Friday, December 27, 2013

በከፊቾ ዞን የጽላት ዝርፊያና ቀበኞቹ


"ባለሃብቶች በእድሳት ስም ቤተ መቅደስ ዘልቀው ጽላት ይቀይራሉ"

tabot


በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች ክልል በከፊቾ ዞን በጥንታዊ አድባራት ጽላት መዘረፉን እናውቃለን ያሉ ለጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ ገለጹ። የዜናው ምንጮች የዞኑ አገረ ስብከት በዞኑ በሚገኙ አድባራት ላይ ምርመራ እንዲያካሂድ ጠይቀዋል። ዝርፊያውን የሚያካሂዱት “ባለሃብቶች” መቀመጫቸውን አዲስ አበባና ጅማ ከተማ ያደረጉ የክልሉ ተወላጆች መሆናቸውን አስታውቀዋል።
ነዋሪነታቸው ቦንጋና ጊምቦ እንደሆነ የሚገልጹት የዜናው ምንጮች “ቀበኞች” በማለት የሚጠሯቸውን የጽላት ዘራፊዎች የዝርፊያ ስልት ተናግረዋል። በመጀመሪያ እድሜ ጠገብ የሆኑትን አድባራት ይለያሉ። በቃፊሮቻቸው አማካይነት መረባቸውን ዘርግተው ሰዎችን ያጠምዳሉ። ህዝበ ክርስቲያን በሚሰበሰብበት ወቅትና ዓመታዊ የበዓላትን ቀን መርጠው በርዳታና በእድሳት ስም ውዳሴ ይቀበላሉ።
በዞኑ የሚገኙት አቢያተ ክርስቲያናት እድሜ ጠገብ በመሆናቸው በርካታ ጥንታዊ ቅርስም እንዳላቸው የሚጠቁሙት ክፍሎች “ያረጁትን አድባራት እናድሳለን በማለት ጥቁር ለምዳቸውን ለብሰው መቅደስ ውስጥ ይዘልቃሉ” በማለት የዝርፊያው ድራማ እንዴት እንደሚከናወን ያስረዳሉ።
ለሃይማኖታቸው የቀኑና የታመኑ የቤተ መቅደስ ጠባቂዎችና አገልጋዮች ሲያጋጥሟቸው መቅደስ ውስጥ ተመላልሰው በሚሰበስቡት መረጃ መሰረት አብረቅራቂ ሃሰተኛ ጽላት በመተካት ዝርፊያ እንደሚካሂዱ፣ ለዝርፊያ የሚመችና ስብናው የወደቀ አገልጋይ ሲያገኙም በግልጽ ያሻቸውን አድርገው ስርቆቱን እንደሚፈጽሙ የዜናው ሰዎች ያስረዳሉ።

Tuesday, December 24, 2013

ከአቶ አያሌው መነሳት ጀርባ የአቶ ደመቀ ሚና


"የቆየ ቁጭትና ቁርሾ ነው"

ayalew n demeke


በአማራ ክልል የተካሄደውን ሹም ሽር ተከትሎ የተሰጠው ሹመትና የሹም ሽሩ አካሄድ መነጋጋሪያ ሆነ። “በቃኝ አሉ የተባሉትን ባለስልጣን አውርዶ እንደገና መሾም የተነቃበት የህወሃት የማረጋጊያ ጨዋታ ነች” ሲሉ ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ ተናገሩ። በሹም ሽሩ የአቶ ደመቀ መኮንን እጅ እንዳለበትና መንስዔውም “የቆየ ቁጭትና ቁርሾ” እንደሆነ ተጠቆመ።
የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አያሌው ጎበዜ ከመንበራቸው እንዲነሱ ተደርጓል። የመንግስት ልሳን መገናኛዎች እንዳመለከቱት አቶ አያሌው ከሃላፊነታቸው የተነሱት ታህሳስ 9/2006 በተጠራ አስቸኳይ የክልሉ ጉባኤ ነው። አዲስ ሹመት ያስፈለገው አቶ አያሌው ባቀረቡት “የመተካካት” ጥያቄ እንደሆነም ተመልክቷል። ምትካቸው የነበሩት አቶ ገዱ አንዳርጋቸው የክልሉ ፕሬዚዳንት ሆነዋል።
አቶ ገዱ ፕሬዚዳንትነታቸው በጉባኤ ተወስኖ ይፋ ከመደረጉ ጎን ለጎን ዜና የሆነው የሳቸው ሹመት ሳይሆን የአቶ አያሌው ስልጣናቸውን በፍላጎታቸው መልቀቃቸው ነው። አቶ አያሌው የ”በቃኝ” ጥያቄ ማቅረባቸው ከተሰማ ብዙ የቆየ ቢሆንም አሁን አስቸኳይ ጉባኤ ተጠርቶ የተወሰነበት ምክንያት ዜናውን አነጋጋሪ ያደረገው ጉዳይ ነው።
የአቶ አያሌው ከሃላፊነታቸው መነሳት ከግራና ቀኝ መነጋገሪያ በሆነ ማግስት ኢህአዴግ የሙሉ አምባሳደርነት ሹመት እንደሰጣቸው ይፋ መደረጉም ሌላ ግርምት ፈጥሯል። በ”መተካካት” ሰበብ ከስልጣን ተነሱ የተባሉት አቶ አያሌው “ባለሙሉ ስልጣን” አምባሳደር ሆነው መሾማቸው ደግሞ የሹም ሽር ተውኔቱን “ኮሜዲ” አሰኝቶታል ያሉና በማህበራዊ ድረገጾች መዝናኛ ያደረጉት ጥቂት አይደሉም።

Wednesday, December 11, 2013

በቃ! በለን አምላክ (say us enough! O’ God)



(ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው)

prayer1


ያ የምትወደው ፤ ያ የምታሞካሸው
ልጆቸና ሕዝቤ ፤ እያልክ ያከበርከው
መከራ አፈናቅሎት ፤ ከሀገሩ ከቀየው
ከአሕዛብ ደጅ ወድቆ ፤ ግፍ ሰቆቃ ቆላው፡፡
የጭንቅን ልክ ዓየ ፤ ሞት በዓይነት ቆጠረ
የሰቆቃን ጣራ ፤ ከፍ ብሎ በረረ
ሞትን ተላመደ ፤ ንቆም ተዳፈረ
በእሱ እየተበላ ፤ በእሱ ላይ ፎከረ
የአውሮችን አውሬነት ፤ ተበልቶ አጋለጠ
ድብቁን አወጣ ፤ ነፍሱን ለሀቅ ሰጠ፡፡

Sunday, December 8, 2013

በመዲናዋ ምስጢራዊ የወሲብ ገበያ ደርቷል


(አብዛኛዎቹ "የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች" አረቦች ናቸው)

p


  • የትላልቅ ድርጅቶች ፀሃፊዎች፣ ሞዴሎችና ተዋናዮች አሉበት
  • ድንግልናን በ10ሺ ብር የሚያሻሽጡ ደላሎች ሞልተዋል
  • የከተማዋ ቱባ ባለሃብቶች “የአገልግሎቱ” ተጠቃሚዎች ናቸው
ሲኤምሲ ሣሚት ማዞሪያ አካባቢ ካሉት ዘመናዊ ቪላ ቤቶች በአንደኛው 12ሺ ብር ወርሃዊ ኪራይ እየከፈለች ትኖራለች፡፡ የምታሽከረክረው ኤክስኪዩቲቭ ቶዮታ፣ በየዕለቱ የምትቀያይራቸው እጅግ ውድ ዋጋ ያላቸው አልባሳቶቿና በየመዝናኛ ሥፍራው የምትመዘው ረብጣ ብር የተንደላቀቀ ኑሮ እንደምትመራ ይመሰክራሉ፡፡ በሳምንቱ መጨረሻ ቀናትና መዲናችን አለማቀፋዊ ስብሰባዎችን በምናስተናግድበት ጊዜያት እሷን ፈልጐ ማግኘት የማይታሰብ ነው፡፡
ቦሌ ፍሬንድሽፕ ሕንፃ ላይ በከፈተችው ቡቲክ የምታገኘው ገቢ ይሄን ያህል ሊያዝናናት እንደማይችል የታወቀ ነው፡፡ ገቢ ወጪዋን አጥብቃ የማትቆጣጠርበትን ይህንኑ ቡቲኳን ታናሽ እህቷ ትውልበታለች፡፡ እሷም አልፎ አልፎ “ሥራ” በማይኖራት ጊዜ ብቅ እያለች ትጐበኘዋለች፡፡ ታናሽ እህቷ ቤተሰቡን ሁሉ ቀጥ አድርጋ የምታስተዳድረው እህቷ፤ ስለምትሰራው ምስጢራዊ ሥራ አንዳችም የምታውቀው ነገር ያለ አይመስልም፡፡ እሷ የምታውቀው ከተለያዩ የውጪ አገር ሰዎች ጋር የአየር ባየር ንግድ እንደምታጧጡፍና በየጊዜው ወደተለያዩ አገራት ለሥራ ጉዳይ እንደምትመላለስ ብቻ ነው። ሥራዋ የግል ሚስጢሯ ብቻ ሆኖ እንዲኖር የምትፈልገው ህሊና (ስሟ ለዚህ ጽሑፍ የተቀየረ) ይህንን የእህቷን እምነት አጥብቃ ትፈልገዋለች። በተለያዩ የመዝናኛ ሥፍራዎች ከአገር ውስጥና ከውጭ አገር ደንበኞቿ ጋር እየከረመች በመጣች ቁጥር ለእህቷ የተለያዩ ቸኮሌቶችና ስጦታዎችን እየያዘችላት መምጣቷ የእህቷን እምነት አጠናክሮላታል፡፡
እሷ “ቢዝነስ” ብላ የገባችበት ህይወት ገቢ፣ እህቷ ቀኑን ሙሉ ተገትራ ከምትውልበት ቡቲክ ገቢ ጋር ሊወዳደር እንደማይችል ስለሚገባት “ሥራውን” አጥብቃ መያዙን  ትፈልገዋለች፡፡ የንግድ ፍቃድ እድሣት፣ ቫት ምዝገባ፣ ሪሲት ማሽን፣ ቀረጥና ታክስ የሚሉ ዝባዝንኬዎች የሌሉበት፣ “ራስን እያስደሰቱ ሌሎችን በማዝናናት” በቀን የሚገኝ ረብጣ ብር ከቡቲኳ ወርሃዊ ገቢ በእጅጉ ይልቃል። ተፈጥሮ ያደላትን ውበትና ማራኪ ቁመናዋን ለገበያ እያቀረቡ በተሻለ ገንዘብ ለመሸጥና ጠቀም ያለ የኮሚሽን ገንዘብ ለመቀበል አሰፍስፈው የሚጠባበቁ ደላላ ደንበኞች አሏት፡፡ ለዚህ ተግባር ብቻ የምትጠቀምበት የሞባይል ስልኳ ሲጮህ “ሥራ” እንደተገኘ እርግጠኛ ትሆናለች። ቅያሬ ልብሶችን የምትይዘበትና ሁሌም ለጉዞ ዝግጁ የምታደርገውን ቦርሣዋን አንጠልጥላ ውልቅ ነው። አብዛኛውን ጊዜ ወደ ሥራ የምትንቀሳቀሰው በደላሎቹ መኪና ነው። ደላላው እሷን ካለችበት ወስዶ ወደምትፈለግበት፣ ሥራዋን ስትጨርስ ደግሞ ወደነበረችበት የመመለስ ግዴታ አለበት፡፡

Friday, December 6, 2013

ኢትዮጵያን በሙስና ከሚታወቁ የዓለም አገሮች ተርታ ያሰለፈው ሪፖርት ይፋ ሆነ


corruption index


ትናንት ኅዳር 24 ቀን 2006 ዓ.ም. በመላው ዓለም ይፋ የሆነው የትራንስፓረንሲ ኢንተርናሽናል ተቋም የሙስና አመላካች ሪፖርት፣ ኢትዮጵያ ከሙስና ጽዱነት ተርታ ውጭ ከሆኑና በሙስና ተግባር በከፍተኛ ደረጃ ከሚፈረጁ አገሮች አንዷ ሆና መገኘቷን ይፋ አደረገ፡፡
ሪፖርቱ በሚከተለው የሙስና መለኪያ ሚዛን መሠረት፣ ከሙስና ጽዱ የሚባሉ አገሮች ከዘጠና እስከ መቶ ነጠብ የሚያገኙት ናቸው፡፡ በአንፃሩ ከፍተኛ ሙስና ተንሰራፍቶባቸዋል፣ የሙስና ጎሬ ሆነዋል ተብለው የሚታሰቡ አገሮች ደግሞ ከመለኪያው ከ50 በመቶ በታች የሚያስመዘግቡት ናቸው፡፡ በመንግሥት ተቋሞች ውስጥ ከፍተኛ ሙስና ተንሰራፍቶባቸዋል ተብለው ከተለዩት ውስጥ ኢትዮጵያ 33 ከመቶ የመለኪያውን ነጥብ በማስመዝገብ ከከፍተኛ ሙስኞች ተርታ እንደምትሰለፍ የትራንስፓረንሲ ኢንተርናሽናል ሪፖርት ይፋ አድርጓል፡፡ ከ177 አገሮች ውስጥ 111ኛውን ደረጃ መያዟም በሪፖርቱ ይፋ ሆኗል፡፡
ኢትዮጵያን ጨምሮ መላው አገሮች ለሙስና ተጋላጭነት ከሚለኩባቸው መመዘኛዎች መካከል፣ የፕሬስ ነፃነት፣ የተጠያቂነትና የሰዎች የመደመጥ መብት፣ የፍትሕ አካላት ከተፅዕኖ ነፃ መሆን፣ የሕግ የበላይነት፣ የሰብዓዊ ልማት መለኪያና ሌሎችም ጠቋሚዎች እንደሚካተቱ ትራንስፓረንሲ ኢንተርናሽናል በድረ ገጹ ይፋ አመላክቷል፡፡

ኢትዮጵያን በሙስና ከሚታወቁ የዓለም አገሮች ተርታ ያሰለፈው ሪፖርት ይፋ ሆነ


corruption index


ትናንት ኅዳር 24 ቀን 2006 ዓ.ም. በመላው ዓለም ይፋ የሆነው የትራንስፓረንሲ ኢንተርናሽናል ተቋም የሙስና አመላካች ሪፖርት፣ ኢትዮጵያ ከሙስና ጽዱነት ተርታ ውጭ ከሆኑና በሙስና ተግባር በከፍተኛ ደረጃ ከሚፈረጁ አገሮች አንዷ ሆና መገኘቷን ይፋ አደረገ፡፡
ሪፖርቱ በሚከተለው የሙስና መለኪያ ሚዛን መሠረት፣ ከሙስና ጽዱ የሚባሉ አገሮች ከዘጠና እስከ መቶ ነጠብ የሚያገኙት ናቸው፡፡ በአንፃሩ ከፍተኛ ሙስና ተንሰራፍቶባቸዋል፣ የሙስና ጎሬ ሆነዋል ተብለው የሚታሰቡ አገሮች ደግሞ ከመለኪያው ከ50 በመቶ በታች የሚያስመዘግቡት ናቸው፡፡ በመንግሥት ተቋሞች ውስጥ ከፍተኛ ሙስና ተንሰራፍቶባቸዋል ተብለው ከተለዩት ውስጥ ኢትዮጵያ 33 ከመቶ የመለኪያውን ነጥብ በማስመዝገብ ከከፍተኛ ሙስኞች ተርታ እንደምትሰለፍ የትራንስፓረንሲ ኢንተርናሽናል ሪፖርት ይፋ አድርጓል፡፡ ከ177 አገሮች ውስጥ 111ኛውን ደረጃ መያዟም በሪፖርቱ ይፋ ሆኗል፡፡
ኢትዮጵያን ጨምሮ መላው አገሮች ለሙስና ተጋላጭነት ከሚለኩባቸው መመዘኛዎች መካከል፣ የፕሬስ ነፃነት፣ የተጠያቂነትና የሰዎች የመደመጥ መብት፣ የፍትሕ አካላት ከተፅዕኖ ነፃ መሆን፣ የሕግ የበላይነት፣ የሰብዓዊ ልማት መለኪያና ሌሎችም ጠቋሚዎች እንደሚካተቱ ትራንስፓረንሲ ኢንተርናሽናል በድረ ገጹ ይፋ አመላክቷል፡፡

Wednesday, December 4, 2013

ከሰማይ የራቀችው ምድር ከምድሪቱ የራቀው ሰማይ


(ሠዓሊ አምሣሉ ገ/ኪዳን አርጋው)

ethio saudi 16


ከጥቂት ጊዜያት ወዲህ ‹‹መንግሥት›› ስደትን በተመለከተ ከዚህ ቀደም ባልነበረው ትኩረት ያስቆጨውና ያሳሰበው መስሎ በመታየት በሕዝብ የብዙኃን መገናኛዎች የተለያዩ ዲስኩሮችን እያደረገ ይገኛል ፡፡
ሲጀመር ገዥው ፓርቲ (ቡድን)  የዜጎችን ስደት በተመለከተ ማንነቱን አሳምሮ ለሚያውቀው ሕዝብ ምንም የማለት የሞራል (የግብረ-ገብ) ብቃት ጨርሶ አልነበረውም፡፡ ራቅ ካለው ታሪኩ እስከ ቀረብ ካለው ከዚያም እስከአሁን ካለው ታሪኩ አሁን ባለበት ሁኔታም ተስፋ የሚሰጥ ምንም ነገር ባለመኖሩ ነገም ከሚኖረው ታሪኩ ስንመለከት ይሄንን ክስ የሚያስተባብል ሆኖ አናገኘውም ፡፡ ከዚህ አንጻር ትኩረቱን በጣም አጥቦ በአራቱም አቅጣጫዎች በእግር እግራቸው ወደ አመራቸው በሚሰደዱ ታዳጊ ሕፃናትና ወጣቶች ላይ ማድረጉ በቦሌ በኩል በተለያየ ጫና ፣እንግልትና ውክቢያ ሳይወዱ ሀገራቸውን ጥለው በሚሰደዱት፤ ሕዝቡ በሌለው አቅም አስተምሮ ላቅ ላለ ደረጃ ያበቃቸው ፤በሀገርና በሕዝብ ጉዳይ ላይ ንቁ ተሳታፊ የሆኑ ውድ ልጆቹ ምሁራን ላይ አለማድረጉ የቦሌዎቹ ተሰዳጆች የማይጎዳ የእግረኞቹ የሚጎዳ የሚያጎል ነው ብለው አስበው ሳይሆን ስለስደት ማውራት ካለባቸው የርእሰ መሬያቸው ጠባብ አማራጭ እነሱው በመሆናቸው ብቻ ነው፡፡
ወደ ተሰዳጅ ወገኖቻችን ስመለስ ይሄኛው ወይም ያኛው የኅብረተሰብ ክፍል መሰደዱ የሚጎዳና የማይጎዳ የሚል ሒሳብ ውስጥ ከተገባ ብዙ ነገር አለ ሲጀመርም እዚህ ስሌት ውስጥ ልንገባ አይገባንም፡፡ ዜጎች ተማሩም አልተማሩ ዜጎች በመሆናቸው ጥበቃና እንክብካቤ ያስፈልጋቸዋል፡፡ ያልተማሩም ቢሆኑ እነሱን የማይተካ ሀገር የምትጠብቅባቸው ለሀገር የሚያበረክቱት ብዙ ነገር መኖሩ አይቀርምና ፡፡ የሚያሳትፋቸውና የሚጠቀምባቸው ዓይናማ መንግሥት ካገኙ፡፡ እናም ‹‹መንግሥት›› በቦሌ በኩል ለሚሰደዱት ሥልጣን ከያዘ ማግሥት ጀምሮ (ሀገሪቱ የተማሩ ብርቅዬ ዜጎቿን ስታጣ የሚደርስባት ከባድ ጉዳትና የምታጣው ጥቅም ኢምንት እንኳን ሳያሳስበው 42 ሲቀነስ 1 በአብዛኛው ዶክተሮችን ፕሮፌሰሮች የሚበዙበትን የምሁራንን ቡድን በአንድ ጊዜ አባሮ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲን (መካነ-ትምህርትን) ወና ካደረገበት እስከ 1997ዓ.ምሕረቱ ምርጫ ማግስት ምሁራን የፖለቲካ ፓርቲ (የእምነተ አስተዳደር ቡድን) መሥርተው አሸናፊ ከሆኑ በኋላ ሥልጣን ለማስረከብ ባለመፍቀዱ ከሕዝቡ ያገኙትን ድምፅ እንኳን ባይሆን ከተሳትፎ በዘለለ የወሳኝነት ሥልጣን አጋርቶ አስተዋጽኦዋቸውን እንዲያበረክቱ ማድረጉ ለሀገር ሳይሆን ለቡድኑ ስላልተስማማው ብቻችንን ዐወቅንበትም አላወቅንበት፣ ገባንም አልገባን እስክናልፍ ድረስ ብቻችንን እንደመሰለን እያባከንንም፣ እያበላሸንም፣ እያጨማለቅንም እንማርበታለን እንጅ እናንተን ከጎናችን አስቀምጠን አንጋለጥም፣ አንሸማቀቅም፣ አንዋረድም በሚል ደንቆሮና ጠባብ አስተሳሰብ ሀገር ይረቡኛል ብላ በድሀ ሕዝቧ አቅም ያስተማረቻቸው የምትጠብቅባቸውንም ለማበርከት ንቁ ተሳታፊ ሆነው ለተፍጨረጨሩት ምሁራን የስደት ግብዥ በማቅረብ ተገደው እንዲሰደዱ እንዳደረገና ምሁራንን የሚያስጠላ ከባድ በሽታ እንዳለበት በግልጽ በአደባባይ ተናግሯልና፡፡

ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን ወዳገራቸው የመመለስ ግዴታው የህወሃት/ኢህአዴግ ነው!


ኦባንግ ለቴድሮስ መልክት ላኩ

obang and tedros


ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን)
ኅዳር 23፣ 2006 ዓም
ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን ወዳገራቸው የመመለስ ግዴታው የህወሃት/ኢህአዴግ ነው!
ግልጽ ደብዳቤ ለሚኒስትር ቴድሮስ አድሃኖም ገ/የሱስ
____________________________________________________________
ለዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ገብረየሱስ
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር
አዲስ አበባ
ኢትዮጵያ
ሚኒስትር ቴድሮስ አድሃኖም፤
ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) ኢትዮጵያውያንን በቀለም፣ በዘር፣ በጎሣ፣ በቋንቋ፣ በጾታ፣ በክልል፣ ወዘተ ሳይከፋፍል በየትኛውም የዓለም ክፍል (ኢትዮጵያንም) ጨምሮ የሚደርስባቸውን ማንኛውም ዓይነት ማኅበራዊ ኢፍትሃዊነት ለመከላከል፣ ለማስቆም፣ ለማጋለጥ፣ ወዘተ እና ባሉበትም ቦታ ሁሉ ከፈጣሪ የተሰጣቸውን መብት ለማስጠበቅ የቆመ ድርጅት ነው፡፡ ሆኖም ግን እኔ ኦባንግ ሜቶ ይህንን ደብዳቤ የምጽፍልዎ የዚህ ንቅናቄ ዋና ዳይሬክተር እንደመሆኔ ብቻ ሳይሆን የውቢቷ ኢትዮጵያ የደም ውጤት በመሆኔ እንደ አንድ ወንድም በመሆንም ጭምር ነው፡፡
ይህንን ደብዳቤ የምጽፍልዎ እርስዎንም ሆነ እርስዎ አባል የሆኑለትን የህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) እና ኢህአዴግን ለመለመን ወይም ለማስደሰት ሳይሆን በሳዑዲ አረቢያና በሌሎች የመካከለኛው ምስራቅ አገራት ውስጥ በኢትዮጵያዊ ሕዝቤ ላይ እየደረሰ ያለውን ከሰብዓዊነት ውጪ የሆነ አሰቃቂ ተግባር የማስቆምና አስቸኳይ መፍትሔ የማምጣት ግዴታ ህወሓት/ኢህአዴግ እንዳለበት ለማስታወቅ ነው፡፡
በመሆኑም እኔና እርስዎ የፖለቲካም ሆነ የአስተሳሰብ ልዩነት እንዳለን ግልጽ ቢሆንም አገር “እየመራሁ ነኝ” የሚለው ህወሃት/ኢህአዴግ የኃላፊነት ቦታ ላይ ያስቀመጥዎት እርስዎን በመሆኑ ይህ ጉዳይ በቀጥታ ከሚመለከታቸው ሰዎች አንዱ ነዎት፡፡ ከሥልጣኑም ጋር አብሮ ከፍተኛ የሆነ ኃላፊነት ይመጣል፤ ይህም በሁሉም ዘንድ ተጠያቂ ያደርጋል፡፡ ህወሃት/ኢህአዴግም የሕዝብ ውክልና ባይኖረውም እንኳን ለእያንዳንዱ ነገር በቀጥታ ተጠያቂ ነው፡፡ ስለሆነም በዚህ ደብዳቤ ላይ የማሰፍራቸው ነጥቦች እርስዎንም ሆነ ህወሃት/ኢህአዴግን የሚያስደስት ላይሆን ይችላል፡፡ በተለይ በሳዑዲና በሌሎች የመካከለኛ ምስራቅ አገራት በወገኖቻችን ላይ የሚደርሰው ግፍ በዓለም ዙሪያ ተበትነው በሚገኙ ኢትዮጵያውያን ላይ ያሳረፈው ተጽዕኖና ኃፍረት እንዲሁም ቁጭት ይህ ነው ተብሎ የሚነገር እንዳልሆነ ህወሃት/ኢህአዴግ በሚከተለው የመረጃ ማፈን ፖሊሲ የኢትዮጵያ ሕዝብ መመልከት ባይችልም እርስዎና አብሮዎት ያሉት ሳታዩት ያለፋችሁት ጉዳይ አይደለም፡፡ ይህንን ደብዳቤ የምጽፍልዎ መረጃን በመመርኮዝ በመሆኑ ለምጽፈው እያንዳንዱ ነገር ሙሉ ኃላፊነት በመውሰድ መሆኑን አስቀድሜ ላስገነዝብዎት እወዳለሁ፡፡
ባለፉት ሳምንታት በ30 አገራት የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በ80 ከተሞች ውስጥ ሰላማዊ ሰልፍ በማድረግ በአንድ ድምጽ በሳዑዲ አረቢያ በኢትዮጵያውያን ላይ እየደረሰ ያለው ግፍ ይቁም በማለት ቁጣችንን ስናሰማ ቆይተናል፤ አሁንም ቀጥሏል፡፡ ይህ እየተደረገ ያለበት ምክንያትም በሳዑዲ ያሉት ኢትዮጵያውያን ከአንድ የተወሰነ ክልል ወይም የአንድ ጎሣ ቋንቋ ተናጋሪ ወይም የተወሰነ የኅብረተሰብ ክፍል ወዘተ ስለሆኑ ሳይሆን በቅድሚያ ሰብዓዊ ፍጡራን ስለሆኑ ከዚያም በላይ የእኛንም ኢትዮጵያዊነት ማንነትና ክብር የሚነካ በመሆኑ ነው፡፡ታዲያ ለዚህ ቀውስ መፍትሔው ለመንገድ ሥራ እንደሚገኝ ድጎማ ከዓለም ባንክ ወይም ከተባበሩት መንግሥታት ወይም ከሌሎች ለጋስ አገራት ወይም ደግሞ እንደ “ህዳሴ ግድብ ቦንድ” ከዳያስፖራ የሚገኝ አይደለም፡፡ በተጻጻሪው ለዚህ ቀውስ ዋንኛውን ኃላፊነት የሚወስደውና በሳዑዲ የሚሰቃዩትን ኢትዮጵያውያንን የመታደግ ግዴታው የህወሃት/ኢህአዴግ ነው!
ይህ በኢትዮጵያውያን ላይ እየደረሰ ያለው ሰቆቃ የሁላችንንም ህልውና የነካ በመሆኑ “በእርግጥ ኢትዮጵያዊን አገር አላቸው ወይ?” ብለን እንድንጠይቅ ያደረገን ሆኗል፡፡ በተጻጻሪው ግን በህወሃት/ኢህአዴግ በኩል የሚታየው የውሳኔ አሰጣጥ እና እርምጃ አወሳሰድ አናሳነት እንዲሁም ዝግተኝት በአመራር ላይ ያሉትን ሁሉ ስለ ችግሩ ያላቸው የግንዛቤና የአመራር ደካማነት ያለአንዳች ጥያቄ በጉልህ ያሳየ ነው፡፡ እንደ እውነቱ ከሆነ ፈርጀ ብዙ ለሆነው የኢትዮጵያ ችግር ዋንኛ ተጠያቂ ህወሃት/ኢህአዴግ ቢሆንም የችግሩ አፈታት ግን ለሥራ ባልደረቦች ጊታር የመጫወት ያህል ወይም በጥቂት ቃላት ትዊተር ላይ መልዕክት የመላክ ያህል የቀለለ እንዳልሆነ እሙን ሆኗል፡፡