Friday, November 9, 2012

እነ አቶ አንዱለም አራጌ ዛሬ ፍርድ ቤት ቀረቡ




ጥቅምት ፴ (ሰላሳ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-በሽብርተንነት ወንጀል ተከከሰው ብግፍ እስር ላይ የሚገኙት የአንድነት ፓርቲ ም/ሊቀመንበርና የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ አቶ አንዱአለም አራጌ፣ ሌላው የአመራር አባል አቶ ናትናኤል መኮንን እንዲሁም የመኢዴፓ የአመራር አባል የሆነው አቶ ክንፈ ሚካኤል ደበበ የይግባኝ አቡቱታቸውን ለማቅርብ ፍርድ ቤት ቢቀርቡም ዳኞቹ ለህዳር 13 ቀን 2005 ዓም ቀጠሮ በመስጠት ችሎቱን አሰናብተዋል።
የፍርድ ሂደቱን በተመለከተ ችሎቱን የተከታተሉትን አንድነት ፓርቲ ሊቀመንበርና የቀድሞው የኢትዮጵአ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ የእስረኞች መንፈስ ጠንካራ እንደነበር ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ መንግስት በግፍ ያሰራቸውን የፖለቲካ እስረኞች እንዲፈታ በአለማቀፍ የሰብአዊ መብት ድርጅቶች እና መንግስታት ቢጠየቅም እስካሁንም አሻፈረን እንዳለ ነው።

Thursday, November 8, 2012

ኢህአዴግ ስንት ቦታ ሊሰነጠቅ ይችላል?


(ከተመስገን ደሳለኝ)

ብርዱ የጥቅምት ነው፤ አጥንት ድረስ ዘልቆ የሚያንቀጠቅጥ ኃይለኛ ቅዝቃዜ፡፡ አዲስ አበባ ገና ከእንቅልፏ በመንቃት ላይ ነች፡፡ ለስራ የቸኮሉ መንገደኞች ትራንስፖርት ፍለጋ ወዲያ ወዲህ ይካለባሉ፡፡ ማክሰኞ ጥቅምት 7 ቀን 2005 ዓ.ም. ከጠዋቱ 12 ሰዓት ከ50 ደቂቃ ላይ ብስራተ ገብርኤል አደባባይ ‹‹መገናኛ ራዲዮ›› በያዙ የትራፊክ ፖሊስ አባላት በቁጥጥር ስር ዋለ፡፡ የትራፊክ ፖሊሶቹ ስራ የበዛባቸው ይመስላሉ፡፡ 12 ሰዓት ከ55 ደቂቃ ሲል በሁለት የሞተር ብስክሌት በተፈናጠጡ የትራፊክ ፖሊሶች ፊት አውራሪነት አንዲት ሳይረን የተገጠመላት የፖሊስ ታርጋ የለጠፈች መኪና የ‹‹መንገድ ልቀቁልኝ›› ጩኸቷን እያንባረቀች አቋርጣ በማለፍ ወደ ሳር ቤት አቅጣጫ ከነፈች፡፡ ሶስት ‹‹ቪኤት›› መኪና ሰለሱ፡፡ ሌላ ባለሳይረን መኪናም ከኋላ እየተከተለች ነው፡፡ ሁሉም መኪኖች በከባድ ፍጥነት ነው የሚበሩት፡፡ ሳር ቤት ያለው የፑሽኪን አደባባይም ተመሳሳይ ቁጥር ባላቸው የትራፊክ ፖሊሶች ተጨናንቋል፡፡ ሜክሲኮ አደባባይ፣ አምባሳደር፣ ፍልውሃ፣ ገብርኤል መሳለሚያ… ቤተ-መንግስቱ የአጀቡ መድረሻ ቦታ ነው፡፡
አጀቡ አዲሱን ጠቅላይ ሚኒስትር ኃ/ማርያም ደሳለኝን ከመኖሪያ ቤታቸው ወደ ስራ ቦታቸው ለማድረስ ነው፡፡ ይኸው ትዕይንት ከምሽቱ ሶስት ሰዓት ላይ ይደገማል፡፡ ቅደም ተከተሉ ተገልብጦ፤ ከቤተ-መንግስት… ብስራተ ገብርኤል፤ የአደጋ ማስጠንቀቂያ ድምጽ፡፡

Wednesday, November 7, 2012

ዜና ፎቶ፤ ትላንት ቃሊቲ ይሄንን ትመስል ነበር




በቃሊቲ ማሰሪያ ቤት እነርሱ “ማረሚያ ቤት” ይሉታል። በርካታ ወገኖቻችን እንደሚገኙ ይታወቃል። በቅርቡ ደግሞ የሙስሊም ኢትዮጵያውያን መፍትሄ አፈላላጊዎች ወደ ቃሊቲ ተዛውረዋል። ይህ ፎቶ ህብረተሰቡ ከታሳሪዎቹ ጎን መሆኑን ያሳያል። “አያሳይም” የሚል ካለ በደንብ ደግሞ ይመልከተው!  ፎቶውን ብቻ ሳይሆን የታሰሩበትንም ምክንያት በደንብ ብንመለከት ደግሞ ሁላችንም ከነዚህ ወገኖች ጎን  መቆማችን አይቀሬ ነው!
በመጨረሻም
እንመርቃለን…
እግዜር ያለ አሳሪዎችን “ሃይ…!” ይበልልን ታሳሪዎችን ያበርታልን!

Tuesday, November 6, 2012

ማን ጸሎት ያሳርግ


(ለምለም ጸጋው)



“በቃሊቲ ማሰሪያ ቤት እነርሱ “ማረሚያ ቤት” ይሉታል። በርካታ ወገኖቻችን እንደሚገኙ
ይታወቃል። በቅርቡ ደግሞ የሙስሊም ኢትዮጵያውያን መፍትሄ አፈላላጊዎች ወደ ቃሊቲ
ተዛውረዋል። ይህ ፎቶ ህብረተሰቡ ከታሳሪዎቹ ጎን መሆኑን ያሳያል። “አያሳይም” የሚል ካለ
በደንብ ደግሞ ይመልከተው!  ፎቶውን ብቻ ሳይሆን የታሰሩበትንም ምክንያት በደንብ
ብንመለከት ደግሞ ሁላችንም ከነዚህ ወገኖች ጎን መቆማችን አይቀሬ ነው!”November 
5th, 2012”  (http://www.ethiopianreview.net/index/?p=47899)

ማን  ጸሎት ያሳርግ 

ወይ ነውር አይገዛው
አምልኮት ዓልነካው፤
የእትዮጵያን ሰው ሁሉ
በቃሊቲ አጎረው።
ይድነቃችሁ ብሎ
በየሱስ ስም ማለ፤የመለስን ወንጌል
እንደ ክታብ እርጎ
በአንገቱ ሰቀለ።
ለሁሉም ለመሆን
አዲሱ ምንስቴር በቃሊቲ ሳይቀር፤
አርብ ሰኞ ሳይል
አለ ዓላህ አክብር።
ምነው የኔ ወዳጅ
ጓዴ የጴንጤ አማኝ
አያቴ ኦርቶዶክስ
የሚያምኑ በየሱስ
የዓባቴ ወገኖች
አሉ ብዙ እስላሞች
በክርስትና መልክ እስኪ ልጠይቅህ
በቃሊቲ ቦታ ቁርስ ምሳ ሲቀርብ
ማን  ጸሎት ያሳርግ
ብለህ ታውጃለህ
ዐረ ባላህ በሉ ወይንም በየሱስ
እስከመቸ ድረስ
እንዲህ እንታመስ
አዳምጠኝ ይልቅስ ወሪውን ልንገርህ
ብቻውን አልቅሷል ዖሮሞው አባትህ
ለአማራዋ እናትህ
ተው እንጅ ዓትቀልድ ምነው ምኑ ነካህ
ከለቅሶው ያልደረስህ
አሁን ገና ገባኝ አላህን ፈርቶ ነው
ሰላም በማወጅህ
ዐረ ባላህ በሉ ወይንም በየሱስ
እስከመቸ ድረስ
እንዲህ እንታመስ
© ለምለም  ጸጋው በስልምና ሃይማኖትም ሆነ መብታቸውን ለማስጠበቅ በመናገራቸው በእስር ቤት
ለሚማቅቁ ሁሉ (http://www.ethiomedia.com/assert/4785.html) 

ትውልደ ኢትዮጵያዊያን አሜሪካውያን በ2012 ምርጫ መሳተፍ ይገባቸዋል

ከፕሮፌሰር  ዓለማየሁ  ገብረማርያም
ትርጉም  ከነጻነት ለሃገሬ
ጉዳዩ የምርጫ  ብቻ አይደለም እኮ
ባለፈው ሴብቴምበር ስለ ፕሬዜዳንት ባራክ ኦባማ ድጋሚ መመረጥ ድጋፌን ገልጬ ነበር፡፡ ለታዳሚዎቼ  እንዳስነበብኩት በ2008 ምርጫ ተወዳዳሪ ባራክ ኦባማን ደግፌ እንደነበርና
Ethiopian Americans your vote counts vote on November 6 2012
ከምርጫው በኋላ ግን በታየው በተለይም ኢትዮጵያንና  አፍሪካን በተመለከተ  ስለተካሄደው አስተዳደራዊ ፖሊሲ ግን በጣሙን ቅሬታ አድሮብኛል፡፡ እንደትጠቀስኩት:-
ፕሬዜዳንት ኦባማ በአፍሪካ ውስጥ ተግባራዊ አደርጋለሁ ያሉትን መልካም አስተዳደርን፤የሰብአዊ መብትን መከበር፤የዴሚክራሲን ተግባራዊነት በተመለከተ ቃላቸውን ጠብቀዋል?  በኢትዮጵያ ውስጥ ስላለው የሰብአዊ መብት ገፈፋና ረገጣ ያሉትን አድርገዋል? በጭራሽ! ኢትዮ አሜሪካውያንስ ፕሬዜዳንቱ በአክራ (ጋና) የገቡትን ቃል ስላልጠበቁና የሰነዘሩትን የተስፋ ቃል ባለማክበራቸው ቅር ተሰኝተዋል? አስተዳደራቸውስ በኢትዮጵያ በጉልበት ስልጣን ለያዘው ፈላጭ ቆራጩ ዲክታተራዊ ገዢ ድጋፍ ማድረጋቸውስ ኢትዮ አሜሪካውያንን አሳዝኗል? አዎን በሚገባ እንጂ!
ፕሬዜዳንት ኦባማ ‹‹በአፍሪካ ጠንካራ የሆነ የዴሞክራቲክ ስርአት፤ት የሕግ የበላይ ነት የሚከበርበት፤ለፖለቲካዊ እንቅስቃሴ አድሎ የሌለበትና ሁሉም በእኩል የሚስተናገዱበት መድረክና ሰብአዊ መብትም በእውነተኛ መልኩ የሚተበርበት ኢኒስትቲዩሽን መፍጠር አስፈላጊ ነው›› ማለታቸውን እናስታውሳለን፡፡ ከዚህ ባሻገርም ‹‹አፍሪካ ጡንተኞች አየስፈልጓትም፤ በጉልበት ስልጣን ላይ በመንጠላጠል ማስተዳደርን ወደ መግዛት መለወጥ ባህሪያቸው የሆኑ ሰዎችም አያስፈልጓትም፤ የሚያስፈልጓት ጠንካራ የሆኑ ተቋሞች ነው፡፡›› ልማት ምንግዜም በመልካም አስተዳደር ላይ የተመሰረተ ነው፡፡ ማንም ሃገር መሪ ነን ብለው ስልጣን የተቀመጡት የሕዝቡን ካዝና የሚበዘብዙት ከሆነ ሕዝቡ በምንም መልኩ ሃብት ሊያፈራ ንብረት ሊኖረው አይችልም::  ታዲያ ፕሬዜዳንት ኦባማ እነዚህን አጓጊና የኢትዮጵያ የሌለችም አፍሪካዊያን ናፍቆት የሆኑትን ቃላት ሲናገሯቸው አምነውባቸው ከልባቸው ነው ወይስ ለማለት ብቻ ነው የተነፈሱት?

Friday, November 2, 2012

November “Ethiopian Election Massacre” Commemoration Month



On May 15, 2005, over 26 million Ethiopians voted peacefully to elect their leaders. As the results started to come in, showing a landslide victory for the opposition party, Meles Zenawi went on TV and declared a state of emergency. He also ordered re-votes in several districts where members of his party went down in defeat, banned political rallies, and unleashed his killers against peaceful citizens who protested his attempt to steal the election.

When the Addis Ababa Police showed restraint, Meles ordered all of them to be disarmed, and gave the Federal Police and his personal army, the Agazi, a shoot-to-kill order.
The Agazi and Federal Police snipers from roof tops and military trucks gunned down young, hundreds of unarmed protesters with 50 caliber rifles. Over 50,000 students and other individuals were rounded up and sent to concentration camps in remote parts of the country. All senior members of the opposition CUD were arrested. All the private press were shut down. The 2005 election massacre was one of the darkest moments in the history of Ethiopia.

ከጠ/ሚኒስቴር መለስ ምኑን እንውረስ?



ጠቅላይ ሚኒስቴር መለስ መሞታቸው ሁሉም ሰው ያሳዘነ ጉዳይ ነው፡፡ ለምን ከተባለ ሁሉም ሰው ከመሞት የሚያመልጥ ባይኖርም
የአሟሟታቸው ሁኔታ ግን ለየት ባለ ሁኔታ ስለተፈፀመ በጣም ያሳዝናል፡፡ መጀመሪያ በሪፖርተር ጋዜጣ አንድ የመንግሥት ቃለ-አቀባይ መነሻ በሌለው ሁኔታ ጠቅላይ ሚኒስቴር መለስ የጤና ችግር የለባቸውም የሚል መግለጫ ሰጠ፡፡ ሰዉየው ይህ ያሉበት ምክንያት ምንድነው? ስለጤናቸው ምን ተብሎ እና ነው ይህን መግለጫ የሰጡ ማለት ጀመረ፡፡ በስተጀርባ አንድ ነገር እንዳለ ጥርጣሬ ውስጥ ገባ፡፡ ቆየት ብለው ጠቅላይ ሚኒስቴር መለስ ታመው ህክምና እንደገቡና ህመሙም የሚያሰጋ እንዳልሆነ መግለጫ ተሰጠ፡፡ ቆየት ብለውም በተለይ አቶ በረከት ስምዖን በዕረፍት ላይ መሆናቸው በቅርብ ግዜ ሥራቸው እንደሚጀምሩ መግለጫ ሰጡ፡፡

ይህ ሁላ ሲሆን ግን አንድ ደ/ር እንኳ ስለየጤንነታቸው ጉዳይ መግለጫ የሰጠ አልነበረም፡፡ ይህ ህዝቡ በበለጠ ጥርጣሬ ውስጥ
ከተተው፡፡ የታመመ ሰው ስለህመሙ የሚያቅና ሁኔታውን ማብራራት የሚችል ሃኪም ነው ስለ ጠቅላይ ሚኒስቴር የጤንነት ጉዳይ
የሚነገረን ያለ በመንግሥት ሥልጣን ባሉ ሰዎች ነው ይህንን ነገር እንዴት ነው በማለት ራሱ በራሱ መወያየት ጀመረ፡፡ የሃኪም
መግለጫ ሳይሰማ ዜና ዕረፍታቸው ተሰማ፡፡ መሞታቸው በጣም አሳዝኖናል፡፡ የጠቅላይ ሚኒስቴር መለስ ባህሪያት ለተነሱለት ዓላማ በፅናት የሚተገብሩ ሰው ነበሩ፡፡ የሆነ ሐሳብ አቅርበው ተቀባይነት ካላገኘ ሞተው ይገኛሉ፡፡ በሐሳባቸውና
በአመለካከታቸው የሚነሱ ልዩነቶች ፍፁም አያስተናግዱም፡፡ ለማስተናገድ ቢሞኩሩም የትም አይደርስም ብለው የገመቱት እንደሆነ ብቻ ነው፡፡ በዓቅም የሚቀናቀናቸው ሰው አይወዱም፡፡ ብዙ አብነቶች ማቅረብ ይቻላል፡፡ አቶ አርከበ ዕቁባይ አቶ መለስ እንደሚጠሩዋቸው “ጅብ”  ናቸው፡፡ ጅብነታቸው በሥራ ነው፡፡ የትግራይ ም/ፕሬሲዳንት በነበሩበት ጊዜ አንዳንድ መሰረታዊ ለውጥ ለማምጣት ሲሞኩሩ አዲስ አበባ ወስደው የአዲስ አበባ ከንቲባ ሁነው እንዲሾሙ አደረጉ፡፡ በዚ ጊዜ በተለይ በነጋዴው የአገልግሎት አሰጣጥ ለውጥ ሲያስመዘግቡ ቀለም ከመቀባት የማያልፍ ሥራ ነው የሠራኸው ብለው መዓት ወረዱባቸው፡፡ ከዛ በኋላ የማዕድንና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስቴር ድኤታ ሁነው እንዲሠሩ ተደረገ፡፡ ከዛ በማንሳት ደግሞ አማካሪ ብለው ሰው በማያያቸው (አቅማቸው ህዝቡ በማያየው ዋሻ) እንዲገቡ አደረጉ፡፡ይህ ሁሉ መነሻው ስጋት ነው፡፡ አቶ አርከባ በግልፅ መቃወም አልደፈሩም እንጂ ውስጣቸው ከኛ በላይ የአቶ መለስ በላያቸው ላይ ያደረጉት ዘመቻ ያውቁታል፡፡ በዚህ ቅሬታ ነበር በህወሐት ማእከላዊ ኮሚቴ ለፖሊት ቢሮ ምርጫ አልፈልግም ብለው ራሳቸው ያገለሉት፡፡

አቶ መለስ በተለይ “ከተሃድሶ” በኋላ እሳቸው እንደአስተማሪ የቀረው ማእከላዊ ኮሚቴ የህወሐት/ኢህአዴግ እንደተማሪ ወንበር ላይ ቁጭ ብሎ የሚማርበት ሁኔታ ነው የነበረ፡፡ የዚህ ጉዳት በጣም ብዙ ነው፡፡ አቶ መለስ ብቁ ሰው ማፍራት አልቻሉም፡፡ በተለይ በትግራይ፡፡ ወጣቱ ትውልድ ሥልጣን ላይ እንዲወጣ አይፈለግም ለምን አይታመንማ፡፡ ነባሩ ታጋይ ደግሞ እሳቸውን በዓቅም የሚወዳደር አጥላልተው ሞራሉ እንዲነካ ያደርጉታል፡፡ እነ አባይ ፀሃዬ፣ሥዩም መስፍንና አርከበ ዕቁባይ የዚህ አብነቶች ናቸው፡፡
አቶ መለስ ስልጣን ሙሉ በሙሉ ሳይቆጣጠሩ ጊዜ ያሳዩት የነበረ በህሪ ብዙም አይስተዋልም ነበር፡፡ የድርጅቱ ከፍተኛ አመራሮች
ለነበሩ ሰዎች የሚያሳዩትን ስህተቶች ማረም፣ ለህዝብ ተብሎ ሐቅም ቢሆን ህዝቡ ካልተቀበለው ድርጅቱ ተቀብሎ ተግባራዊ ማድረግ ይጠበቅብናል ሲሉ ይስተዋሉ ነበር፡፡ ስልጣን ሙሉ በሙሉ በተቆጣጠሩበት ጊዜ ጀምሮ ግን አንድ ቀንም ህዝቡን ያነሳው ጥያቄ ወይም አንፈልገውም ያለውን ነገር ተቀብለው አያውቁም፡፡ ለምሳሌ፡ የሊዝ አዋጅ መጥቀስ ይቻላል፡፡ ህዝብ ሲቃወም የተቃዋሚ ድርጅቶች ሐሳብ ነው ተብሎ ይፈረጃል፡፡ ያነሳ ሰውም እንዲሁ፡፡ ለስልጣን ብለው ዲሞክራሲ ያፍናሉ፡፡ እስከአሁን የተካሄዱ ምርጫዎች ህያው አብነቶች ናቸው፡፡ የተካሄዱ ምርጫዎች ሁሉም በማጭበርበር እንጂ ህዝቡ በነጻነት ያካሄደው ምርጫ አይደለም፡፡ ህዝቡ የፈለገው ፖለቲካዊ ፓርቲ መርጧል ማለት ፍፁም አይቻልም፡፡እርግጥ ነው በ1997 ዓ.ም ዲሞክራሲ ባልገመቱት ሁኔታ ህዝቡ ተነሳስቶ እነሱን ገፍትሮ የመሰለውን የፖለቲካ ፓርቲ መምረጥ በቅቶ ነበር፡፡ በተለይ የአዲስ አበባ ህዝብ በድፍን ቅንጅትን መርጦ ነበር፡፡ ቅንጅት መከራን ተቀብሎ ህዝብን ለማገልገል ስላልተነሳ የህዝብን ድምጽ መንገድ ላይ ጥሎት ሄደ፡፡ የዚሁ ጠባሳ አሁን የምናየው ያለን ዓይነት ምርጫ እንድናስተናግድ ተገደናል፡፡ ይህም ሆኖ ቅንጅት ሥልጣን ይይዛል ከሚል ፍራቻ ምርጫው ከተካሄደ በነገታው አዲስ አበባ ለኦሮምያ ክልል ተሰጥታለች ብሎ በፓርላማ እንዲታወጅ አገረጉ አቶ መለስ፡፡ ይህ የልጆች ጨዋታ ግን ደግሞ ይቅር የማይባል የታሪክ ስህተት ለምን ተደረገ ብለን ካልን የቅንጅትን ዓቅም ለማዳከም ተብሎ ነበር፡፡ ለዚህ ነው አቶ መለስ ለሥልጣን ብለው የማያደርጉት ነገር የለም ያልነው፡፡ በፍትሕ  በኩል  ስንሄድ፤  ዳኛችና ዓቃቢያነ-ህግ በሙያቸው ባላቸው ብቃት ሳይሆን በፖለቲካ ተአማኒነታቸው ብቻ ነው ዳኛችና ዓቃቢያነ ህግ ሊሾሙ የቻሉት፡፡ ይህ በህዝብ ላይ ከፍተኛ የፍትሕ ዕጦት ፈጥሮ ህዝቡ ዕሪ እያለ ይገኛል፡፡ ሁሉም ነገር አሁን በጉቦ ነው የሚፈፀመው፡፡ ከቀበሌ እስከ ከፍተኛ ፍርድ ቤትና የፍትሕ አካላት፡፡ መሬት በካድሬዎች ስለሚስተዳደር እንደፈለጉት እያደረጉት ይገኛል፡፡ በሌሎች የመንግሥት ሥራዎችም ኃላፊነት የሚሰጣቸው በፖለቲካ አባልነታቸው ነው ብቃት፣ትምህርት፣ስራ ልምድ አይሰራም፡፡ 

ይህ ማንን እየጎዳ ይገኛል ? ህዝብ ነዋ፡፡ ታድያ ህዝብ የሚጎዳ ከሆነ ለምን ተመረጠ ? ለስልጣን ተብሎ፡፡ ስልጣንን ከህዝብ ማስቀደም ማለት ነው? በትክክል፡፡ ሙስናን በሚመለከት፡- ጠ/ሚኒስቴር መለስ ሙስና መዋጋት አይፈልጉም፡፡ ለምን ? በሥልጣን ላይ ያሉ ሰዎች በፈፀሙት ህግ ፊት በማቅረብ ፍርድ እንዲገኙ አይፈልጉም፡፡ ምክንያት፡- 1ኛ. የቀኝ እጃቸው የሆኑ በሙስና የተዘፈቁ በመሆናቸው አሳልፈው መስጠት አይደፍሩም፡፡

2ኛ. ለቅርብ ወዳጆቻቸው ካላጋለጡ ሌለሎች ማጋለጥ ድፍረት አያገኙም፡፡ በዚህ ምክንያት ከድሃው ህዝብ ብዙ ሚሊዮን የአገሪቱ
ሃብት ጥቂት ባለሥልጣናት እያግበሰበሰት ይገኛል፡፡ አድልዎ ወገናዊነት በሰፊው ይስተዋላል፡፡ ከዩኒቨርስቲ ተመርቆ የሚወጣው ወጣት በመንግሥትም ይሁን በፖለቲካ ድርጅቶቻቸው ስም የተቋቋሙ የኢኮኖሚ ካምፓኒዎቻቸው ለመቅጠር አንችልም ራስህ ተደራጅተው ሥራ ፍጠር ይሉታል፡፡ ወጣቱም ሌላ አማራጭ ስለሌለው በድንጋይ ጠረባ፣በኮብል ስቶን ሥራ፣በብሎኬት፣በልስን እና በሌሎች የሥራ ዘርፎች ሳይወድ በግድ ያልፍልኝ ይሆናል በሚል ተስፋ ሲንቀሳቀስ ይገኛል፡፡ የባለሥልጣኖች ልጆች ግን በነዚህ የወጣቶች የኢኮኖሚ ድርጅቶች ብለው በሚጠሩዋቸው ድርጅቶች አንድም የለም፡፡ የሚበዙ ውጭ አገር ተምረው በዛው የቀሩ ናቸው ሌሎች ደግሞ ትእምት በሚባል የህወሐት ካምኒ ተቀጥረውና ሃላፊ በመሆን ወፈር ያለ ደመወዝ እየተከፈላቸው የተንደላቀቀ ኑሮ ይኖራሉ፡፡