጊቶችን የሚያስረዱ ማስረጃዎች በአቶ ጌታቸው እጅ እንደገቡ አረጋግጠዋል። አቶ ነጋ ገ/እግዚያብሄር በኮንትሮባንድ ቀረጥ ሳይከፈልባቸው ወደ አገር ውስጥ ያስገቧቸው የህክምና መሳሪያዎች ተይዘው ክስ ከተመሰረተባቸው በኋላ ክሱ እንዲቋረጥ ያደረጉት አዜብ መሆናቸውን የገለፁት ምንጮቹ፣ በተለያዩ ጊዜያት የገቡና የነጋ ገ/እግዚያብሄር ንብረት የሆኑ ከባድ ተሽከርካሪዎች ያለቀረጥ እንዲገቡ በማድረግ አዜብ መተባበራቸውን አያይዘው ገልፀዋል። ጉዳዩም «ክስ በማቋረጥ..» በሚል በሰነድ ተደግፎና ከሌሎች መሰል ድርጊቶች ጋር ተያይዞ በታሳሪዎች ላይ ክስ የቀረበ ቢሆንም፣ ዋናው ተዋናይ ግን አዜብ ሳይጠየቁ መቅረታቸው አነጋጋሪ መሆኑን ምንጮቹ አልሸሸጉም። ከስሚንቶው ጋር በተያያዘ አስተያየት የጠየኳቸው ታዋቂ የሆኑ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ባለሙያ ፥ « መንግስት ስለ ፍራንኮ ቫሉታ ሕግ አውጥቷል፤ ይህን በመተላለፍ ሶስት መርከብ ስሚንቶን የሚያክል ነገር በታሳሪዎቹ ብቻ ሊፈፀም አይችልም፤ ከዚህ ሕገወጥ ድርጊት በስተጀርባ ትልቅና ቁልፍ ስልጣን ያለው ሰው እጁ እንዳለበት ግልፅ ነው።» ብለዋል።

Thursday, July 18, 2013

ኢህአዴግ በሩን እንዲከፍት የዓለም ባንክ አዘዘ


የማነቂያው ገመድ ከርሯል፤ “ትግሉ ይቀጥላል” ኦባንግ ሜቶ

world-bank


ኢህአዴግ ለሚገዛት ኢትዮጵያ ከፍተኛ መጠን ያለው ዕርዳታ የሚሠጠው የዓለም ባንክ፤ ለዕርዳታና ልማት የሚልከው ገንዘብ ኢህአዴግ የሕዝቡን ሰብዓዊ መብት ለመጣስ ተጠቅሞበታል በሚል ሙሉ ምርመራ እንዲካሄድ አዘዘ፡፡ የባንኩ ውሳኔ ኢህአዴግን የማነቂያው ገመድ እንደሚያከረው ተገለጸ፡፡ የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዋና ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ ሜቶ በተለይ ለጎልጉል በሰጡት መግለጫ “ይህ በጥናት ከምናካሂደው ትግል አንዱ ውጤት ነው፤ ገና ጅማሬ ነው፤ ጠንክረን እንሠራለን” አሉ፡፡
የዓለም ባንክ ለልማት ሥራዎች የሚሰጠው የእርዳታ ገንዘብ በኢትዮጵያ በተለይም በጋምቤላ ክልል የሚኖሩትን ዜጎች ሰብዓዊ መብት በመጣስ ላይ ውሏል በሚል ከዚህ በፊት ክስ ቀርቦበት እንደነበር ይታወሳል፡፡ ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ጉዳዩን ከ9 ወራት በፊት በዘገበበት ወቅት ተጠቂዎቹ ዜጎች ያቀረቡትን ማስረጃና የኢንስፔክተር ቡድኑ የሚያደርገውን ምርመራ በዝርዝር ሰፍሮ ነበር፡፡ በወቅቱ ምርመራውን ያደረገው የመርማሪ ቡድን (ኢንስፔክሽን ፓናል) በአካባቢው የሚገኙትን ተጠቂዎች ካነጋገረ በኋላ ለባንኩ የሥራ አመራር ቦርድ በሰጠው ሪፖርት በዕርግጥ የዕርዳታው ገንዘብ በሰብዓዊ መብት ረገጣ ላይ መዋሉን ይፋ አድርጓል፡፡
ይህ የኢንስፔክተር ቡድን ከፍተኛ ሥልጣን ያለው መ/ቤት ሲሆን የዓለም ባንክ ለአገራት የሚሰጠውን ገንዘብ በትክክለኛ ቦታ ላይ አለመዋሉን በመጥቀስ ክስ የሚያቀርቡ ወገኖችን ጉዳይ በመከታተልና ቦታው ድረስ የራሱን ምርመራ በማካሄድ ውጤቱ ተግባራዊ እንዲሆን የባንኩን እጅ የማስጠምዘዝ ዓቅም ያለው እንደሆነ ከዚህ በፊት ያካሄዳቸው የምርመራ ውጤቶች ይጠቁማሉ፡፡
ቡድኑ መረጃውን ይፋ ባደረገበት ወቅት ቢያንስ የ600 ሚሊዮን ዶላር ዕርዳታ ከዚህ ካለፈም በቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ የማጣት ጭንቀት ውስጥ የገባው ኢህአዴግ አንገቱ መታነቁን ሲያስተውል የኢንስፔክሽን ቡድኑን ውሳኔ አጣጥሎት ነበር፡፡ በወቅቱ መግለጫ የሰጡት በጠ/ሚ/ር ሃይለማርያም ቢሮ አፈቀላጤ የነበሩት ጌታቸው ረዳ “ከኢንስፔክተር ቡድኑ ጋር አንተባበርም፤ ትብብር ማድረግ ካስፈለገንም ከዓለም ባንክ ጋር ይሆናል፤ … ይህ በኢህአዴግ ላይ የተነጣጠረ የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ ነው፤ … ኢንስፔክሽን ፓናል የራሱ የዓለም ባንክ ኢንስፔክተር (መርማሪ) ቡድን አይደለም፤ … ቡድኑ የራሱን ልብወለድ ዘገባ በዓለም ባንክ አሠራር ላይ ለመጫን ያደረገው ሙከራ ነው” በማለት ነበር ያጥላሉት፡፡

Wednesday, July 17, 2013

ትንሽ ቁምነገር፤ ለብሄር ብሄረሰቦች በሙሉ


አበበትንሽ ቁምነገር፤ ለብሄር ብሄረሰቦች በሙሉ
ኢህአዴግ በአራት ድርጅቶች ግንባር የተገናበረ ነው፡፡ (የተደናበረ፤ አላልኩም፡፡ የተገናበረ ማለት፤ በእኔኛ ቋንቋ ግንባር የፈጠረ ማለት ነው) ስማቸውም ኦህዴድ፣ ብአዴን፣ ደህዴን እና ህውሃት ይባላሉ፡፡
ደሞ አሉልህ አጋር ተብለው አገር የሚበጠብጡ እንደ እነ ሶህዴፓ፣ ጋህዴን ቤህዴፓ ምናምን የመሳሰሉት፡፡
ብታምንም ባታምንም… ልልህ ነበር በአደባባ የምታውቀውን ሀቅ ማመን አለማመንን ምን አመጣው… ብቻ እነዚህ ሰዎች ኦሮሞዎች ናቸው፣ አማሮችም ናቸው፣ ደቡቦችም ናቸው፣ ትግሬዎች ናቸው  ቤኒሻጉልም ናቸው ሶማሌዎችም ናቸው ጋንቤላዎችም ናቸው፡፡
ሁሉም በየክልላቸው ላይ ቢያንስ ቢያንስ ዜጎቻቸውን አበሳ የማሳየት ፈቃድ አላቸው፡፡
የትግራዩ ባለስልጣን ትግራይ ላይ ትግሬዎችን ያስራል ከመኖሪያቸው ያፈናቅላል… ወዘተ ይወዝታል፡፡ የኦሮሞው ባለስልጣን ኦሮሞ ዘመዶቹን ኦነግ ነህ እያለ ይገርፋል ያስራል ያሳድዳል ሻ ሲለው ደግሞ ተኮሶ ይገድላል፡፡ አማራ ክልል ብትሄድ ራሱ አማራው ባላስልጣን መርጠውኛል የሚላቸውን አማራ ወገኖቹን ሲያማርር ታየዋለህ፡፡ ደቡብም ብትሄድ ተመሳሳይ ነው፡፡
እውነቱን እንነጋገር ከተባለ ሁሉም መከራውን እያየ ያለው ኢህአዴግን እንደ ግል አዳኛቸው እና አዳኛቸው (ጠብቆ እና ላል) በተቀበሉ ዘመዶቹ ማናለብኝነት የተነሳ ነው፡፡ የምሬን ነው የምልህ ኦሮሞው በአሁኑ ሰዓት በደል እየደረሰበት ያለው በኦሮሞ ዘመዶቹ ነው አማራውም ትግሬውም ደቡቤውም እንደዛው፡፡
ስለዚህ በዝምድና መደራጀት የትም አያደርስም በሀሳብ መዛመድ ነው የሚበጀው፡፡
ብሄሮችን መዋጋት ሳይሆን አጉራ ዘለል ዘመዶቻችንን ነው ተዉ ማለት ያለብን፡፡
ለራስህ ብዬ ነው!