Wednesday, May 28, 2014

ጠረኑ የሚከረፋው የግንቦት ሃያ 23ኛ ዓመት “ዓመድ”


(ቀጭኑ ዘ-ቄራ)

amanuel
ሚስት ከቤቷ ጥጋ ጥግ ትንንሽ ጊዜያዊ ጉልቻ ጎልታ ካንዱ ወዳንዱ እየተዛወረች ስራዋን ስትሰራ፣ ስትቀቅል፣ ስታነኩር፣ ስትጋግር፣ ስትወጠውጥ … ድንገት ባንዱ አቅጣጫ እሳቱ መልኩን ቀየረ። ቀስ ብሎ ለካስ ወደ ቤቱ ተዛምቶ ነበርና ቤቱ ነደደ። እሳቱን ያዩ ለማጥፋት እየተሯሯጡ ደረሱ። አልሆነም የቤተሰቡ መኖሪያ ነደደ። ቤቱ የቆመው ለመቀጣጠል በሚያመች ማዋቀሪያ ነበርና ወደ አመድ ተቀየረ። ልክ እንደ ጎሳ ፖለቲካ!! እንደ ግንቦት 20 ዓመዳማ ፍሬዎች!!
እሳቱን ለማጥፋት የሞክሩት ጎረቤቶች አዘኑ። “እሳት በቀላሉ የሚበላው ቤት ይዘሽ ዙሪያውን እሳት ማቀጣጠል አልነበረብሽም” ብለው ገሰጿት። ማጣፊያው ያጠራት ሴት “እባካችሁ ባለቤቴ ሲመጣ አትንገሩት” አለቻቸውና ተማጸነች። ጎረቤቶቿ በንግግሯ ተገርመው “ከሄደበት ሲመጣ የሚገባበት ካገኘ ማን ይነግረዋል” ብለዋት ተሰናበቷት። “ቤት ባገር ይመሰላል” እያለ የሚያስተምረኝ የመሰየሚያ ቤት ባልደረባዬ ታወሰኝ፡፡
የተለመደው ሰላምታዬን በቅድሚያ ኑሮ ለሚያላምጣችሁ … ለኑሮ ችጋር ሰለባዎች ይሁን!! ክረምት/ቡሄ መጣ። ክረምት ስጋት የሆነባችሁ ኗሪዎች “አንድዬ ይከልላችሁ” ከማለት የዘለለ ምርቃት የለኝም። ዶፉን፣ ውርጩን፣ ቁሩን …. በደጅ ሁናችሁ የምትገፉት የ”ኗሪዎች” “አኗኗሪዎች”፣ በወጉም አኗኗሪ መሆን እንኳን ያቃታችሁ፣ ለናንተም ምርጫ ደርሷል። አሁን እናንተን ምን ብለው ይሆን “ምረጡኝ” ብለው የሚጀነጅኗችሁ? ለነገሩ እኮ ዝናብ ሲመጣ የሚያነቡ ቤት ውስጥ ያሉ የውጪ/ደጅ አዳሪዎች ከናንተ ይበዛሉ። በፈረቃ የሚተኙትስ ከናንተ በምን ይሻላሉ? አረ ስንቱ … ቀኝኑ ዘ-ቄራ ነኝ!! ቋሚን አሳንሰው ለሙት መንፈስ በሚገብሩና በሚሰግዱ መመራትም ያው የደጅ ኑሮ ማለት ነው። ያለ ህግ መገዛትም ያው የዱር ኑሮ ነው !! ሲያስጠላ!!

40 – 23 የኢህአዴግ የጎሳና የመጥበብ ሰረገላ ሐዲዱ ላይ ነውን?


“ኢትዮጵያን በጎሳ ሳጥን ቆልፎ የሚጓዘው ህወሃትና ድግሱ”

40 - 23
ህወሃት በነጻ አውጪ ስም ታግሎ ኢትዮጵያን መግዛት የጀመረበትን 23ኛ ዓመት በዓሉን እያከበረ ነው። ወዳጆቹና መሪዎቹ ባስቀመጡት እቅድ መሰረት ኢትዮጵያን “በመተካካትና በተሃድሶ” ስም ራሱን እያገላበጠ ለመግዛት የቆረጠው ጊዜ በትንሹ 40 ዓመታት እንደሆነ ይታወቃል። አሁን ባለው የሰረገላው ጉዞ ኢህአዴግ ከ40 – 23 ከመቀነሱ ውጪ አሰበበት ስለመድረሱ መገመት የሚያስችል ምልክት የለም። እንደውም ስጋት እንጂ።
ሲጀመር “የገበሬ ተሟጋች” ነኝ በማለት ራሱን የአርሶ አደሩ ወኪል አድርጎ የተነሳው ህወሃት፣ ኢህአዴግ ሆኖ አገር መግዛት ሲጀምር ያስቀደመው የብሄር ብሄረሰቦችን የመብት ጥያቄ እንደ ውዳሴ ጸሎት በመደጋገም ነበር። በዚሁ በጎሳ ላይ ተመስርቶ በቋንቋ የተቆለፈው የአገዛዝ ስልት ሲጀመር ማስጠንቀቂያ የሰጡ፣ ለመታገል የሞከሩ፣ የታገሉ፣ ያስተባበሩ፣ ያደራጁ የህወሃት የ40 ዓመት ጉዞ ጸር ተደርገው ተወሰዱ። ስለ ኢትዮጵያ ጥቅምና ኢትዮጵያዊነት ያሳሰቡ ጠላት ተደርገው ተፈረጁ። በስውር በአፈና፣ በግልጽ ህግ እየተጠቀሰባቸው ከጫወታና ከመኖር ተገለሉ። ብዙዎች እንደሚሉት “የጉዳቱን መጠን ህወሃትና የተጎዱት ቤተሰቦች ይቁጠሩት”!

Saturday, May 24, 2014

ስብሃት “እርቅን” እንሞክራለን፤ ከባልደረቦቼ ጋር እመክራለሁ አሉ


እርቅ ላይ የምትሰሩ የት አላችሁ?

reconciliation
ባለፈው ሳምንት የጀርመን ድምጽ ሬዲዮ የተቃዋሚ ፓርቲ ወኪሎችንና አቶ ስብሃትን ባንድነት በየተራ አናግሮ ነበር። ከውይይቱ የተለመደ ክርክር በዘለለ አቶ ስብሃት እርቅ አስፈላጊ መሆኑንን ማመናቸው የተለየ ጉዳይ ነበር። እንደ እርሳቸው አነጋገር አሁን የተጀመረውን መልካም የልማት ስራ ለማስቀጠል እርቅ አስፈላጊ ነው። የእርቅን አስፈላጊነት በማመን ከባልደረቦቻቸው ጋር በመምከር የእርቅ ጉባኤ ለማዘጋጀት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል።
አቶ ስብሃት “የተቃዋሚ ፓርቲ አለ ብዬ አላምንም” በማለት ተቃዋሚዎችን እንደወትሮው ሁሉ ዘልፈዋል። “መደብ የላቸውም” ሲሉ ተቃዋሚዎችን ጭራሽ እንደ ፓርቲ እንደማይቆጥሯቸው የተናገሩት አቶ ስብሃት ከዘለፋቸው በኋላ ስለ እርቅ አግባብ መናገራቸውን፣ ጠያቂው እሳቸው ባነሱት አዲስ ሃሳብ ላይ በመንተራስ ማረጋገጫ ሲጠይቃቸው “ከጓደኞቼ ጋር መክሬ” በማለት በቅርቡ የእርቅ መድረክ እንዲፈጠር እንደሚተጉ መናገራቸውን ተከትሎ እርቅ ላይ እንሰራለን ከሚሉ ወገኖች ምላሽ አልተሰማም።
አሁን ባለው ውጥረት የነገሰበት የኢትዮጵያ ፖለቲካ አብዛኞችን ስጋት ውስጥ የከተተ ነው። በስዊድን አገር በአንድ የእራት ግብዣ ላይ ተገኙ የትግራይ ተወላጅ ለጎልጉል እንደተናገሩት “በጎሳና በክልል ተለይቶ የሚንቦገቦገው የጥላቻ ፖለቲካ መጠኑ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱ አስግቶኛል። እርቅ ብቸኛ መፍትሔ ነው። በዚህ ሃሳብ ላይ መስራት ግድ ነው” የሚል አስተያየት ሰጥተዋል።
በፍርሃቻ ከሁሉም ያጣ ላለመሆን ኢህአዴግን የሚደግፉ እንዳሉ ያመለከቱት እኚሁ ሰው የኢትዮጵያ ጉዳይ በእጅጉ ዕረፍት እንደነሳቸው አልሸሸጉም። “ስብሃት ነጋ እርቅ ላይ ለመስራት ከልብ ያሰቡ ይመስልዎታል?” በሚል አስተያየታቸውን የተጠየቁት እኚሁ ሰው “ኢህአዴግም ሆነ ህወሃት እኮ የሰዎች ጥርቅም እንጂ ሌላ ግዑዝ ነገር አይደሉም። ችግሩን ከሁላችንም በላይ ይረዱታል። እንደውም እነሱ የሚያውቁትን ያህል የችግሩን አሳሳቢነት ተራው ነዋሪ ቢረዳ ልቡ በድንጋጤ ሊቆም ይችላል” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል። አያያዘውም ኢህአዴግ ችግሮች ገንፍለው እንዳይወጡ የሰጋበት ደረጃ እንደሚገኝ አመልክተዋል። በሁሉም አቅጣጫ የሚያገኟቸው ወገኖች የሚነግሯቸው ይህንኑ የስጋት ጉዳይ እንደሆነም ተናግረዋል።

Tuesday, May 20, 2014

በአባይ ጉዳይ ኃያላኑ በግብጽ ላይ ጫና እየፈጠሩ ነው


የጫናው መነሻ አነጋገሪ ሆኗል

egypt abay and the west
ምዕራባውያን ሃያላን አገሮች ግብጽ በአባይ ዙሪያ የድርድር ጠረጴዛ ላይ እንድትቀመጥ ጫና እያደረጉ መሆኑ ተሰማ፡፡ ዜናውን የዘገበው አልአህራም ቃል በቃል ግብጽ ላይ ጫና ተፈጠረ ብሎ ባይጽፍም ከዜናው ለመረዳት እንደተቻለው ግብጽ ላይ ጫና እየተደረገባት ነው፡፡ ሃያላኑ ግብጽ ላይ እያሳደሩት ያለው ጫና መነጋገሪያ ሆኗል፡፡
እንደ ጋዜጣው ዘገባ ያለፈው ቅዳሜ የግብጹ የውጭ ጉዳይ ሚ/ር ከኢትዮጵያ ጋር በአባይ ጉዳይ ለመደራደር አገራቸው ፈቃደኛ መሆኗን ማሳወቃቸውን ጠቅሶ ዘግቧል፡፡ ይህንን መግለጫ ከመስጠታቸው በፊት የግብጹ የውጭ ጉዳይ ሚ/ር በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚ/ር መ/ቤት የውሃ ሃብት ልዩ አስተባባሪ ከሆኑት አሮን ሳልዝበርግ እንዲሁም ከአውሮጳ ኅብረት ልዩ ልዑክ አልክሳንደር ሮንዶስ ጋር ውይይት ማድረጋቸው ታውቋል፡፡
በተለይ የአሜሪካው ተወካይ ሳልዝበርግ ወደ ግብጽ ከመሄዳቸው በፊት አዲስ አበባ ላይ ቆይታ አድርገው ከኢህአዴግ ባለሥልጣናት ጋር ግድቡን በተመለከተ ውይይት ማድረጋቸው አብሮ ተዘግቧል፡፡ ሆኖም ኢህአዴግ በምን ነጥቦች ላይ እንደተደራደረ የተገለጸ ነገር ባይኖርም የአሜሪካው ባለሥልጣን ወዲያው ወደ ግብጽ እንደበረሩ ግብጽ ድርድር መፈለጓ መገለጹ የበርካታዎችን ትኩረት የሳበ ጉዳይ ሆኗል፡፡
idan ofer
ኢዳን ኦፈር – ፎቶ ሪፖርተር
በተያያዘ ዜና ሪፖርተር እሁድ ባስነበበው ጋዜጣ ላይ እስራኤል በኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጨት ሥራ የመሰማራት ዕቅድ እንዳላት ዘግቧል፡፡ እስካሁን ድረስ እስራኤል በኃይል ማመንጨት ሥራ ውስጥ የመሳተፍ ፍላጎት እንዳለት ሲጠቀስ የቆየ ቢሆንም ከዚሁ ጋር ተያይዞ በርካታ ጥያቄዎች ሲነሱ ቆይተዋል፡፡ ሆኖም እንደ ሪፖርተር ዘገባ ከሆነ በኢትዮጵያ የፖታሽ ፕሮጀክት 30በመቶ ባለድርሻ የሆኑትን የሚስተር ኢዳን ኦፈር ኩባንያዎች በኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ዘርፍ የመሰማራት ዕቅድ እንዳላቸው ጠቅሷል፡፡
እንደ ዜናው ከሆነ እስራኤል የምትሰማራበት የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ “የውኃ፣ የጂኦተርማል ወይም የንፋስ መሆኑን” በግልጽ እንዳላሳወቀች ነገር ግን ጥናቱ በኩባንያው ቴክኒክ ቡድን በኩል እንደሚካሄድ የኩባንያው ባለቤት መናገራቸውን ጨምሮ ዘግቧል፡፡ ሚስተር ኦፈር የሚመሩት ኢዝራኤሊ ኬሚካልስ የተባለው ኩባንያ በማዳበሪያና መሰል ምርቶች ላይ የተሠማራ ሲሆን የማዕድን ማውጣት ተግባሩን በእስራኤል፣ በአሜሪካ፣ በአውሮጳና ቻይን ያካሂዳል፡፡ ከኩባንያው አክሲዮን ሁለተኛው ከፍተኛ ባለድርሻ የካናዳው የፖታሽ ኮርፖሬሽን እንደሆነ ይታወቃል፡፡
የእስራኤል በኢትዮጵያ በኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት ተግባር የመሰማራቷ ዜና ምናልባትም ከአባይ ግድብ ጀርባ የሃያላኑ አገራት ድጋፍና ጥበቃ እንዲሁም ቀጥተኛ ወይም ተዘዋዋሪ የሆነ ጥቅም የማስከበር ፍላጎት እንዳለ የሚሰነዘረውን ሃሳብ ያጠነክረዋል፡፡ አንዳንዶች እንደሚሉት የጫናው መነሻ ይህ የጡንቸኞቹ የጥቅም ጉዳይ እንደሆነ ያስረግጣል ይላሉ፡፡
በዚህና በተለያዩ ምክንያቶች በአባይ ግድብ ዙሪያ የሚነሱት መላምቶች ወይም መከራከሪያዎች ከሃያላኑ ጫና ጋር ተዳምረው መነጋገሪያ ርዕስ ሆኗል፡፡ግብጽ ጫናውን አስመልክቶ በይፋ የገለጸችው ተቃውሞ ወይም ቅሬታ የለም፡፡ ይሁን እንጂ በግብጽ የፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ዘመቻ ላይ ያሉትና የምዕራባውያን ቀጥተኛ ድጋፍ ያላቸው ፊልድ ማርሻል አል-ሲሲ “የውሃ ነገር” ለግብጽ “የህይወትና የሞት ጉዳይ” መሆኑን መግለጻቸውንና  ከኢትዮጵያ ጋር በመሆን መፍትሔ መፈለጉ “የግድ” እንደሆነ ማስታወቃቸውን ጎልጉል ዘግቦ ነበር፡፡

Tuesday, May 13, 2014

ደቡብ ሱዳን – የሰላም ድርድር ወይስ ቁማር?


“ካልፈረማችሁ ለICC አሳልፈን እንሰጣችኋለን” ሃይለማርያም

Ethiopia South Sudan
የደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ስምምነቱን የማይፈርሙ ከሆነ ጠ/ሚ/ር ሃይለማርያም ለዓለምአቀፉ የወንጀለኞች ፍርድቤት (ICC) አሳልፈው እንደሚሰጧቸው መግለጻቸውን በጁባ የጎልጉል ምንጭ አስታወቁ፡፡ ሱዳን ትሪቢዩን በበኩሉ ስምምነቱ የማይፈረም ከሆነ እስር እንደሚጠብቃቸው ሃይለማርያም ለሳልቫ ኪር መናገራቸውን ምንጮቹን ጠቅሶ ዘግቧል፡፡ አርብ የተፈጸመው የስምምነት ፊርማ ገና ሳይደርቅ ሁለቱም ኃይላት ወደ እርስበርስ ውጊያው ተመልሰው በመግባት እየተካሰሱ ነው፡፡
እጅግ ደም አፋሳሽ በሆነውና ለበርካታ ዜጎች መፈናቀል ምክንያት የሆነው የደቡብ ሱዳን የእርስበርስ ጦርነት ከጥቂት ቀናት በፊት አዲስ አበባ ላይ በፊርማ ሲጸድቅ ብዙ ተስፋ የተጣለበት ነበር፡፡ ሆኖም ስምምነቱ ከተጽዕኖ ባለፈ መልኩ በዕለቱ በፊርማ ካልጸደቀ ሳልቫ ኪርንም ሆነ ሬክ ማቻርን ሃይለማርያም ደሳለኝ ለዓለምአቀፉ የወንጀለኞች ፍርድቤት አሳልፈው እንደሚሰጧቸው የተነገራቸው መሆኑን የጎልጉል ምንጭ ከጁባ አስረድተዋል፡፡ ሳልቫ ኪር ወደ ጁባ ከተመለሱ በኋላ ከካቢኔያቸውና ቅርብ አማካሪዎቻቸው ጋር በተነጋገሩ ወቅት በስምምነቱ ወቅት የነበረውን ሁኔታ ባስረዱበት ወቅት መናገራቸውን የመረጃው አቀባይ ለጎልጉልአስታውቀዋል፡፡ ሁኔታው ለደቡብ ሱዳን እጅግ አሳፋሪ ከመሆኑ የተነሳ ደቡብ ሱዳን አምባሳደሯን ከኢትዮጵያ እስከማስወጣት እንዳሳሰባት ጨምሮ ተገልጾዋል፡፡

Sunday, May 11, 2014

ከቦታቸው መፈናቀልን የተቃወሙ ኢትዮጵያዊያን እስራትና ግድያ እናወግዛለን!


eprp yl
ሰሞኑን ከአዲስ አበባ አቅራቢያ ያሉ ብዙ ከተሞችን በዋና ከተማው ስር ለመጠቅለል የወያኔ አጋዛዝ “ የተቀናጀ የልማት ማስተር ፕላን” በሚል ያወጣውን አቅድ፣ የማፈናቀል እርምጃ ነው ብለው በሰላማዊ መንገድ ተቃውሟቸውን ለማሰማት ሰልፍ የወጡ ዜጎችን በጅምላ ገድሏል፣ ብዙዎቸን አቁስሏል፣ በገፍ አስሯል። በአምቦ ከተማ ብቻ አስካሁን በተገኑት መረጃዎች በትንሹ 47 የሚሆኑ የተገደሉና ብዙ የቆሰሉ ሲገኙበት፣ በጅማ ካምፓሶች፣ ወለጋ፣ መቱ፣ ቦሉ ሆራ፣ አዳማ ሃረሚያና በሌሎች አካባቢዎች ተመሳሳይ የጭካኔ አርምጃ ወስዷል። ኢሕአፓ-ወክንድ ይህን የወያኔ ኢሰብአዊ ድረጊት አጅግ በመረረ ቃል ያወግዛል። (ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ)

Wednesday, May 7, 2014

Ethiopia: Brutal Crackdown on Protests


Human Rights Watch

asko
(Nairobi) – Ethiopian security forces should cease using excessive force against students peacefully protesting plans to extend the boundaries of the capital, Addis Ababa. The authorities should immediately release students and others arbitrarily arrested during the protests and investigate and hold accountable security officials who are responsible for abuses.
On May 6, 2014, the government will appear before the United Nations Human Rights Council in Geneva for the country’s Universal Periodic Review of its human rights record.
“Students have concerns about the fate of farmers and others on land the government wants to move inside Addis Ababa,” said Leslie Lefkow, deputy Africa director. “Rather than having its security forces attack peaceful protesters, the government should sit down and discuss the students’ grievances.”Basic RGB
Since April 25, students have demonstrated throughout Oromia Regional State to protest the government’s plan to substantially expand the municipal boundaries of Addis Ababa, which the students feel would threaten communities currently under regional jurisdiction. Security forces have responded by shooting at and beating peaceful protesters in Ambo, Nekemte, Jimma, and other towns with unconfirmed reports from witnesses of dozens of casualties.
Protests began at universities in Ambo and other large towns throughout Oromia, and spread to smaller communities throughout the region. Witnesses said security forces fired live ammunition at peaceful protesters in Ambo on April 30. Official government statements put the number of dead in Ambo at eight, but various credible local sources put the death toll much higher. Since the events in Ambo, the security forces have allegedly used excessive force against protesters throughout the region, resulting in further casualties. Ethiopian authorities have said there has been widespread looting and destruction of property during the protests.

“ውሃ የህይወትና የሞት ጉዳይ ነው”፤ መፍትሔ መፈለግ “የግድ” ነው፤ አል-ሲሲ


“በግድቡ ምክንያት ግብጽ 'የማይቀር አደጋ' ውስጥ አይደለችም”

el sisi
በቅርቡ በግብጽ ለሚካሄደው ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ያሸንፋሉ እየተባለ የሚጠበቁት ዕጩ ተወዳዳሪ አብዱል ፈታህ አል-ሲሲ “የውሃ ነገር” ለግብጽ “የህይወትና የሞት ጉዳይ” ሲሉ ገለጹ፡፡ ከኢትዮጵያ ጋር በመሆን መፍትሔ መፈለጉ “የግድ” እንደሆነ አስታወቁ፡፡ በቅርቡ በግድቡ ዙሪያ ጥናታዊ ጽሁፍ ያቀረቡ በውጭ የሚገኙ ሦስት ኢትዮጵያውያን ምሁራን የግድቡ መሠራት ግብጽን “በማይቀር አደጋ” ላይ እንደማይጥላት አስረዱ፡፡
በግብጽ በተላለፈ የቴቪ ስርጭት ትላንት ቃለመጠይቅ የሰጡት የቀድሞው የግብጽ ጦር መሪ ፊልድ ማርሻል አል-ሲሲ ግድቡን አስመልክቶ ሰፊ ትንተና እንዳልሰጡ አልሃራም የቲቪ ስርጭቱን ጠቅሶ ዘግቧል፡፡ ሆኖም ዕጩ ፕሬዚዳንታዊ ተወዳዳሪ “የሌሎችን ፍላጎትና ጥቅም የምንረዳ መሆናችንን ማሳየት ይገባናል፤ (የዚያኑ ያህልም) የራሳችንን ጥቅም ለማስጠበቅ ጽኑ መሆን አለብን፤ (ምክንያቱም) ውሃ ማለት ለእኛ የህይወትና የሞት ጉዳይ ነው” ብለዋል፡፡

Monday, May 5, 2014

የዞን ዘጠኝ ጦማርያን እና ጋዜጠኞች እነማን ናቸው?


zone 9
ፍርሃት የማያሰራው ነገር የለም።ኢህአዲግ በከፍተኛ የፍርሃት ማጥ ውስጥ ነው።ሁሉንም ይፈራል።አይዞህ አትፍራ ቢሉትም የሚችል አይመስልም።በሕዝብ ላይ የሰራቸው ሕዝብ የሚያውቃቸው እና የማያውቃቸው ብዙ ድብቅ ስራዎች ስላሉት የመፍራት ደረጃው ከዕለት ወደ ዕለት እየባሰበት እንጂ እየተሻለው አልሄደም። የሚደግፉትም ልያፅናኑት አልቻሉም።ከሚገባው በላይ ፍርሃት ሲያንቀጠቅጠው ሲመለከቱ እነርሱም ይብሱን ፈሩ።ብዙ የስርዓቱ ደጋፊዎች እና በሀብት የደለደሉቱ ሀገር ጥለው እየወጡ መሆኑን መረጃዎች ያሳያሉ።ይህ ደግሞ ሌላው የፍርሃት ገፅታ ነው።
የዞን ዘጠኝ ጦማርያን እና ሌሎች ሰሞኑን የተያዙት ጋዜጠኞች ምንም የተደበቀ አጀንዳ የሌላቸው ግን ህገ መንግስቱ ላይ የሰፈረው ሃሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት ይከበር ያሉ በእዚህም መስረት የሕገ መንግስቱን አንቀፅ እየጠቀሱ የሃሳብ የመግለፅ መብታቸውን የተጠቀሙ፣የሚሰሩት በመንግስት መስርያቤቶች የሆነ፣የሚፅፉት አይደለም ምን በልተው ከማን ጋር ውለው እንዳደሩ መንግስት ብቻ ሳይሆን ሕዝብ የሚያውቃቸው ኢትዮጵያውያን ናቸው።ከእዚህ በፊት በሃሳብ የሞገቱትን ሁሉ ”ህገ መንግስቱን እና ስርዓቱን ለመናድ የተንቀሳቀሱ” እያለ ሲያስራቸው የነበረው መንግስት ዛሬ እራሱ ህገ መንግስቱን አክብረው ሕግ እየጠቀሱ የፃፉትን በ20 ዎቹ እድሜዎች ውስጥ የሚገኙ ወጣቶችን ”ሃገርን በውጭ ከሚኖር ድርጅት ጋር ተመሳጥረው ሊያሸብሩ” እያለ ፌዝ አይሉት ቀልድ መሰል ክስ አቅርቦ ማዕከላዊ እስር ቤት አስገባቸው።ምንም አይነት ወንጀል እንደሌለባቸው እራሱ ኢህአዲግ ያውቀዋል።ግፍ መስራት የማይሰለቸው እና በፍርሃት የተዋጠ መሆኑ ግን የእዚህ አይነቱን ተግባር እንዲቀጥልበት አድርጎታል።

Saturday, May 3, 2014

ህመሙ የጋራ ሀመም ነው ጩኸቱም የሁላችንም ጩኸት ነው (የአቋም መግለጫ እና ምክር ብጤ!)


10177945_10201933830169591_165690015030009442_nህመሙ የጋራ ሀመም ነው ጩኸቱም የሁላችንም ጩኸት ነው (የአቋም መግለጫ እና ምክር ብጤ!)
በአሁኑ ሰዓት በኦሮሚያ ክልል ሁሉም አካባቢዎች ለማለት በሚያስደፍር መልኩ ህብረተሰቡ በመንግስት ላይ ያለውን ተቃውሞ እያሰማ ነው። መንግስትም በበኩሉ የፈሪ ዱላውን እያወረደው ይገኛል። እውነቱን ለመናገር መፍራት ተቃወሞ የሚያመጣ ተግባር ሲፈጽሙ ነበር እንጂ ተቃውሞውን አለነበረም።
ኢህአዴግዬ በክላሿ ተማምና ያላስቀየመችው የህብረተሰብ ክፍል ካለ እርሱ ኢህአዴግን እንደ ግል አዳኙ የተቀበለ ብቻ ነው። ዛሬ በኦሮሚያ ክልል ሰላማዊ ተቃዋሚዎች ላየ እየተወሰደ ያለው ርምጃ በተመሳሳይ መልኩ በአማራ ክልል ጎንደርም እየተወሰደ ይገኛል ይሄው አይነት ከዚህ በፊት በጋምቤላ፣ በአዲሳባ፣ በደቡብ ብሄር በሄረሰቦች ክልል ሀዋሳ እና ተረጫ ወረዳ ላይ እንዲሁም በቅርብ ጊዜ በሀረሪ ከልል ሀረር ላይ ሲወሰድ ነበር። (እነዚህ በቀላሉ ያስታወስኳቸው ናቸው ማስታወሻ ብናገላብጥ ደግሞ ሌላም ሌላም ይገኛል)
በጥቅሉ እነደ ኢህአዴግ ያሉ ”ፋራ” አምባገነኖች ለሰላማዊ ተቃወሞ ሰላማዊ ምላሽ ሲሰጡ ታይቶም አይታወቅ። እኛ የምንጸለይ የነበረው ኢህአዴግ ገደላውን ትታ የምትጠየቀውን እንደ ዘመናዊ ገዢ ፓርቲ፤ በቅጡ ብትመልስ ነበር። ግን አልሆነም። በዚህም የተነሳ እስከ አሁንም ድረስ በኦሮሚያ ክልል ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ሰላማዊ ዜጎች በአልሞ ተኳሾች እና ሳያልሙ ተኳሾች ተገድለዋል ቆስለዋልም።
ይህ ህመም የኦሮሚያ ክልል ነዋሪዎች እና ዘመዶቻቸው ብቻ ሳይሆን የመላው ኢትዮጵያውያን ነው። ሰለዚህም ሁሉም በያለበት እና በየ አቀሙ ጩኸቱን ሊቀባበል ይገባል የምለው።
“አንተ ውጪ ቁጭ ብለህ….”
ወጪ ሀገር የሚገኝ ሰው የሚገጠመው ትልቁ ፈተና ይሄኔ ነው። ጩኸቱ የጋራ ነው ብዬ ስናገር አንዳንድ ወዳጆች ገና አንብበው ሳይጨረሱት ሁላ “አንተ ውጪ ቁጭ ብለህ እኛን ልታስጭርስ” የሚል አስተያየት ለመጻፍ ሲያቆበቁቡ ይታየኛል። በተወሰነ ደረጃ እወነትም ውጪ ሃገር የሚገኝ ሰው “አይዟችሁ አትፍሩ በረቱ…” ብሎ ለማለት የሞራል የበላይነት እንደሌለው አምናለሁ።

“አውሬነት” – ለማንም አይበጅምና ጠንቀቅ!!

(ርዕሰ አንቀጽ)

police brutality
አሁን ከኢህአዴግ ጋር ገድለሃል አልገደልክም የሚል ክርክር የለም። ራሱ ባንደበቱ “ገድያለሁ” ብሏል። ነፍስ ማጥፋቱን አውጇል። ያልገለጸው በጸጥታና በስም እንጂ አንጋቾቹ ህይወት መቅጠፋቸውን አረጋግጧል። ግድያው በዚህ ስለማብቃቱ ማረጋገጫ አልተሰጠም። ተቃውሞውም እየቀጠለ ነው። ከዚያስ? በደም እየታጠቡ፣ ወንጀልን እያባዙና የደም ጎርፍ እየጎረፈ “ህግ” ማስከበር እስከመቼ ያስኬዳል። ያዋጣልስ? የህዝብ እንባስ እንዲሁ ከንቱ ይቀራል?
በርግጥ ህግ ማፍረስ አይደገፍም። ህግ መከበር አለበት። ከሁሉም በላይ ደግሞ ህገመንግስት ክቡር የመተዳደሪያ ዋስትና በመሆኑ ሊናድ አይገባውም። ህግን የማክበርና የማስከበር ጥያቄ አይለያዩም። ኢህአዴግ እንዳሻው የሚምልበትን ህገ መንግሥት እየጨፈላለቀና እየጎራረደ ሌሎች ህግ እንዲያከብሩ መጠየቅ ለምዶበታል። ሰዎች መብታቸውን እንዲለማመዱ አይወድም። ይህ ችግሩ በደም የታጠበ፣ የደም እዳ ያለበት፣ ታሪኩ ሁሉ ከደም ጋር የተሳሰረ እንዲሆን አድርጎታል። እስኪ ወደ ዛሬው ጉዳይ እናምራ!
አልታደልንም
ህዝብን የሚያከብር፣ ለህዝብ ቅድሚያ የሚሰጥ፣ በህዝብ የሚምል፣ ህዝብ ውስጥ የሚኖር፣ ህዝብ እውቅና የሰጠው፣ ህዝብ የሚያምነው፣ ሲፈልግ የሚቀጣው፣ ሲፈልግ የሚያሞግሰው አስተዳደር አጋጥሞን አያውቅም። የቀደመውን ኮንኖ የሚመጣው ከቀደመው የማይሻል፣ ደም የጠማው፣ ጠመንጃ አምላኩ የሆነ አገዛዝ ነው። አገሪቱም፣ ትውልዱም፣ የወደፊቱ እንግዳ ዘርም ሁሉም በስህተት ቅብብል በርግማን ይኖራሉ። ነፍጠኛ፣ ትምክተኛ፣ ጎጠኛ፣ ጠባብ፣ ኪራይ ሰብሳቢ፣ አንጃ … ቃላት እንደ ፋብሪካ ምርት እየተፈበረኩልን ስንሰዳደብ እንኖራለን። የሁሉም አስተሳሰብ አንድ ብቻ ነው – የራሱን ህልውና ለማስፈን የሚቃወሙትን ሁሉ መደምሰስ! “በጠላቶቻችን መቃብር ላይ …” የሚለው መፈክር ደርግ ቢለውም የራሱ በማድረግ አንግቦ የሚዞረው ግን እጅግ በርካታ ነው፡

ኦሮሚያ ካለቀሰች በኋላ – ህዝብ ሃሳቡን ሊጠየቅ ነው

የኢህአዴግ ቴሌቪዥን የቅስቀሳ ዘመቻ ጀመረ

mothers
በአምቦ ህዝብ አዝኗል። የሟቾች ቁጥር ከ22 በላይ እንደሆነ ይገመታል። በድፍን ኦሮሚያ ከ36 ሰዎች በላይ ተገድለዋል የሚሉ መረጃዎች አሉ። ኢህአዴግ ባወጣው መግለጫ 11 ሰዎች መሞታቸውን አምኗል። ታዛቢዎች እንደሚሉት ኦሮሚያ እያነባች ነው። ህዝብ ለቅሶ ከተቀመጠ በኋላ ኢህአዴግ በቴሌቪዥን ቅስቀሳ ጀመረ።
አርብ ሚያዚያ 24፤2006 (2/05/2014) ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም በትዊተር ባሰራጩት መረጃ በጉዳዩ ዙሪያ ህዝብ ሃሳቡን እንደሚጠየቅ አመላክተዋል። የዚሁ መነሻ እንደሆነ የተነገረለት የቅስቀሳ ዘመቻ ዛሬ በቴሌቪዥን ተላልፏል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ አቶ ኩማ የድንበር ጉዳይ እንደማይነሳ በመጥቀስ ተቃዋሚዎችን ወቅሰዋል።
ኦሮሚያን ልዩ ዞን ከአዲስ አበባ ጋር ያዋሀደው አዲሱ ማስተር ፕላን ተግባራዊ እንዲሆን እንቅስቃሴ መጀመሩን ተከትሎ በክልሉ ከተካሄዱት ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፎች የአምቦው በጉልህነቱ ይጠቀሳል። አምቦ ነዋሪው ግልብጥ ብሎ በመውጣት ተማሪዎችን ተቀላቅሏል። ኢህአዴግ ባወጣው መግለጫ “… በአምቦ ዩኒቨርስቲ የተቀሰቀሰው ሁከት ወደ ከተማ በመዝለቁ እስካሁን ባለው መረጃ መሰረት በአምቦና ቶኬኩታዮ ከተሞች የሰባት ሰዎች ህይወት ያለፈ ሲሆን ባንኩን ጨምሮ በበርካታ የመንግስትና የሀዝብንብረት ላይ ጉዳት ደርሷል” በማለት ግድያውን ከንብረት ውድመት ጋር ለማያያዝ ሞክሯል። በመደ ወላቡ ሶስት ሰዎች መገደላቸውን፣ በሌላም በኩል “በሃሮማያ ዩኒቨርሲቲ ለጊዜው ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች በሰላም የእግርኳስ ጨዋታ በቴሌቪዥን በመከታተል ላይ በነበሩ ተማሪዎች ላይ በተወረወረ ፈንጂ ወደ70 ያህል ተማሪዎች የመቁሰል አደጋ የደረሰባቸው ሲሆን የአንድ ተማሪ ህይወት ማለፉ ተረጋግጧል” ሲል በህይወት ላይ የደረሰውን ጉዳት አስታውቋል።

Thursday, May 1, 2014

በኦሮሚያ የተጀመረው ተቃውሞ መካረረ ስጋት ፈጥሯል


ኦህዴድ የተከፋፈለ አቋም ይዟል፤ ኢህአዴግ ጉልበት መርጧል

demo
በኦሮሚያ የተለያዩ ከተሞች የተቃውሞ ድምጽ ለማሰማት በሞከሩና ተቃውሟቸውን ለመግለጽ ሰልፍ በወጡ ወገኖች ላይ አገዛዙ የ”ከፋ” ነው የተባለ ሃይል መጠቀሙ ተሰማ። ቁጥራቸው በውል የማይታወቅ ታስረዋል። ለተቃውሞ መነሻ በሆነው አዲሱ የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ላይ ኦህአዴድ ተመሳሳይ አቋም መያዝ አልቻለም። ችግሩን በሰላማዊ መንገድ መፍታት ያልቻለው ኢህአዴግ ጉልበት መምረጡ አገሪቱ ውስጥ ካለው የተከማቸ ብሶቶች ጋር ተዳምሮ አለመረጋጋቱን ያሰፋዋል የሚል ስጋት አለ።
ከኦሮሚያ ክልል አስተዳደር የጎልጉል ምንጮች እንዳሉት በአቀራረቡ ቢለያይም ከተለያዩ ሚዲያዎች የሚሰሙት ዜናዎች ሊስተባበሉ የሚችሉ አይደሉም። በታችኛው እርከን የሚገኙትን ጨምሮ የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች፣ የዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ በጥቅሉ፣ ገሃድ አይውጣ እንጂ በመዋቅር ውስጥ ያሉ ሰራተኞችና ካድሬዎች የተቃውሞው ተሳታፊና ደጋፊ መሆናቸውን ክልሉም ሆነ ኢህአዴግ አረጋግጠዋል።
የአዲስ አበባ አዲሱ ማስተር ፕላን በዙሪያዋ ያሉትን ስድስት የኦሮሚያን ከተሞችና ስድስት የገጠር ቀበሌዎች የተካተቱበት መሆኑ ያስነሳው ተቃውሞ ቀደም ሲል በክልሉ በምክር ቤት ደረጀ በካድሬዎች ተቃውሞ አጋጠመው። ይህንኑ ተከትሎ ከሳምንት በፊት በአንዳንድ የትምህርት ተቋማት ብልጭ ድርግም ሲል የነበረው ተቃውሞ እየጠነከረ መጣ። የክልሉ የጎልጉል ምንጭ “ተቃውሞው እንደሚጨምር፣ ካድሬውም የተቃውሞው ስውር አጋር እንደሆነ፣ በመረጃ ትንተና አስቀድሞ ይታወቅ ነበር። በዚሁ መሰረት አስቀድሞ አመጹን ማምከን ካልተቻለ የማያዳግም ርምጃ እንዲወሰድ ለፌዴራልና ለመከላከያ አባላት መመሪያ ተሰጥቷል”።