Thursday, September 12, 2013

” እኔ ባልፍም እንኩዋን ሺህ ርዕዮቶች ስላሉ በርቱ አትደናገጡ “

September 12, 2013

Sources:-  Daniel Haregawi Timeline(FB)
ke  Sekedar alemu
Reeyot-Alemu
* የርዕዮት ደህንነት አደጋ ላይ መሆኑን እንድታዉቁት ስል ነዉ ይህንን በብዙ ሀዘን ዉስጥ ሆኜ የጻፍኩላችሁ
ትላንትና እንደሁል ጊዜዉ ስንቅ ይዤላት ወደ ቃሊቲ ሔድኩ በር ላይ ያለዉ ፖሊስ “የርዕዮት እህት ነሽ አይደል እሱዋን መጠየቅ አትችይም በአስተዳደር በኩል ሔደሽ ጠይቂ” አለኝ፡፡ እንዳዘዘኝ በአስተዳደር በር በኩል ሔድኩ ወደ ዉስጥ በስንት ትግል ከስለሺ (የርዕዮት እጮኛ) ጋር ገባን፡፡
ከብዙ ጥበቃ በሁዋላ በብዙ ፖሊሶች ታጅባ መጣች ፊትዋ ተለዋዉጦ ስለነበር ምን እንደሆነች ስጠይቃት ከእናት፡ አባት እና ንስሃ አባት ዉጪ ማንም ሊጠይቃት እንደማይችል እና የእነሱን ስም እንድትሰጥ እንደተጠየቀች እና አሚናዘር የሚትባል የሴቶች ክፍል ሀላፊ አልጋዋ ድረስ በመምጣት እንደሰደበቻትና እንደዛተችባት እየነገረችኝ እያለ አሚናዘር የተባለችዉ ሃላፊ ወደኛ በመምጣት ርዕዮትን በማመናጨቅና በመስደብ ከኛ ልትወስዳት ስትሞክር ለምን እንደሆነ ስጠይቃት “ከዛሬ ወዲህ ዐይኑዋን አታዩትም ማንም እኔን ሊያዝ አይችልም የእናንተ ጋዜጣና ሚዲያ ምን እንደሚያመጣ እናያለን ” በማለት ርዕዮትን በማዋከብ እና በመጎተት እየሰደቡ ወሰዱዋት፡፡ ምድር ላይያሉ ሰቅጣጭ እና ለህሊና የሚከብዱ ስድቦችን አወረዱብን በዚህ መሀል ርዕዮት ድምጹዋን ከፍ አርጋ “የማልጨርሰዉን ነገር አልጀምርም እኔን ለማንበርከክ እና ለማሸማቀቅ ክሆነ መቼም አላረገዉም ትገይኝም ከሆነ ነይ ተኩሺ ” ስትል ጎትተዉ ወሰዱዋት፡፡ እኛንም ከጊቢዉ አዋክበዉ አስወጡን፡፡

ኮሎኔል ሃይማኖት ይፈቱ…! ርዮት አለሙም ትፈታ!


733CornellHaymanotTesfayaኮሎኔል ሃይማኖት ይፈቱ…! ርዮት አለሙም ትፈታ!
ኮሎኔል ሃይማኖት የአቶ ገብረዋህድ ባለቤት ናቸው፡፡ ከጫካ ታግለው መጥተው ሹመት በሹመት ሆነው “ሲሾም ያልበላ ሲሻር ምን ሊበላ ነው” ብለው ሲበሉ፣ ሲበሉ፣ ሲበሉ…”የተበሉ” ሴትዮ ናቸው፡፡
አቶ ገብረውሃድ ማለት ደግሞ፤ “ስልጣናቸውን በመጠቀም ያከማቹት መሬት ቢሰበሰብ ኤርትራን የሚያክል ሀገር ይወጣዋል እና ትልቁ ስጋት ሰውዬው መሬቱን ለምን ወሰዱ… ሳይሆን ይሄንን መሬት ይዤ የራሴን እድል በራሴ ወስኛለሁ እና የመገንጠል መብቴ ይከበርልኝ እንዳይሉ ነው…” በሚል ሀገሬው ሲያማቸው የነበሩ ግለሰብ ናቸው፡፡
እንግዲህ እኒህ ቱባ ባለስልጣን ቱባ ቱባ ዝርፊያ አድርገዋል ተብለው ሲታሰሩ ባለቤታቸው ኮሌኔል ሃይማኖት ደግሞ የራሳቸውንም የባለቤታቸውም ዝርፊያ ውጤት የሆነውን ንብረት “ለማንኛውም መደበቅ ነው የሚሻለው…” ብለው ሲያሸሹ ተገኝተው ነው በቁጥጥር ስር የዋሉት፡፡
ከላይ ያየነው ከመንግስት ሚዲያዎች እንደሰማነው እና በራሳችን ቋንቋ ተርጉምን እንደፃፍነው ነው፡፡
ይሄን ያክል ከተንደረደርን፤
ኮሎኔል ሃይማኖት አዲሱን አመት በእስር ቤታቸው ድል ያለ ድግስ ደግሰው ቤተሰቦቻቸው እዛው ቃሊቲ ድረስ ሄደውላቸው ያማራቸውን ለብሰው ያሰኛቸውን በልተው ደስ ያላቸውን ጠጥተው ስቀው ተጫውተው ነው ያሳለፉት፡፡
ከሁለት ቀን በፊት ከጋዜጠኛ ርዮት አለሙ ጋር ክፍል የተጋሩት ኮሎኔል ከጋዜጠኛይቱ ጋር ከተገናኙበት ቀን አንስቶ “ቀልባቸው አልወደዳትም” ይዝቱባታል፡፡ ይሰድቧታል፡፡ ያንጓጥጧታል፡፡ ለዚህ ደግሞ የስጋ ዘመዳቸው ሆነቸው የቃሊቲ ሴት ዋርዲያዎች ሃላፊ አሚናዘር “እሰይ አበጀሽ የኛ ልጅ” ብላላቸዋለች፡፡
“ሙስና ይብቃ” ብላ ስትፅፍ ተገኝታ በቁጥጥር ስር የዋለችው ጋዜጠኛ ርዮት አለሙ፤ ከእናት እና ከአባቷ ውጪ ሌላ ሰው ማናገር አትችይም ተብላ ስትከለከል፤ ሙስና ይስፋ ብለው በሙስና የተዘረፈ ንብረቶችን ሲያሸሹ በቁጥጥር ስር የዋሉት ኮሎኔል ያለ የሌለ ሃይላቸውን ተጠቅመው ሊያበሳጯት እየተጉ ነው፡፡ ለዚህም አበል እንዲሆን በዓልን እስር ቤቱ መኖሪያ ቤታቸው እስኪመስል ድረስ አሸብርቀውበት ውለዋል፡፡
በተቃራኒው ጋዜጠኛ ርዮት አለሙ በዓሉን በርሃብ አድማ አሳልፋለች፡፡ እንደ ኮለኔሏ እና እንደ ዋርዲያዎቹ ዛቻ ከሆነ ርዮት አለሙን በተለያየ ዘዴ ምግብ መመረዝን ጨምሮ ጥቃት ሊያደርሱባት እንደሚችሉ…  ዝተውባታል፡፡
ኮሎኖል ሃይማኖትን ያሰራቸው አካል በጥፋታቸው እስር አስሯቸው ይሁን በስልጣናቸው ስራ እያሰራቸው ይሁን ግራ ተጋብተን እንገኛለን! ማሰሩ ከሆነ  ግን፤ ይሄ እስር ሙስናን የሚዋጋ ሳይሆን ጭራሽ በሙስና የሚያስወጋ ነውና እና ዛሬውኑ ይፈቱልን! ጋዜጠኛ ርዮት አለሙም ትፈታልን! ሌላው ይቅር …ቢያንስ እስር ቤት ውስጥ ድጋሚ መታሰሯ ይቁም!

Wednesday, September 11, 2013

የ፩ኛ ዓመት መልዕክት – የሚዲያ ተሃድሶ ግድ ነው!!


(ርዕሰ አንቀጽ - የ"ጋዜጠኛነት" ውንብድና ይቁም!!)

media


ዛሬ ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ከተቋቋመ አንድ ዓመቱ ነው። ባሳለፍነው አንድ ዓመት ውስጥ የደገፉን፣ ያበረታቱን፣ አስተያየት በመስጠት ያረቁንና በመድረካችን የተሳተፉ ያሉትን ያህል የምንሰራውን ስራ ለመቆጣጠር፣ የተመሰረትንበትን ግልጽ መስመር ለማስቀየር የሞከሩና ጨዋነት በጎደለው መልኩ የተዛለፉም አጋጥመውናል። ለሁላችም እንኳን ለአንደኛው ዓመት አደረሰን!!
“ወፌ ቆመች በሉን” በማለት ከዓመት በፊት የሚዲያውን ሰፈር በአሃዱ ብለን ከተቀላቀልንበት ጊዜ አንስቶ የሰራነውን ስራ በጥሞና ለመመልከት ሞክረናል። ሌሎች ሚዲያዎችንና ብሎጎችንም ዳሰናል። የራሳችን ደካማ ጎን ስንፈትሽ እግረ መንገዳችንን ዙሪያችንን ስንቃኝ የሚዲያ ተሃድሶ (ሪፎርም) አስፈላጊ እንደሆነ ተረድተናል። አምነናል። “መቼ” ለሚለው ጥያቄ ምላሹ ዛሬ፣ አሁን፣ አሁኑኑ የሚል ነው።

ድክመታችን

ስንጀምር በዘረጋናቸው ዓምዶች መሰረት ጊዜ በመጠበቅ መረጃ በወቅቱ አላስተላለፍንም። የሳምንቱ አጫጭር ዜናዎችና ድንቃ ድንቅ ወሬዎችን የምናቃምስበት የጎልጉል ቅምሻ ዓምድ በጀመርንበት አቅም መቀጠል አልቻልንም። የግጥም ጨዋታን በተከታታይ አላቀረብንም። ጦማሮች ሲላኩ ፈጥነን ያለ መለጠፍ ችግር አለብን። እነዚህ ከድክመቶቻችን መካከል በቅድሚያ የሚጠቀሱ ናቸው። ምንም እንኳን ስራችንን የምንሰራው በበጎ ፈቃደኞች በትርፍ ጊዜ ቢሆንም በግምገማችን በድክመት አስቀምጠነዋል። አንባቢዎችንንም ይቅርታ እንጠይቃለን።

ያጋጠሙ አንኳር ችግሮች

የተሳሳተ መረጃ በመላክ ታማኝነታችንን ለማሳጣት በተደጋጋሚ ሙከራ ተደርጓል። “እነማን ናቸው፣ ከየት መጡ፣” በሚል አጀንዳ ይዘው የተወያዩ አሉ። ማንነታችንና፣ ምንነታችንን እንድናብራራ በደብዳቤ የተጠየቅንበትም ጊዜ ጥቂት አይደለም። የኤዲቶሪያል ፖሊሲያችን ከሚፈቅደው ውጪ በዘለፋ የተሞሉ ጽሁፎች በመላክ እንዲስተናገድላቸው የወተወቱን በርካታ ናቸው። በቀጥታ በአድራሻችን የማይላክልንን ጽሁፍ ስለማናስተናግድ /ወደፊትም አናስተናግድም/ ወደ አንድ መንገድ ሊያጠጋጉን የሞከሩ አንቱና አንተ የሚባሉ አጋጥመውናል። ከሁሉም በላይ በተደጋጋሚ የጋዜጠኛነት ውንብድና ተፈጽሞብናል። ይህ መረን የወጣ ችግር ማቆሚያ ሊበጅለት እንደሚገባ አጥብቀን እናምናለን። ለሙያውና ለስነምግባሩ የሚገዙ በዚህ ሃሳባችን ድጋፍ እንደሚሰጡን እናምናለን።

በ2005 እንዲህ ብለን ነበር!


ከማበስበሻው ባህር የሚወጣ የለም- ይሰፋል እንጂ

difo


በአዲሱ ዓመት የተመሰረትንበትን አንደኛ ዓመታችንን ምክንያት በማድረግ በተለያዩ ወቅቶች ለንባብ ካበቃናቸው ርዕሰ ጉዳዮች መካከል መርጠን ለትውስታ አቅርበናል። ካቀረብናቸውም ሆነ በድረገጹ ላይ ያሉትን ጽሁፎች በመምረጥና በማሰራጨት ልደታችንን ታከብሩልን ዘንድ ግብዣችን ነው።
በሌላ በኩል የዝግጅት ክፍላችን ኤዲሪቶሪያል ቦርድ አንባቢዎች በነጻነት አስተያየት እንዲሰጡ፣ አስተያየታቸውም ያለ አንዳች ገደብ እንዲታተም ወስኗል። በመሆኑም ጎልጉልን አስመልክቶም ሆነ በርዕሰ አንቀጽ ላይ ባስቀመጥነው ሃሳብ ላይ በመንተራስ አስተያየት ለምትልኩ “ከስድብና ከዘለፋ” ውጪ በደስታ የሚስተናገድ እንደሆነ አስቀድመን እንገልጻለን። የዓመቱ ምርጥ በማለት “መለስ የቆፈሩት ጉድጓድ” እና “ጥቁሩ ሰው ይናገራል” የሚሉትን ቃለ ምልለስሶች በስጦታ አቅርበናል። መልካም አዲስ ዓመት፣ ለኛም መልካም አንደኛ ዓመት!!
አዲሱ ዓመት ፍትህ የሰፈነበት እርቅ የሚከናወንበት ይሆን ዘንድ እንመኛለን።
የትግራይ ህዝብ ስማ
“ሰሞኑን በውዴታም ይሁን በግዴታ በመቀሌ እጅግ ከፍተኛ የሚባል ቁጥር ያላቸው የትግራይ ተወላጆች ሲጨፍሩ፣ ሲዘሉ፣ ከበሮ እየመቱ የባህላቸውን ዘፈንና ውዝዋዜ ሲያወርዱ አይተናል። ምክንያቱ በግልጽ ባይነገርም ሲደበቅ የነበረው የህወሃት ሃብትና ንብረት ውጤት የሆኑ፣ በልዩ የመንግስት ድጋፍ የተከናወኑ ግዙፍ ተቋሞች በጎዳና ለህዝብ ሲቀርቡም ተስተውሏል። ልማቱ መልካም ነው። ደስ ይለናል። ምንም ተቃውሞ የለንም። ግን መልዕክት አለን። ለማን?ምሬትን፣ ጭቆናና መንገፍገፍ ሲበዛ በፍቃደኛነት በቦንብ ላይ እንደሚያስሮጥ ለሚያውቀው የትግራይ ህዝብ!! የትግራይ ህዝብ ስማ!!
… “የ100 ዓመት የቤት ስራ ሰጥተናቸዋል” በሚል በየድረገጹ የሚለጠፉ ተራ ድንፋታና ትዕቢት የሚፈጠሩትን ሓውዜኖች ከማብዛት ውጪ ትርፍ የላቸውምና ወደ ደጉ መንገድ መመለስና ሰብዓዊነትን በማስቀደም፤ ተደጋግፎ መኖርን ማጎልበት ይሻላል ለማለት እንወዳለን። ተሳስበውና ተረዳድተው የሚገነቡት የትም ሆነ የት የአገር ነውና ሁሉም ይኮራበታል፤ ይጠብቀዋል። ተጠቃሚ ይሆንበታል። የሚያምርብንም ይህ ነው። ህወሃት አልሰማም ብሏል። የትግራይ ህዝብ ግን ስማ!! ይህ ሁሉ የሚደረገው በስምህ ነው!! …

Tuesday, September 10, 2013

የ2005 ዋና ዋና ፖለቲካዊ ክንዉኖች


hailemariam


የመለስ ዜናዊ አስተሳሰብና ምግባር ሕዝብን በተለይም ፖለቲከኞችን በተራራቀ ተቃራኒ ጫፍ እንዳቆሙ መሞታቸዉ የኢትዮጵያን ፖለቲካ በበጎ ወይም በመጥፎ፥ ወይም በሁለቱም መሐል-ክፉኛ መንካቱ እንደማይቀር ያኔ ተብሎ ነበር። አሁንም አልቀረም።
የቀድሞዉ ጠቅላይ ሚንስትር ተሸኙ።
ሁለት ሺሕ አራትም ተሰናበተ። እና አዲስ ዓመት። ሁለት ሺሕ አምስት። ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ-ክርስቲያን ርዕሠ-ሊቃና ጳጳሳት እና፥ በአቶ መለስ ዜናዊ ሞት ማግስት የባተዉ ሁለት ሺሕ አምስት ካዲስ መሪ፥ ካዲስ ርዕሠ ሊቃነ ጳጳሳት ሹመት ጋር አዲስ ተስፋ አጭሮም ነበር። ዓመቱ ዛሬ-አርጅቶ ሊሰናበት ሁለት ቀን ቀረዉ። የዓመቱን የኢትዮጵያ አበይት ፖለቲካዊ ክንዉኖች እየጠቃቀስን፥ ተስፋዉ መጠዉለግ-መፅደቁን፥ ላፍታ እንቃኛለን። አብራችሁኝ ቆዩ።
መለስ በተቀበሩ በሳምቱ ሁለት ሺሕ አምስት እንደ አዲስ ዓመት ሲብት ሁለት የስዊድን ጋዜጠኞችን ጨምሮ በሺሕ የሚቆጠሩ እስረኞች በምሕረት መፈታታቸዉን የኢትዮጵያ መንግሥት ማወጁ፥ የአዲሱ ዓመት አዳዲስ መሪዎች አሮጌዉን ከፋፋይ መርሕ ከአሮጌዉ ዓመት ጋር ለማሰናበት ፍንጭ ማሳየታቸዉ መስሎ ነበር።
ከእስረኞቹ የመፈታት ዜና በተጨማሪ የኢትዮጵያ መንግሥት ከኦጋዴን ብሔራዊ ነፃዉጪ ግንባር (ኦብነግ) ጋር ለመደራደር መወሰኑን አስታዉቆም ነበር።ኦብነግ የመለስ ዜናዊ መንግሥት ለረጅም ጊዜ ባሽባሪነት የወነጀለዉ፥ ከሁለት ሺሕ ሁለት ጀምሮ ደግሞ ከአልቃኢዳ፥ ከአልሸባብ፥ እና ከሁለት ሐገር በቀል ድርጅቶች ጋር በሕግ-በአሸባሪነት የፈረጀዉ ቡድን ነዉ።semayawi rally
በዚሕም ሰበብ በመለስ ሞት ማግሥት አዳዲሶቹ መሪዎች ከኦብነግ ጋር ለመደራደር መስማማታቸዉን ሲያስታዉቁ፥ ለኢትዮጵያ ፖለቲካ አዲስ ተስፋ ማጫሩ አልቀረም። በአዲሱ ዓመት ዋዜማ ናይሮቢ ኬንያ ዉስጥ በኢትዮጵያ መከላከያ ሚንስትር ሲራጅ ፈርጌሳና በኦጋዴን ብሔራዊ ነፃ አዉጪ ግንባር የዉጪ ግንኙነት ሐላፊ በአብዱረሕማን መሕዲ መካካል የተደረገዉ ድርድር እንዲደረግ የወሰኑት አቶ መለስ ዜናዊ ከመሞታቸዉ በፊት መሆኑ ሲነገር ግን ተስፋዉ የአዲሱ ዓመት ፀጋ፥ የአዲሶቹ መሪዎችም ብልሕነት እንዳልሆነ ግልፅ ሆነ። እስረኞቹ የተለቀቁትም በመለስ ዉሳኔ እንደነበር ተነግሯል።
የሁለቱ ወገኖች ተደራዳሪዎች በድርድሩ ሥነ-ሥርዓታዊ ጉዳዮች ተስማምተዉ፥ ለመስክረም ማብቂያ ለሁለተኛ ዙር ድርድር ለመገናኘት ተቀጣጥረዉ ነበር። መንግሥት አማፂዉ ቡድን ሕገ-መንግሥቱን ካልተቀበለ አልደራደርም በማለቱ፥ አማፂዉ ቡድን ቅድመ ሁኔታዉን ባለመቀበሉ ቀጠሮዉ-በቀጠሮ ቀረ። ተስፋዉም ቢያንስ ለዚሕ ዓመት ተጨናጎለ።

Friday, September 6, 2013

አንዷለም አራጌ ከቃሊቲ ማጎሪያ የላከው መልዕክት እጃችን ደርሷል – የሐምሌ ጨረቃSeptember 5, 2013

 

አንዷለም አራጌ ዋለ (ከቃሊቲ ማጎሪያ) ክፍል ሁለት


Ato Andwalem Araga (UDJ)
በሀገሬ ሰማይ ስር በሚደረገው የተቃውሞ ፖለቲካ እንቅስቃሴ ከኢዴፓ እስከ አንድነት ፓርቲ ድረስ በመሳተፍ ለአስራ ሶስት ዓመታት ያህል የምችለውን አስተዋጽኦ አድርጌያለሁ፡፡ ይህ ኩነትም የፓርቲዎችን ጓዳ ፈትሼ ግንዛቤ እንዳገኝ ስላመቻቸልኝ፣ በቀጣይ ህዝባችን የፖለቲካና ሰብአዊ መብቶቹ ተከብረው ነፃነቱን እንዳያገኝ እንቅፋት ሊሆኑ ይችላሉ ብዬ የማስባቸውን ነጥቦች እንደሚከተለው ለማቅረብ እወዳለሁ፡፡

1-እንደ ገዥው ፓርቲ፣ ተቃዋሚ ድርጅቶችም ከኋላቀሩ የፖለቲካ ባህላ የተላቀቁ አለመሆናቸው ነው፡፡ እናም አዲስ የፖለቲካ ባህል ለማስጀመር ከመስራት ይልቅ ሳያውቁት ከዘመነ-መሳፍንት የተቀዳውን የፖለቲካ ባህል በተሻለ ተግባራዊ ለማድረግ ሲንቀሳቀሱ ዛሬም ይታያሉ፡፡
2-የእስከ ዛሬውን የከሸፈ ሂደት የገመገመና የኢትዮጵያን ህዝብ ለአንዴና ለመጨረሻ ከተጫነበት የጭቆና ቀንበር ለማላቀቅ የሚያስችል በውል የታሰበበትና የተጠና የፖለቲካ ቀመር እጦት በተቀቃዋሚ ፓርቲዎች ዘንድ በጉልህ ይንፀባረቃል፡፡

3-የማያምኑበትን መቃወም ተገቢ የሆነውን ያህል የየራሳችንም ህፀፆች ያለርህራሄ ማየት፣ አይቶም ነቅሶ ማውጣት ተገቢ ነው፡፡ ነገር ግን በተቃዋሞ ጎራ ባለነው ፖለቲከኞች ላይ ይህንን የማድረግ ችግር ይታይብናል፡፡ ህፀፆችን ቀድሞ ማየቱ ከሌላ ወገን የሚሰነዘረው ነቀፋ ምክንያቱን ለመረዳት እድል ይሰጣል፡፡ በትችት ከመሰበርም ይታደጋል፡፡

4-ከ1960ዎቹ ጀምሮ የኢትዮጵያ ፓርቲዎች መለያ ከሆኑት አንዱ ‹ግትርነት› መሆኑ አከራካሪ አይመስለኝም፡፡ ይህ ሁኔታ በፓርቲዎች መካከል ብቻ ሳይሆን፣ በራስ ፓርቲ አባላት ውስጥም የሚፈጠሩ ችግሮች ከግትርነት የሚነሱ ናቸው፡፡ ‹‹መሸነፍ››፣ ‹‹ማሸነፍ››፤ ‹‹መንበርከክ››፣ ‹‹ማንበርከክ›› በሚለው የጫወታ ህግ ታስረን በቆምንበት ስንረግጥ በአስከፊው የመከራ ዘመን እንድንቆይ አድርጐናል፡፡ ችግር የመፍቻ ስልትም ሆነ ባህል አላዳበርንም፡፡ እንዲያውም የትግሉ እንቅስቃሴ ከአገዛዙ ጋር መሆኑ ቀርቶ በእኛ መካከል ሆኗል፡፡

Monday, September 2, 2013

ዛሬ ከሰልፉ ላይ ታፍነው የተወሰዱ ሙስሊሞች በከፊሉ (ድምፃችን ይሰማ)September 1, 2013


 
Ethiopian Muslims 1ዛሬ ከሰልፉ ላይ ታፍነው የተወሰዱ ሙስሊሞች አብዛኞቹ በኤግዝቢሽን
ማእከል ግቢ ውስጥና ከዋናው መድረክ ጀርባ ካለው የኢትዮጵያ የሰላም እና የልማት
ኢኒስቲትዩት ግቢ ውስጥ ይገኛሉ፡፡
ሙስሊሙ እየተነጠለ ሲወሰድ
Ethiopian Muslims 1
ሙስሊሙ እየተነጠለ ሲወሰድ