Wednesday, April 30, 2014

ለወይዘሮሪት ኢህአዴግዬ ሰው ማሰር ሻሽ ሸብ ከማድረግ እኩል ቀላል አይደለምን…


9+ለወይዘሮሪት ኢህአዴግዬ ሰው ማሰር ሻሽ ሸብ ከማድረግ እኩል ቀላል አይደለምን…
ወዳጄ….
በሩቁ የምታውቀው ወዳጅህ ሲታሰር፤ አሳሪዎቹ የሚደረድሩልህ ምክንያት ትንሽ እውነት ሊኖረው ይችላል ብለህ ልታስብ ተችላለህ ከዛ አሳሪዎች መቼም ማሰር አይታክታቸውም አይደል፤ ቀረብ የሚልህ ወዳጅህን ደግሞ ያስራሉ፤ ማሰር ብቻም አይደል ያለ የሌላቸውን ምክንያቶች በቴሌቪዥን በራዲዮ አከታትለው ይነግሩሃል ይሄኔ ግራ ትጋባለህ …መንግስትን ያህል ነገር እንዲህ አይን አውጥቶ ሊዋሽ ይችላል….. ወይስ ወዳጄን በቀጡ አላውቀውም ነበር ብለህ ይምታታብሃል…
የኔ ጌታ አሳሪ ጠዋት ቀበቶውን ካሰረ ሰዓት አንስቶ ሙሉውን ቀን፤ “ደግሞ ማንን ልሰር….” ሲል ነው የሚወለው። እና እያለ፣ እያለ ከራስህ በላይ አውቀዋለው የምትለውን ወዳጅህን ወይም እራስህን ጥርቅም አድርጎ ያስራል። ይሄኔ የፈለግ ምክንያት ቢደረደርልህ አሳሪውን ልታምን እንደማትችል የታወቀ ነው ሀቁ ያለው ራስህ ጋ ነዋ!
እናም ወዳጄ…
በተለይ እንደ ኢህአዴግ ያለ የማሰር ሱስ ያለበት አሳሪ በሩቁ የምታውቃቸውንም በቅርብ የምታውቃቸውንም አስሮ ምክንያት ሲደረድር ወዳጆችህን አተጠራጠር እውነቴን ነው የምልህ መንግስታችን ሰዎችን ሲያስር ጥጃ የማሰር ያክል አይጨንቀውም። ለዚህ ደግሞ አጥጋቢ ምክንያት ሲፈልግ አየገኝም፤ በቃ የአይንህ ቀለም ካላማረው ያስርሃል።
የ ዞን ዘጠኝ ጦማሪዎችን የማውቃቸው ማንም ሰው የታሰረ እነደሆነ መዝገብ አገላብጠው መታሰሩ ከህግ አንጻር፣ ከህገ መንግስት አንጻር፣ ከሞራል አንጻር፤ እያሉ የህሊና ፍርድ ሲሰጡ ነው። ሙስሊም ሳይሉ ክርስቲያን ሳይሉ ኦሮሞ ሳይሉ ጋምቤላ ሳይሉ ያለ ለዩነት ጆሯቸው የደረስ አይናቸው ያየውን ኢፍትሃዊነት ሲያወግዙ ነው። ደግሞ ሲያውግዙ ብቻ አይምሰልህ መንግስት የሚሰራቸው መልካም ነገሮችም እውቅና ሊሰጠው ይገባል፤ ጽንፈኛ መሆን ተገቢ አይደልም ሲሉም ይውቅሱሃል። ዛሬ መንግስት እነዚህን ወጣቶችን ሰባስቦ አስሯቸዋል። (ለወይዘሮሪት ኢህአዴግዬ ሰው ማሰር ሻሽ ሸብ ከማድረግ እኩል ቀላል ነው (በሌላ ቅንፍ ኢህአዴግዬን ወይዘሮሪት ያልኩታ ታግባ አታግባ በቀጡ ሰላላወቅሁ ነው፤ ግራ ስታገባን ግን በድንብ አውቃታለሁ… ሃሃ))

የኢህሃዴግዬ የቀለም አብዮት …!


ቀለምየኢህሃዴግዬ የቀለም አብዮት …!
እንግዲህ መጀመሪያ ለቃላቶቻችን ፍቺ እንስጥ፤
ኢህአዴግ ያው ምንም ፍቺ አያስፍልጋትም ያው ኢህአዴግ ናት! (በቅንፍም፤ ቢቻል ከያዛት አባዜ ራሷ በራሷ ወይም በንስሃ አባቷ በኩል ትፋታ እንጂ እኛ እርሷን ስንፈታ አንገኝም፤ ብለን እንጨምራለን… እርሷ ለንጹሃን እስረኞች ፍቺ መስጠት እምቢኝ እያላት እኛ ንጽህና ለተሳናት ገዢ ምን ፍቺ አሰጠን ብለን ለመቀለድም እንሞክራልን!)
ቀለም ማለት፤ እውቀት ትምህርት ንባብ እና የአዕምሮ ከፍታ ማለት ነው። (ከፈለግዎ መዘገበ ቃላት ያገላብጡ ወላ ከሳቴ ብርሃን ወላ ያሰኝዎን መዝገብ ይፈትሹ… በኔ ይሁንብዎ ወዳጄ ቀለም ማለት የሄው ነው ትርጉሙ!)
አብዮትንስ ምን ብለን እንፍታው… ያልን እንደሆን፤ አዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ያሳተመው የአማርኛ መዝገበ ቃላት፤ “አብዮት ፤በአንድ ነገር ክስተተ ወይም ሂደት ውስጥ ያሉ ቅራኔዎች ተካረው ከፍተኛ ደረጃ ላይ ሲደርሱ የሚፈጠር መሰረታዊ ለውጥ፤ አዲስ ከፍተኛ እና የተሻለ ነገር ክስተት እና ሂደት ወይም አስተሳስብ እና እውቀት የሚከሰትበት” ሲል ይተረጉመዋል።
እና እነዚህን ሁለት ነገሮች ብናቀናጃቸው የቀለም አብዮት ክፋቱ ምን ላይ ነው… ብለን መጠየቃችን አይቀርም።
የቀለም አብዮት ክፋቱ የአምባገነኖችን ዱላ ማበርታቱ….! ካልሆነ በስተቀረ ምንም ከፋት የለውም። ቀለምም እውቀት ነው፤ አብዮትም የተሻለ ለውጥ ነው። (ታድያ ነውጥ እንጂ ለውጥ ምን ጉዳት አለው…. መልሱ ምንም! የሚል ነው።)
ኢህሃዴግ ግን ቀለም ትፈራለች፤ አብዮትማ ጠላቷ ነው። (ሳስበው በአብዮት ጠባቂዎች የያዘችው ቂም ሰላልለቀቃት ነው፤ እዝችጋ የፈጀውን ይፍጅ ሳቅ አል…ሃሃ) ቀለም እና አብዮት ተቀላቀለው፤ የቀለም አብዮት ሲሆንባት ደግሞ ዶክመንተሪ ፊልም ሁላ ለመስራት እስኪያነሳሳት ድረስ የምትጠላው ነገር ነው።

Tuesday, April 29, 2014

ጆን ኬሪ በአዲስ አበባ – ኢህአዴግ አሁንም በሶማሊያ ያስፈራራ ይሆን?


ኢህአዴግ የዞን9 ጦማሪዎችን “አገር በማተራመስ” ወንጀል ከሰሰ

kerry 1
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆን ኬሪ የኢትዮጵያ ጉዞ በርካታ ጉዳዮች የሚከናወኑበት እንደሆነ ተጠቆመ። የዘወትር የጎልጉል ምንጭ አንዳሉት የኬሪ አዲስ አበባ ጉዞ አስቀድመው የተሰሩ ስራዎች ውጤት ነው። ጥቁሩ ሰው “ውሻ ምንም ሳይመለከት አይጮህም” ሲሉ አገር ቤት ያሉ ተቃዋሚዎች ራሳቸውን ብቃት ያላቸው አማራጮች መሆናቸውን እንዲያሳዩ ጠይቀዋል። ኢህአዴግ አሜሪካንንና የምዕራቡን ዓለም እንደለመደው “ከሶማሊያ ጦሬን አወጣለሁ” በማለት መደራደሪያ ከማቅረብ ውጪ ሌላ አቅም እንደሌለው ተገለጸ። ኢህአዴግ የዞን9 ጦማሪዎችና ጋዜጠኞች “አገር በማተራመስ” ወንጀል ክስ መሰረተባቸው።
የድረገጽና የማህበራዊ ገጽ የኢህአዴግ ደጋፊዎችና የስርዓቱ ተጠቃሚ አባላት ባይዋጥላቸውም አሜሪካና ኢህአዴግ የነበራቸው ግንኙነት እየሻከረ መሔዱን ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በተደጋጋሚ ሲገልጽ እንደነበር ይታወሳል። ጎልጉል የዋሽንግቶን ዲፕሎማት ምንጩን በመጥቀስ እንደዘገበው አሜሪካ ኢህአዴግን “የምስራቅ አፍሪካ ስጋት” አድርጋም ፈርጃለች። የኢትዮጵያን ጉዳይ የሚከታተለውና በስቴት ዲፓርትመንት ውስጥ የተቋቋመው የቀውስ መከላከልና ዕርቅ ቢሮ ሃላፊ ከጥር ወር ወዲህ ባሉት ጥቂት ወራት ውስጥ አራት ጊዜ አዲስ አበባ ተጉዘዋል።
ኢህአዴግ እየተከተለ ያለው ፍትሃዊነት የጎደለው አገዛዝ ኢትዮጵያን ወደ ቀውስ እንዳመራትና ይኸው ቀውስ እልባት ካልተበጀለት የምስራቅ አፍሪካን የሚያዳርስ እንደሚሆን በአሜሪካ በኩል አቋም መያዙ ኢህአዴግን እንዳስበረገገው ተንታኞች እየገለጹ ነው። የምስራቅ አፍሪካ “የሰላም አባት ነኝ የሚለው ኢህአዴግ በውስጣዊ የፖለቲካ ቀውስ ስለሚገኝ የመወላለቅ ችግር ሳይገጠመው በፊት አሜሪካ አስቀድማ ስራዋን መስራት መጀመሯ ከራሷ ጥቅም አንጻር ነው” ሲሉ ዲፕሎማቱ እንደቀድሞው ሁሉ ሳይሸሽጉ ተናግረዋል። የኬሪ ጉዞም የዚሁ አካል እንደሆነ አስታውዋል። “ኢህአዴግ” አሉ ዲፕሎማቱ “የቀለም አብዮት እያለ እንደሚደነፋው ሳይሆን በመጪው ምርጫ በሩን ከፍቶ ለመወዳደር ከተስማማ ብቻ የለመደው ርጥባን ይሰጠዋል የሚል ግምት አለኝ” ብለዋል።
በ97 ምርጫ ወቅት እንዳደረገው በሶማሊያ ያለውን አለመረጋጋት እንደ ማስፈራሪያ በመጠቀም ጦሩን የማስወጣት ርምጃ ቢወስድስ? በሚል ለተጠየቁት “ኢህአዴግ የመጫወቻ ካርዶቹ ያለቁበት ይመስለኛል” በማለት የግሌ ያሉትን አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። ኢህአዴግ በምርጫ 97 ተደራደር ሲባል ጦሩን ሰብስቦ ለመውጣት በዝግጅት ላይ እንደሆነ መግለጹን የተለያዩ የውጪ አገር ሚዲያዎች መዘገባቸው አይዘነጋም።
obang-o-metho-hearingየአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) ዋና ዳይሬክተር ኦባንግ ሜቶ /ጥቁሩ ሰው/ “ውሻ ከጮኸ የሆነ ነገር አለ ማለት ነው” ሲሉ ለጎልጉል አስተያየት ሰጥተዋል። ኦባንግ አገር ቤት የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች ይህንን ጩኸት ሰምተው ህዝብን በማስቀደም ራሳቸውን አማራጭ አድርገው እንዲያሳዩ ጥሪ አቅርበዋል። አማራጭ የለም የሚለውን ፍርሃቻ በመስበር ወቅቱን ለህዝብና ለአገር ጥቅም ለማዋል እንዲተጉ አሳስበዋል። የሚመሩት ድርጅት በቅርቡ በዚህ ዙሪያ የሚለው ነገር ስላለ ዝርዝር ጉዳይ ውስጥ ከመግባት ተቆጥበዋል።
የአሜሪካ የውጪ ጉዳይ መስሪያ ቤትን በመጥቀስ የጀርመን ድምጽ እንደዘገበው ኬሪ፤ ሃይለማርያም ደሳለኝን፣ ቴድሮስ አድሃኖምንና የሚመለከታቸውን ባለስልጣናት በሰብአዊ መብት አያያዝና በዲሞክራሲ ትግበራ ዙሪያ እንደሚያነጋግሩ ማረጋገጫ መሰጠቱን ጠቁሟል። በዚሁ ዜና ላይ ቃላቸውን እንዲሰጡ የተጠየቁት አቶ ጌታቸው ረዳ ኬሪ ከሌሎች የፖለቲካ ድርጅት አመራሮች ጋር ይነጋገራሉ የሚል ስጋት እንዳለባቸው የሚያሳብቅ መልስ ሰጥተዋል። ኬሪ የዞን9 ድረገጽና ማህበራዊ ድር ጦማሪዎች እስርን አስመልክቶ የተጠየቁት አቶ ጌታቸው ረዳ ጆን ኬሪ ስለ ዞን9 አባላት እስር ሊያነሱ እንደሚችሉ ተጠይቀው “እንደምናከብረው መሪ ጥያቄውን ካቀረቡ አስፈላጊውን መልስ እንሰጣለን” ካሉ በኋላ “የዞን9 ጦማሪዎች በጋዜጠኛነታቸው አልታሰሩም” በማለት ከገጀራና ከስርቆት ወንጀል ጋር በማዛመድ ለማቃለል ሞክረዋል።

Monday, April 28, 2014

ዜጎች በጎጃም መሬቸውን እየተነጠቁ፤ በወለጋ ደግሞ እየተፈናቀሉ ነው!



map

አርሶ አደሮች መሬታቸውን ያለካሳ እየተነጠቁ ነው

መራዊ፡- በምዕራብ ጎጃም ዞን ሜጫ ወረዳ ያለ ፈቃዳችን መሬታቸውን አሳልፈን አንሰጥም ያሉ አርሶ አደሮች እስርና ድብደባ እየደረሰባቸው መሆኑን ከአካባቢው የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡ በመራዊ አካባቢ ሜጫ ወረዳ እናሸንፋለን ቀበሌ መንግስት የከርሰ ምድር ውሃ ቁፋሮ እናካሂዳለን በሚል ከ400 በላይ የሚሆኑ አርሶ አደሮች ከመሬታቸው እንዲለቁ የተደረገውን እርምጃ አርሶ አደሮቹ በመቃወማቸው እስርና ድብደባ እየደረሰባቸው መሆኑን የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ጠቁመዋል፡፡
በአካባቢው ከአሁን ቀደም ተመሳሳይ እርምጃዎች የተወሰዱ ሲሆን የአርሶ አደሮቹ መሬት በአበባ ኢንቨስትመንት ላይ ለተሰማሩ ባለሀብቶች ተሰጥቶባቸዋል፡፡ ይህም በአሁኑ ወቅት መንግስት ውሃ ለመቆፈር በሚል አርሶ አደሮቹ ከመሬታቸው እንዲለቁ የሚወስደው እርምጃ በተመሳሳይ ለአበባ እርሻ ሊሰጥባቸው እንደሆነ በማመናቸው ከመሬታቸው አንለቅም ብለዋል፡፡ እስካሁን ለአበባም ሆነ ለሌሎች ተግባራት መንግስት ከአርሶ አደሮቹ መሬት ሲወስድ ያለ ምንም ካሳ በመሆኑ አርሶ አደሮቹ አሁንም ቢሆን ያለ ካሳና ያለምንም ፈቃድ እየተነጠቁ በመሆኑ ተቃውሟቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ አድርጓዋል፡፡
ከአርሶ አደሮች ባሻገር በከተሞች የሚኖሩ የአርሶ አደሮቹ ቤተሰቦች ጭምርም ችግር እየደረሰባቸው መሆኑን ምንጮች ጨምረው ተናግረዋል፡፡ በተለይም ታሳሪዎቹን የሚጠይቁት የአርሶ አደሮቹ ቤተሰቦችና ሌሎች የአካባቢውና በየከተማው የሚኖሩ ግለሰቦችም ለእስር መዳረጋቸውን ለመረዳት ተችሏል፡፡ አርሶ አደሮቹ መሬታቸውን ያለ ፈቃዳቸው አሳልፈው እንደማይሰጡ በመግለጽ ጠንካራ ተቃውሞ ማንሳታቸውን ተከትሎ በአካባቢው ፖሊስና መከላከያ በብዛት መሰራጨቱን ምንጮች አክለው ገልጸዋል፡፡

Saturday, April 26, 2014

የ“ህዳሴው” ግድብ ተጽዕኖ ሌላ አቅጣጫ መያዙ አሳሳቢ ሆኗል


የአቡነ ማቲያስ የግብጽ ጉብኝት ላልተወሰነ ጊዜ ተላልፏል

abay and church
ሃያ አምስት በመቶ እንደተጠናቀቀ የሚነገርለት የ“ህዳሴው” ግድብ በኢትዮያና በግብጽ መካከል ከፈጠረው የፖለቲካ ቁርቋሶ በተጨማሪ ወደ ሃይማኖት መንደርም እየዘለቀ ነው፡፡ ዛሬ (አርብ) ግብጽን ለመጎብኘት ቀጠሮ ተይዞላቸው የነበሩት አቡነ ማቲያስ ከግብጽ በኩል እንዳይመጡ በተላለፈላቸው መልዕክት መሠረት ጉብኝታቸውን ላልተወሰነ ጊዜ አስተላልፈውታል፡፡
በግብጽና በመካከለኛው ምስራቅ የሚገኙ የተለያዩ የዜና ዘጋቢዎች እንዳሉት ከሆነ መልዕክቱ ያስተላለፉት የግብጹ ፓትሪያርክ አቡነ ታዋድሮስ ዳግማዊ ናቸው፡፡ ፓትሪያርኩ ለአቡነ ማቲያስ ባስተላለፉት መልዕክት በበርካታ ቢሊዮን ዶላር የሚገነባው የአባይ ግድብ የፈጠረው ሁኔታ እንዳለ ሆኖ ይህንን ጉብኝት ማካሄድ የግብጽን ቤ/ክ “የሚያሳፍር” ይሆናል በሚል ነው ምክራቸውን ለአቡነ ማቲያስ የለገሱት፡፡
ስማቸውን ሳይጠቅሱ መረጃውን ለግብጽ የሚዲያ አካላት የተናገሩት ባለሥልጣን እንደሚሉት ከሆነ ሁለቱ ቤ/ክናት ለረጅም ጊዜ የቆየ ግንኙነት ቢኖራቸውም ግድቡን በተመለከተ ይፋዊ ያልሆነ ሽምግልና የማካሄዳቸው ሁኔታ የማያዛልቅ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ ሁለቱ ከፍተኛ የቤ/ክ መሪዎች በሚገናኙበት ወቅት ይህ ጉዳይ ሳይነሳ እንደማይታለፍ የታወቀ ነው፡፡

Thursday, April 24, 2014

ባርያ ነጻ የሚወጣው መቼ ነው? እሱ ሲፈቅድ ነው? ወይስ ጌታው ሲፈቀድለት?


ክፍል አንድና ሁለት ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም

freedom

አንድ

በአለፈው ሳምንት (ፋክት ቁጥር 36) ወይዘሮ መስከረም የተለያዩ መጻሕፍትን በመጥቀስ በሴቶች ላይ ያለውን መጥፎ ጫና በደንብ ያስመሰከረች ይመስለኛል፤ ግን እኮ በሴቶች ላይ ያለው ጫና የቆየ፣ ክፉና ጎጂ መሆኑን ማንም ያውቀዋል፤ ቁም-ነገሩ ያለው ከዚያ የባህል ጭነት በራስ ጥረት ወጥቶ፣ ነቀፌታንም ሆነ እርማትን ለመቀበል ሳይፈሩና ሳያፍሩ እንደመስከረም በአደባባይ ሀሳብን በመግለጽ በአገርና በወገን ጉዳይ መሳተፍና ሌሎችም እንዲሳተፉ የተቻለን ሁሉ ማድረጉ ላይ ነው፤ ለዚህ ነው ይህንን መልስ የምጽፈው፤ ወይዘሮ መስከረም በአጋጠሟትና በምታያቸው እንቅፋቶች ላይ ማተኮርዋ እንደርስዋ መንፈሳዊ ወኔው የሌላቸውን ያስፈራራቸዋል እንጂ አያበረታታቸውም፤ የማንንም አፍአዊ ጫና ተቋቁመው በራሳቸው የውስጥ ኃይል እንዲመሩ እናድርግ።
አንድ መጽሐፍን በመጥቀስ ወይዘሮ መስከረም የሚከተለውን ጽፋለች፡–
ፈጣሪ የሠራውን  ውጫዊ  ገጽታን ማሽሞንሞን በቂ እንደሆነ ሲነገራት የኖረች ሴት፣ በምን ተነሳሺነት አእምሮዋን የሚመግብ  እውቀት ልትሻ ትችላለች? … በልጅነት እውቀትን  ወደመሻት ያልተገፋ ማንነት በጉብዝና ወራት አላዋቂ በመሆን ቢወቀስ ትርጉም አይኖረውም፤ … ››
ወይዘሮ መስከረም ሔዋን ሲነገራት የማትሰማ የመጀመሪያዋ ሰው (ልብ በሉ ሴት አላልሁም፤) መሆንዋን እንዴት እስከዛሬ ሳታውቅ ቀረች? ባለመጽሐፉም ይሁን መስከረም የሔዋንን ታሪክ ሳያነሡ መቅረታቸው መሠረታዊ ስሕተት ነው፤ በተጠቀሱት ሁለት ዓረፍተ ነገሮች ውስጥ አንድም እውነትን የሚመስል ነገር የለም፤ መስከረም ‹‹የሔዋን ዘር›› ከማለት በፊት የሔዋንን ሥራ ቆም ብላ ብታስታውስ የጠቀሰችውን መጽሐፍ እኔ እንደምነቅፈው ትነቅፈው ነበር፤ የሔዋን ታሪክ የሚነግረን የሚከተለውን ነው፡ ‹‹ዛፉ ለመብላት ያማረ እንደሆነ ለዓይንም እንደሚያስጎመጅ፣ ለጥበብም  መልካም እንደሆነ አየች፤ ከፍሬውም ወሰደችና በላች፤ ለባልዋም ደግሞ ሰጠችው፤ እርሱም ከእርስዋ ጋር በላ፤ የሁለቱም ዓይኖች ተከፈቱ፤›› ዘፍ. 3

Saturday, April 19, 2014

የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎቹ ‘ሮሮና ስጋት


“ምላሽ ካልተሰጠን የትምህርት ማቆምና ሰላማዊ ሰልፍ እናደርጋለን!”

addis ababa university
የትምህርት ሚኒስትር በ2006 ዓ.ም በአገሪቱ በተፈጠረው የመምህራን እጥረት ምክንያት በተለ ያዩ የትምህርት ዘርፎች የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ያገኙ ኢትዮጵያውያንን ለአንድ አመት ሙሉ ወጫቸውን ችሎ የማስተማር ስነ ዘዴ (ፔዳጎጅ) በማስተማር ወደ መምህርነት እንዲገቡ ማስታ ወቂያ ያወጣል፡፡ በወጣው ማስታወቂያ መሰረ ትም ለማጣሪያነት የቀረበውን ፈተና በመፈተን መልምሎ ለስልጠና እንዲገቡ ይደረጋል፡፡ በዚህ መሰረት በ10 ዩኒቨርሲቲዎች (መቀሌ፣ ባህር ዳር፣ ወሎ፣ ወለጋ፣ ጅማ፣ ወላይታ ሶዶ፣ ዲላ፣ ሀሮማያ፣ ሀዋሳና አዲስ አበባ) እንዲሰለጥኑ ይደረጋል፡፡
ይህ ስልጠና እየተካሄደ ባለበት ወቅት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የተመደቡት ሙሉ ወጫቸ ውን መንግስት እንደሚችል ተነግሯቸው ነበር የመጡት፡፡ በዩኒቨርሲቲው መጀመሪያ የተደለ ደሉት 330 ነበሩ፡፡ ሆኖም ግን ተማሪዎቹ ቃል በተገባላቸው መሰረት መቀጠል አለመቻላቸውን ነው በቅሬታ የሚናገሩት፡፡ ወደ ዝግጅት ክፍላችን በአካል መጥተው ስለሁኔታው ያስረዱት ተማሪዎች ሁኔታውን እንደሚከተለው ያስረዳሉ፡፡ ‹‹ማስታወቂያውን አይተን ስራችን ለቀን ነው የመጣነው፡፡ ሆኖም አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርት ሚኒስትር ቃል በገባው መሰረት ከህዳር 23 ጀምሮ የምግብም ሆነ የቤት አገልግሎት ሊሰጠን አልቻለም፡፡ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመኝታ አገልግሎት የለም በመባሉ ደብረዘይት በሚገኘው የዩኒቨርሲቲው ቅርንጫፍ የእንሰሳት ህክምና እና የግብርና ኮሌጅ ለሁለት ሳምንት እንድንቆይ ተደረገ፡፡ ሆኖም ደብረ ዘይት በሚገኘው ኮሌጅ ጥቁር ሰሌዳን ጨምሮ ለመማር ማስተማር የሚያገለግሉ አቅርቦቶች ልናገኝ አልቻልንም፡፡››
ከዚህም ባሻገር በዚህ ወቅት ተማሪዎቹ የመብት ጥያቄ እንዲያነሱ ያደረጋቸው ሌላ ምክንያትም ተፈጠረ፡፡ ‹‹ትምህርቱ በተባለው መልኩ ሊሰጠን አልቻለም፡፡ አንድ መምህር ወደ ደብረዘይት ሄዶ የሳምንቱን የትምህርት ፕሮግራም ከጠዋቱ 2 ሰዓት እስከ 6 ሰዓት እንዲሁም ከ7 ሰዓት ተኩል እስከ 11 ሰዓት ተኩል አስተምሮ ይሄዳል፡፡ ይህን ተከትሎም አንዳንድ የመብት ጥያቄዎችን ማንሳት ጀመርን፡፡›› ይላል አስተባባሪውና የጅኦግራፊ ተማሪው ጋሻነህ ላቀ፡፡