Thursday, August 29, 2013

ተስፋሁንን መግደል ለኢህአዴግ ተስፋ ይሆናታልን….!?


bbbተስፋሁንን መግደል ለኢህአዴግ ተስፋ ይሆናታልን….!?
አብዲሳ የብዙ ጊዜ ወዳጄ ነበር፡፡ በየገጠሩ እየዞርን በርካታ ስራ አብረን ሰርተናል፡፡ የዋህነቱ እጅግ በጣም አስገራሚ ነበር፡፡ በየክልሉ ስንዞር አበሉን የሚጨርሰው “ቸገረኝ” ላለው ሁላ መበስጠት እንደነበር አብረነው የሰራ ሁላ እርሱን የምንለይበት ባህሪው ነው፡፡ ይሄ ልጅ በአንዱ ቀን ለስራ ልንሄድ የተቀጣጠርንበት ቦታ ሆነን ስንጠብቀው ስንጠብቀው ሳይመጣ ቀረ… ስልኩን ብንደውልልት አይሰራም፡፡ ካለንበት እየተንቆራጠጥን… ወደ ሶስት ሰዓት ድረስ ዘግይተን ጠበቅነው የውሃ ሸታ ሆነብን… ምን ሆነ ብለን እየተጨነቅን እንጀራ ነውና ጉዟችንን ቀጠልን…
አብረን ስንጓዝ ከነበርነው መካከል አብዲሳን በቅጡ የምናውቀው ሰዎች “ይሄኔ አንድ የታመ ሰው አጋጥሞት ሆስፒታል ሳላደርስ አልሄድም ብሎ ነው…” ….ወይ ደግሞ “…አንዱ ገንዘብ ተቸግሮ አጋጥሞት  ምንም ሳያስቀር ገንዘቡን ሰጥቶ ወደ እኛ መምጫ ራሱ ተቸግሮ ይሆናል …” ካልሆነ ግን “…ዘራፊዎች አግኝተው ጉድ አድርገውት ሊሆን ይችላል…. እያልን መገመታችንን ተያያዝነው…
ግምታችን ሁሉ ትክክል አልነበረም፡፡
አብዲሳ በስንተኛው ጊዜ በቴሌቪዥን መስኮት መታየቱን ሰማን… በየዋህነቱ የተቸገረ በመርዳቱ የምናውቀው አብዲ “አሸባሪ” ተብሎ በመንግስት ቁጥጥር ስር ውሏል፡፡ አብዲሳ “አሻባሪ” ከተባለማ እኛ ምን ልንባል ነው… ብለን ራሳችንን እንደ ነውጠኛ የምናየው እኛ በጣም ተደነቅን!
አብዲ ወደ አምስት ወራት በማዕከላዊ፣ ወደ አምስት አመት በቃሊቲ እንዲሁም ሁለት ሶስት አመት ነው መሰለኝ በዝዋይ ማሰሪያ ቤቶች ቆይቶ ነፃ ነህ ተብሎ እስኪሰናበት ድረስ በአስር ቤቱ ውስጥ ሲደርስበት በነበረው መከራ ብዙ ጉዳት ደርሶበታል፡፡ ታድያ ከእስር ቤት ሊወጣ አካባቢ አንድ ባለስልጣን ብጤ ሰውዬ ጎብኝተውት ነበር፡፡

የእኛ “መንግስት” (ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ)


August 29, 2013

“በእያንዳንዱም መንግስት የሚያድሩ ብዙ ልዩ ልዩ ነገዶች ይኖሩ ይሆናል፡፡ ስለ ሆነ መንግስት አንዱን ነገድ አጥቅቶ ሌላውን ነገድ ለመጥቀም ሥራው አይደለም፡፡ አስተካክለን ካሰብን ዘንድ መንግስት መቆሙ ለሕዝቡ ሁሉ ጥቅም ነው፡፡ ጥረቱም ህዝቡን ሁሉ በትክክል ለመጥቀም ያልሆነ መንግስት ሊቆም አይችልም፡፡ ለአንዱ ነገድ ወይም ለጥቂት ሰዎች ብቻ ማድላት ለመንግስት የሚገባ ሥራው አይደለም” ይህንን መግቢያ የወሰድኩት በልዑል የኢትዮጵያ መንግስት አልጋ ወራሽ ተፈሪመኮንን ማተሚያ ቤት የካቲት 1 ቀን 1917 ዓ.ም ከታተመው የነጋ ድራስ ገብረ ሕይወት ባይከዳኝ‹‹መንግስትና የሕዝብ አስተዳደር›› መፅሀፍ ነው፤ ዛሬም ያለንበትን ዘመን ይዋጃልና፤ በተለይ ስለ‹‹ነገድ›› የተጠቀሰውን አርቀን ሰቅለን፣ ‹‹ለጥቂት ሰዎች ብቻ ማድላት›› የምትለዋን ሀረግ በወጉ ካጤንናት ለጊዜያችን በልክ የተሰፋች መሆኗን ለመረዳት አስቸጋሪ አይደለም፡፡
Journalist Temasegan Dasaleg
እናም የስርዓቱን የአስተዳደር ዘይቤ ያለፍርሃት አደባባይ ካዋልነው የቀድሞ ገዥዎቻችን የተጓዙበትን ጎዳና እየተከተለ መሆኑን ለመተንተን የምሁራንን ጥናት መጠበቅ ግድ አይለም፤ ምክንያቱም ለዓመታት የተመለከትነው እውነታ የሚነግረን የአመራሩን እና በዙሪያው የሠፈሩ የጥቅም ተጋሪ ግለሰቦችን ብልፅግና ታሳቢ ያደረገ፣ ከታግሎ መጣል ህግ የተቀዳ፣ የራስ ሀገርንና የራስ ሕዝብን በምርኮ ያስገበረ ፖለቲካ መንበሩን ነው፤ ገብር፣ ገብር፣ ገብር…!!
ዛሬ መንገድ ዳር ረሀብ አዙሮ የጣለው ወንድምህ ስቃይ እንደ ጥላ የሚከተልህ፤ ህፃናት በትምህርት ገበታቸው ላይ በጠኔ ተሸንፈው መመልከቱ የሰርክ አሳዛኝ ክስተት የሆነብህ ከሰው ሰራሽ ችጋር፣ ከሰው ሰራሽ የቀዬ ፍንቀላ፣ ከሰው ሰራሽ እርዛት… የመነጨ መርገምት እንጂ የሰማይ ቁጣ አይምሰልህ፤ እመነኝ መለስም ሆነ ተተኪዎቹ ስኬት አድርገው የሚሰብኩትም ይህንን ነው፤ ‹ሀገር አቀናን!› የሚሉትም ይህንን ነው፤ ሰሞኑን የሚያሰለቹህ ተረኛ ምሁራንም ‹‹ትምህርትና ጤናን በተመለከተ መለስ ‹እልል› የሚያስብል ሥራ ሰርቷል›› የሚሉህ ጣራና ግድግዳ እየቆጠሩ ነው፤ ይህ አይነቱ መደዴ ሙገሳም ለፕሮፓጋንዳ የሚሆን ሪፖርት ለማዘጋጀት ከሚረዳ ቁጥር የዘለለ አበርክቶ አንደማይኖረው አትዘንጋ፡፡

Monday, August 26, 2013

ሕወሐት በአዜብ ጉዳይ ተወጥሯል (ኢየሩሳሌም አርአያ)


August 25, 2013

ከኢየሩሳሌም አርአያ
ለስድስት አመት ኤፈርትን ሲመሩ የቆዩት ወ/ሮ አዜብ መስፍን ከሃላፊነት መነሳት ተከትሎ በሕወሐት ውስጥ ውጥረት መንገሱን ምንጮች አመለከቱ። የኤፈርት ቦርድ ሰብሳቢ በነበሩት ባለቤታቸው አቶ መለስ አማካይነት ዳይሬክተር ተደርገው አዜብ መሾማቸውን ያስታወሱት ምንጮች፣ ከመለስ ሕልፈት በኋላ ቦታውን የተረከቡት ኤርትራዊው ቴዎድሮስ ሃጎስ መሆናቸውን፣ እንዲሁም ዳይሬክተር የመሾምና የመሻር ስልጣኑ የቦርዱ መሆኑን ያስረዳሉ። አዜብ ከኤፈርት እንዲወገዱ የተደረገው ግን በነቴዎድሮስ ሃጎስ ሳይሆን ስብሃት ነጋ ባቀነባበሩት ጣልቃ ገብ ውሳኔ መሆኑን ምንጮቹ ገልፀዋል። በኤፈርት የተለያዩ ተቋማት የሚሰሩ ሰራተኞች አዜብ በመባረራቸው ደስታቸውን እየገለፁ መሆኑን የጠቆሙት ምንጮች፣ አያይዘውም ደስታቸውን በስብሰባ ጭምር ከመግለፅ ባለፈ፥ « አዜብ ከኤፈርት ጀምሮ ለፈፀሟቸው የሙስና ወንጀሎች በሕግ መጠየቅ አለባቸው» በማለት አቋም እስከ መያዝ መድረሳቸውን አስታውቀዋል። ከዚህ በስተጀርባ በበቀለኝነታቸውና የጥፋት ሴራ በማቀነባበር የሚታወቁት ስብሃት ነጋ እንዳሉበትና ከኤፈርት ስልጣናቸው ያስነሷቸውን አዜብ ከጨዋታ ውጭ ከማድረግ ባለፈ በሙስና እንዲጠየቁ በየአቅጣጫው ጫና እያሳደሩ መሆኑን ምንጮቹ አስረድተዋል። በአዜብ ተፈፀሙ ተብለው ከተነሱት የሙስና ወንጀሎች በኤፈርት ስም 200 ከባድ ተሽከርካሪዎች አቶ ነጋ ገ/እግዚያብሄር ቀረጥ ሳይከፍሉ እንዲያስገቡ ማድረጋቸውን፣ በሚሊዮን የሚገመት ቀረጥ ሊከፈልባቸው የሚገቡ የተለያዩ የሕክምና መሳሪያዎች፣ በኤፈርት ገንዘብ ሶስት መርከብ ስሚንቶ የፍራንኮ ቫሉታን ሕግ በመተላለፍ ቀረጥ ሳይከፈልበት አገር ውስጥ መግባቱ፣ ክሶች እንዲቋረጡ ትእዛዝ በመስጠት..የሚሉት በዋነኛነት መነሳታቸውን ምንጮቹ አመልክተዋል። ( አዜብ ከኤፈርት እንደሚነሱ ከዚህ ቀደም በወጡ ዘገባዎች ምንጮችን በመንተራስ መገለፁ ይታወሳል)

“የኢትዮጵያውያን ህይወት በዓረብ ሀገሮች”


የልማታዊ ጋዜጠኞች አንዝህላልነት እና የአብርሃ ደስታ እማኝነት

eth women


ባሳለፍነው ሳምንት በሳውዲ አረቢያ ግፍ ተፈጸሞባቸው ወደ ባገር ቤት የሚሸኙ እህቶች የመኖራቸው መረጃ ደረሰኝ። በተለይም በቅርብ እከታተላቸው የነበሩ አህቶች እንግልት በመጠቆም በዚው በፊስ ቡክ የማለዳ ወግ ዳሰሳየ ላይ አንድ መልዕክት አስላልፊ ነበር! መልዕክቱም ለልማታዊ የሃገር ቤት ጋዜጠኞች ሲሆን የመልዕክቱ ፍሬ ሃሳብ “የምንናገረውን ማመን መቀበል አቅቷችሁ እንደ ጠላት ከምታዩን ረቡዕ ወደ ቦሌ አየር ማረፊያ ሂዱና ከፍተኛ ግፍ ተፈጸደሞባቸው ከሳውዲ ተጠርፈው ወደ ባገር የሚገቡትን የኮንትራት ሰራተኞችን ተመልክቱ !” የሚል ነበር።
ንቁ እዝነ ልቦንና ያልታደሉት ልማታዊ ጋዜጠኞች በቦታው ሄደው ከቤሩት የተመለሱትን ሻንጣ የደረደሩ እህቶች በቴሌቪዥኑ መስኮት ብልጭ አድርገው ከማጥፋታቸው ባለፈ ከሳውዲ ያለጫማና የረባ ልብስ ተደብድበውና ተደፍረው የተመለሱትን ግፉአን ሊያሳዩን እንኳ አልፈቀዱም! ጋዜጠኞቻችን አልተሳሳቱም!!! የተሳሳትኩት እኔ ነኝ!!! ያን ሰሞን “ስደት ይቅር” ምንቴስ ሰፊ ሽፋን በየሚዲያው እየሰጡ፣ የደበቁትን መከራችን እያሳዩ እያሉ ህዝበ አዳም፣ ሃገሬውን ሲያስለቅሱን የከረሙት ወደ ነፍሳቸው ተመልሰዋል ብየ በማሰቤ ስህተቱ የእኔ ግምት ነው!!! ጉዳታችን እዩት ቀሪው እንዲማርበት ፣ ሃላፊዎቻችን ይዩትና ወደ ዘነጉት የዜጎች ጉዳይ ያተኩሩ ዘንድ የተገፊ ግፉአኑን ጉዳይ ተከታትየ መጠቆሜ በአደባባይ ቃል የገቡትን ይፈጽማሉ ብየ በማሰቤ የተሳሳትኩት እኔ ነኝ!!! ስህተቴ አንድና አንድ ነው!!! የአረብ ሃገሩን የስደት መከራ የሚፈልጉት ለፕሮፖጋንዳ እንጅ ቀሪውን ማስተማርን እንደልሆነ አለማሰቤ ነው ስህተቴ!
በእንዝህላል ልማታዊ ጋዜጠኞቻችን አዝኘም ብቻ ሳይሆን አፍሬ ዝም ማለቴ ግን እውነት ነው! ዛሬ ማለዳ ግን መልካም መረጃም የሚየ ስፈነጥዝ ባይሆንም መረጃው በመሰራጨቱ የተደሰትኩበትን መጣጥፍ ተመለከትኩ። ሮብ ነሓሴ 15, 2005 ዓም ከአረብ ሃገር ወደ ሃገር የገቡትን እህቶች አብርሃ ደስታ አግኝቷ እንዳነጋገራቸው በማህበራዊ ድህረ ገጽ ካስተላለፈው መልዕክት ለመረዳት በመቻሌ ደስ አለኝ! በገዥው የኢህአዴግ መንግስት አስተዳደር ላይ በተለይም ስለ ህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ከመቀሌ ሆኖ በሚያሰራጫቸው የሰሉ ሚዛናዊ ሂሶች ተወዳጅነትን እያተረፈ የመጣው አብርሃ ድስታ ግፉአን እህቶቸችን ቦሌ አየር ማረፊያ አግኝቷቸው ያየውን የሰማውን እጥር ምጥን ባለው የለመድነው መረጃ አቀባበል እንካችሁ ብሎናል። የአብርሃ እማኝነት አስደስቶኝ እኔም ለዛሬ ወግ ዳሰሳ አበቃሁት!

The Totolamo-Kofele blood bath victims named, death toll still climbing.


(Getahune Bekele-South Africa)

Totolamo-Kofele


“Wolahi, Wolahi…” swears 85 year old Totolamo village barley farmer and cattle herder Hajji Abdinur Shifa when a reporter asked him if he know  any terrorist hiding in his village. His face looks like a paint of sorrow and grief. His wife affectionately called by the villagers, Adiyo, was too fragile to talk about the August 3 2013 blood bath that turned their agriculture and livestock rich village into an inferno.
“My son took three bullets and died a day later at Sashemene general hospital. The body that was weakening by fasting could not respond well to treatment and he succumbed to his wounds without saying goodbye. His killers (federal police commandos) did not allow us entry to the hospital. My son Abdulkarim is dead but he will live in my heart until I join him in paradise…,” the respected elder said wiping his tears with a piece of garment

Wednesday, August 21, 2013

በሰሜን ኮሪያ የደናግላት ቁጥር መመናመን ፕሬዚዳንቱን አሳስቧል!


በኢትዮጵያስ?

north korea


ወጣቱ የሰሜን ኮሪያ መሪ ኪም ጆንግ እን ለሚያካሂዱት የዳንስ ስኳድ በቂ ደናግልት ለማግኘት መቸገራቸውን የደቡብ ኮሪያ ዜና ቾሱን ኢልቦ ገለጸ፡፡
ሰሜን ኮሪያ ለፕሬዚዳንቷ ክብር የምትጠቀምባቸው ዳንሰኞች የሚውጣጡት ከደናግልት ሴቶች ነው፡፡ ለዚህ ፕሬዚዳንቱን ለማዝናናት የሚደረገው የዳንስና ሙዚቃ ሙያ አባል ለመሆን የሚችሉ ድንግል ሴቶች በአብዛኛው ወጣቶችና የኮሌጅ ተማሪዎች እንደሆኑ ተዘግቧል፡፡ ክብረንጽህናን መጠበቅም ዋንኛው ቅድመ ሁኔታ ነው፡፡
ሆኖም ሰሜን ኮሪያ ካለባት ከፍተኛ የኢኮኖሚ ችግር ባሻገር አሜሪካንን ጨምሮ ምዕራባውያን በጣሉባት የኢኮኖሚ ማዕቀብ የአገሪቱን ኢኮኖሚ አሽመድምዶታል፡፡ በመሆኑም ሴቶች የትምህርት ወጪያቸውን ለመደጎም እንዲሁም የኑሮውን ውድነት ለመቋቋም በሴተኛ አዳሪነት በመሰማራታቸው የደናግልቱ ቁጥር ባልተጠበቀ ሁኔታ ለማሽቆልቆሉ እንደ ምክንያት ተጠቅሷል፡፡
ሴቶቹን የመረመሩት ወታደራዊ ሃኪሞች እንደገለጹት ከተመረመሩት የ16 ዓመት ሴቶች መካከል 60በመቶው በወሲብ ግንኙነት ድንግልናቸውን ያጡ መሆናቸውን አረጋግጠዋል፡፡ ሁኔታው ለፕሬዚዳንቱ የዳንስና ሙዚቃ ቡድን አባልነት የሚመዘገቡት “ብቃት” ያላቸው ዳንሰኞች ቁጥር ችግር ላይ ጥሎታል፡፡
ለሴተኛ አዳሪነት ያጋለጣቸው የኑሮው ሁኔታ እንደሆነ ቢገለጽም አብዛኛዎቹ ደምበኞቻቸው ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት ሲሆኑ ሴቶቹ በሚያገኙትም ገንዘብ ለኑሮ ከሚያስፈልጋቸው ሌላ ለጌጣጌጥ፣ ለሞባይል ስልክ፣ የጋብቻ ወጪያቸውን ለመሸፈን፣ ወዘተ እንደሚጠቀሙበት ዜናው ጨምሮ ገልጾዋል፡፡

Tuesday, August 20, 2013

ከእሁድ እስከ እሁድ


(የሳምንቱ አጫጭር ዜናዎች ከተለያዩ ምንጮች)

water line


ነዋሪዎች በውሃ እጦት ተሰቃየን አሉ
በሳምንት አንድ ቀን ውሃ ማግኘት ብርቅ የሆነባቸው ሰፈሮች፣ በውሃ እጦት አካባቢያቸውን በመጥፎ ጠረን የሚበክሉ የኮንዶሚኒየም መኖሪያዎች፣ ለተደጋጋሚ አቤቱታ ምላሽ ሳያገኙ በርካታ ወራት እየተቆጠሩ የሚማረሩ ነዋሪዎች የአዲስ አበባ የዘመኑ ገጽታ ሆነዋል፡፡
በቂ ውሃ ስለሌለ በራሽን ለማከፋፈል እየሞከረ መሆኑን የሚልፀው የውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን በበኩሉ፤ የኤሌክትሪክ መቆራረጥና የአንዳንድ ሰራተኞች እንዝህላልነት፣ ለመንገድ ግንባታ የሚቆፈሩ ቧንቧዎች እንዲሁም በከንቱ የሚባክን ውሃ መብዛቱ የውሃ እጥረትን እንዳባባሱ ይናገራል፡፡
የአገሪቱ እንዲሁም የአህጉሪቱ መዲና በሆነችው ከተማ፣ ለዚያውም በሰለጠነ ዘመን በርካታ ነዋሪዎች የዝናብ ውሃን ደቅኖ ለማጠራቀም ሲሯሯጡና በጀሪካን ተሸክመው ውሃ ሲያመላልሱና የፎቅ ደረጃዎችን ለመውጣት ሲውተረተሩ ማየት የተለመደ ሆኗል፡፡
በገርጂ፣ አየር ጤና፣ ጀሞ፣ እንቁላል ፋብሪካ፣ አዲሱ ገበያ፣ እንዲሁም በየአቅጣጫው የተገነቡ ኮንዶሚኒየሞችን ጨምሮ በርካታ የከተማዋ ሰፈሮች፣ በውሃ እጥረት የተቸገሩ ነዋሪዎች “አወይ ስልጣኔ” በማለት መላ እንደጠፋባቸው ይገልፃሉ፡፡
የፉሪ አካባቢ ነዋሪ ወ/ሮ አልማዝ ሞገስ፣ ቀድሞም ቢሆን በሁለት በሶስት ቀን ነበር ውሃ የምናገኘው ይላሉ፡፡ አሁን ግን ብሶበታል፣ ይሄውና በሰፈሩ ውሃ ካገኘን ከሳምንት በላይ ሆኖናል የሚሉት ወ/ሮ አልማዝ፤ ውሃ የምናገኘው ጀሪካን ተሸክመን ሰፈር አቆራርጠን ነው ብለዋል፡፡ ብዙ ጊዜ አቤቱታ አቅርበን ደከመን፤ ምንም መልስ አላገኘንም ብለዋል – ወ/ሮ አልማዝ፡፡
በጀሞ ቁጥር 1 መኖር ከጀመረች ሁለት አመት የሆናት ሰናይት ፈቃደ በበኩሏ፣ የውሃ ችግር የጠናብኝ ዛሬና ትላንት አይደለም፣ በጣም ቆይቷል ትላለች፡፡ ድሮ ድሮ ሌሊት ላይ ብቅ ይል የነበረው ውሃ፤ ዛሬ ሽታውም የለም የምትለው ሰናይት፣ የኮንዶሚኒየም ቤት ያለ ውሃ የስቃይ ቤት ማለት ነው ብላለች፡፡ የመጀመሪያ ፎቅ ነዋሪዎች የዝናብ ውሃ ደቅነው ለማጠራቀም ይሞክራሉ፣ ሁለተኛና ሦስተኛ ፎቅ ግን አይሞከርም፡፡ ቧንቧ በየቤታችን አለ፤ ውሃ የምናመጣው ግን እንደ ጥንቱ የገጠር አኗኗር ነው የምትለው ሰናይት፤ ለውሃና ፍሳሽ አመልክተናል፡፡ ውሃውን ወደ ላይ ለመሳብ የፓምፕ ሃይል ስለሚያስፈልግ ነው ይሉናል፤ ይህንን እንደ በቂ ምላሽ ይቆጥሩታል በማለት ግራ መጋባቷን ትገልፃለች፡፡

እነ “ሻኪራ” በአሞራ ገደል


(ናፍቆት ዮሴፍ)

the shakiras


የዛሬ ሳምንት ሀዋሳ ነበርኩኝ፡፡ የወትሮዋ ሳቂታዋ ሀዋሳ አልነበረችም፡፡ አኩርፋለች፡፡ ሌላ ችግር ገጥሟት ግን አይደለም፡፡ ክረምቱ ነው ያስኮረፋት፡፡
ዝናቡ፣ ቅዝቃዜውና ደመና የሸፈነው ሰማይ ተጫጭነዋት ነበር፡፡ እንደኔ እንደኔ ሀዋሳ ደርሶ አሞራ ገደልን ሳይጐበኙ መመለስ ካለመሄድ እኩል ነው፡፡ እዚህ ስፍራ ዓሳ እንደጉድ ይበላል፡፡ ያውም ቁጥር – ልክ እንደ ስጋ፡፡ የአሳ ቁርጥ ተመጋቢዎች በእንጨት ግድግዳ በተከበበው ዳስ መሳይ ቤት ውስጥ ግፊያውና መረጋገጡን ተያይዘውታል፡፡ በሀዋሳ ሀይቅ ዳር ባለው በዚህ ስፍራ ሰው ከአንድ ቦታ አሳውን ይገዛና እዛው ዳስ ቤት ውስጥ የአሳውን እሾክ እያስወጣ ቁርጡን በሳህን እየያዘ ማባያውን ለማግኘት ሁለት ጐን ለጐን የተቀመጡ ማባያ አቅራቢዎች ጋር መገናኘት ይጠበቅበታል፡፡ አንዱ “ዳጣ” የተባለው እና ከሚጥሚጣ እንዲሁም ከሌሎች ቅመሞች የተሰራ የሚያቃጥል ማባያ ሲሆን (እኔ በጣም ከማቃጠሉ የተነሳ “እንላቀስ” ብየዋለሁ) ሁለተኛው ትንንሽ ክብ የበቆሎ ቂጣዎች ናቸው፡፡ ሁለት ወጣቶች የአሳ ቁርጥ ከግፊያው ውስጥ ይዘው ወጥተው አንዱ ሌላውን፣ “ሂድና ሲዲ ይዘህ ና፣ ታዲያ ስክራች እንዳይኖረው” ሲል አስጠነቀቀው፡፡ ሲዲ ምንድነው ስል ጠየቅሁት አንዱን ወጣት፡፡ “ሲመጣ ታይዋለሽ” አለና ዳጣ ሊያስጨምር መስከረም ወደ ተባለች ዳጣ ሻጭ አመራ፡፡ እኔም “ስክራች እንዳይኖረው” የተባለውን ሲዲ በጉጉት መጠበቅ ጀመርኩ፡፡ ለካስ ሲዲ የሚሉት የበቆሎውን ቂጣ ነው፡፡ “ስክራች” የተባለው ደግሞ ያረረ እና የተሰነጣጠቀ እንዳይሆን ለማለት የተጠቀሙበት አገላለፅ ነው፡፡
ከወጣቶቹ የእንብላ ግብዣ ቀረበልኝ፡፡ የአሳ ቁርጥ በልቼ ስለማላውቅ ብፈራም “ሲዲ”ውን በዳጣ ግን አልማርኩትም፡፡ ወጣቶቹ ቁርጡን እየበሉ ሳሉ አንዱ “ሲዲውን በርን (burn) አድርገው” ሲል ሰማሁ፡፡ ደሞ ምን ማለት ይሆን አልኩኝ – ለራሴ፡፡ ለካ ቂጣው ስለላቀ ጨምር እና ግዛ ለማለት ነው፡፡ በሳቅ ታጅቤ አብሬያቸው ቆየሁ፡፡ በአሞራ ገደል ከአሳ ቁርጥ ባልተናነሰ የአቮካዶ ቁርጥም እንደ ጉድ ይበላል፡፡ ታዲያ የአቮካዶም ማባያ ዳጣ ነው፡፡ የሲዲ ሻጮቹ ሴቶች ቁጥር በርካታ ነው፡፡ ተደርድረው “ከእኔ ግዛ፣ ከእኔ ግዛ” ይላሉ፡፡ ከሁሉም ዳጣ በመሸጥ ፋታ አጥታ የምትተጋው ግን መስከረም ናት፡፡
መስከረም ላለፉት አራት አመታት በዚህ ስፍራ ዳጣ በመሸጥ ስራ ላይ መቆየቷን አጫውታኛለች፡፡ በዚህ ስፍራ ጠዋት ጠዋት ዳጣ በጅምላም በችርቻሮም ትሸጣለች፡፡ በአካባቢው ከልጅ እስከ አዋቂ ሁሉም የአሳ ቁርጥ በሊታ ነው፡፡ እርግጥ የተጠበሰ አሳም በስፍራው ይገኛል፡፡ ግን ቁርጥ ተመጋቢው በቁጥር ይልቃል፡፡ የተጠበሰ አሳ ከአሞራ ገደል ይልቅ በፍቅር ሀይቅ በኩል ኦሲስ አሳ መሸጫ ውስጥ ይገኛል፡፡ በዚህ ቦታ የአሳ ሾርባው ተጠጥቶ አይጠገብም፡፡
እነሆ ሌላ ትዕይንት፡፡ የአሳ ቁርጥ ሲሰራ የሚጣለውና ትርፍራፊውን የአሳ ስጋ በፌስታል በመያዝ እና በአካባቢው አባ ኮዳ ተብሎ ለሚጠራው ግዙፍ የወፍ አይነት እየወረወሩ በመስጠት ሌላ ስራ የሚሰሩም ታዳጊዎች አስደምመውኛል፡፡ እንግዳ ሆነው ከሄዱ ይህ ወፍ በረጃጅም ማንቁርቱ ስጋውን ለመያዝና ከተቀናቃኙ ሌላው ጓደኛው ለመቅደም የሚያደርገው ዝላይ አይን ያፈዛል፡፡ ብልጣብልጦቹም ታዳጊዎች “ሂዱና ፎቶ ተነሱ” ብለው ወፉ አካባቢ እንዲቆሙ ይነግሩዎታል፡፡ እርስዎም በዚህ ትዕይንት መሀል አንድ ታሪካዊ ፎቶ ልነሳ ብለው ወፉ ስጋ ለመቅለብ የሚያደርገውን ዝላይ እየተመለከቱ ፎቶ ሲነሱ ይቆዩና እግዜር ይስጥልኝ ብለው ሊሄዱ ሲሉ “እንዴ ጋሼ (እትዬ) አስር ብር ይክፈሉ፤ ይህንንም ስራ የምንሰራው እኮ በማህበር ነው” ብለው እርፍ ይላሉ፡፡ እየሳቁም እየተገረሙም ከፍለው ይሄዳሉ፡፡ ሌሎች በርካታ ትዕይንቶችም በዚህ ስፍራ ይገኛሉ፡፡

Monday, August 19, 2013

የሽብርተኝነት አዋጁ፤ የጠሉትን መምቻ?


ተመስገን ደሳለኝ

ኢህአዴግ ባለፉት ሃያ ሁለት ዓመታት በስራ ላይ ካዋላቸው አዋጆች መካከል የ‹‹ፀረ-ሽብር ህጉ››ን ያህል
ያጨቃጨቀ የለም ቢባል ከእውነቱ ብዙም አልራቀም፡፡ በርግጥ ከተቃውሞ አቅራቢው አብዛኛው በደፈናው ‹‹ህጉ
አያስፈልግም›› የሚል አልነበረም፡፡ ህጉ ‹‹ሽብርተኝነት››ን የገለፀበት መንገድና አንዳንድ አንቀፆቹ ለትርጉም አሻሚ
በመሆናቸው ከስርዓቱ ባህሪ አኳያ ለፖለቲካ ጥቅም የሚውሉበት ዕድል መኖሩ አይቀሬ ነው የሚል ስጋት ነበር፡፡
የህግ ረቂቁ ለተወሰኑ የምዕራብ ሀገራት ዲፕሎማቶች ይመለከቱት ዘንድ በተሰጣቸው ጊዜም ተመሳሳይ ስጋት
ሲያነሱ፤ አምነስቲ ኢንተርናሽናል ደግሞ ‹‹ሽብርተኝነት››ን ከየትኛውም የአለማችን ሀገር እጅግ በሰፋ መልኩ ስለሚተረጉም መሰረታዊ
መብቶችን ሊዳምጥ እንደሚችል ጠቅሶ መጽደቁን ለመቃወም ብዙ ጊዜ አልወሰደበትም፡፡
በጊዜው የግንባሩን ለዘብተኛ አመራሮች ጨምሮ ተቃዋሚ ፓርቲዎች፣ አለም አቀፍ የመብት ተሟጋች ተቋማት፣ የምዕራብ ሀገራት
ዲፕሎማቶች፣ ጋዜጠኞች፣ ምሁራኖች… ይህ ህግ ፀድቆ በስራ ላይ ቢውል የፖለቲካ መብቶችን እና የዜጐችን ነፃነት ከመገደብ አልፎ
ስርዓቱ በአይኑ መዓት የሚያያቸውን ፖለቲከኞች እና ጋዜጠኞች መምቻ (ማጥቂያ) ሊያደርገው ይችላል በሚል ጥርጣሬ ቢያጣጥሉትም
በነሐሴ 22/2001 ዓ.ም በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከመውጣት ሊያስቆሙት አልቻሉም፡፡
…ህጉ ስራ ላይ ከዋለ ሶስት አመት ሞቶታል፡፡ በዚህ ፅሁፍም ህጉ ከመተግበሩ አስቀድሞ የተነሱ ስጋቶች እውን መሆናቸውን እና በተግባር
ከታየው የህጉ ዓላማ ጋር አሰናስዬ ለማየት እሞክራለሁ፡፡
እንደ መግቢያ
የአፍሪካ ቀንድ ከተፈጥሮአዊው ጂኦ-ፖለቲካ አኳያ እና በአካባቢው ያሉ ሀገራትም የፈራረሰችውን ሶማሊያን ጨምሮ ለጽንፈኛ የእስልምና
እንቅስቃሴ የተጋለጡ መሆናቸው ለሽብርተኝነት የተመቻቸ ሜዳን እንዲፈጥር ማድረጉ አያከራክርም፡፡
በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የአሸባሪዎች ቀጥታ ጥቃት የታየው የቀድሞውን የግብፅ ፕሬዘዳንት ሆስኒ ሙባረክን ዒላማው ያደረገ አንድ
ቡድን በ1986 ዓ.ም. በአዲስ አበባ የግድያ ሙከራ ባደረገበት ጊዜ ነበር፤ ቀጥሎ ደግሞ በ1991 ዓ.ም. በትራንስፖርትና መገናኛ ሚኒስትሩ
አብዱልመጅድ ሁሴን ላይ የተሞከረው ግድያ የሽብርተኝነት ጅማሮዎች ሆነዋል፡፡ ይህ ከሆነ ጥቂት ዓመታት ዘግይቶ በተመሳሳይ ሰዓት
በግዮን እና በዋቢ ሸበሌ ሆቴሎች የደረሰው የቦንብ ጥቃት፣ መሀል ፒያሳ ይገኝ በነበረው ትግራይ ሆቴልን የመታው ፍንዳታ የሽብር
አደጋው በቅርብ ርቀት ለመኖሩ አመላካች ነበር፡፡ ይህም ሆኖ ስርዓቱ ድርጊቱን ለመከላከል በስራ ላይ ከዋሉት ህጎች ተጨማሪ አዲስ አዋጅ
‹‹ያስፈልገኛል›› የሚል ድምዳሜ ላይ አልደረሰም፤ ወይም የመፈለግ ምልክት አልታየበትም፡፡

በግብፅ እየሆነ ያለው ለእኛ ምን ትምህርት ይሰጣል?


(ጌታቸው በቀለ ኦስሎ)

egypt-


ከትናንት ጀምሮ ብዙዎች በግብፅ እየሆነ ያለውን በማህበራዊ ድህረ ገፆቻቸው ላይ በፎቶ የተደገፈ መረጃ እየሰጡ ነው።ሁኔታው እጅግ ዘግናኝ እና አሳዛኝም ነው።በተለይ ከጉዳዩ ጋር ምንም ተያያዥነት የሌላቸው አብያተ ክርስትያናት መቃጠል አጋጣሚን ተጠቅሞ የእረጅም ጊዜ እኩይ ዕቅድን የመፈፀም ድርጊት ነው። እኔን የሚያሳስበኝ እኛ በተወሳሰበ ፖለቲካዊ ሁኔታዎች ውስጥ ያለን ተመሳሳይ የታሪክ ክስተት ያሳለፍነው ኢትዮጵያውያን ከእዚህ ተምረን ምን እናድርግ? የሚለውን ጥያቄ መመለስ ነው ቁም ነገሩ።ከእዚህ በተረፈ ግን ለሀገራችን መፍትሄ የምንለውን ለመናገር ፈርተን ወይንም የሀገራችንን ተጨባጭ ሁኔታዎችን ሳናነሳ ስለ ግብፅ ብንናገር ምን ይሆን ፋይዳው?
የፖለቲካ ለውጥ ከመነሻው እስከመድረሻው የሚሄድባቸው ሂደቶች እጅግ አስገራሚ እና ውጤቱም ከተጠበቀው ይልቅ ያልተጠበቀው ክስተት የበላይ መሆኑ አንዱ እና አይነተኛው ተፈጥሮው ነው።ለእዚህም የቅርብ ጊዜ ምሳሌ የሚሆነን የሰሜን አፍሪካው የለውጥ ማዕበል ነው።የለውጥ ማዕበሉ አነሳስ፣ሂደት፣ግብ እና ውጤት የሃገራቱን ተጨባጭ ነባራዊ ሁኔታ ያገናዘበ ቢሆንም በአግባቡ የተደራጁ የፖለቲካ ፓርቲዎች ያሉባቸው እና የሌሉባቸው ሃገራት ልዩነት ግን ፍንትው ብሎ ታይቷል። የቱኒስያን እና የአልጀርያ የለውጥ ማዕበል ከሊብያ ጋር ያለው ልዩነት እና  በአንፃሩ ደግሞ የግብፅ እና የየመን ሁኔታ አሁንም ድረስ በእንጥልጥል መሆኑ ለሰሜን አፍሪካ ብቻ ሳይሆን ለአፍሪካ ቀንድ ብሎም ለኢትዮጵያ የሚኖረው ተዘዋዋሪ ተፅኖ በቀላሉ የሚታይ አይደለም።ቢያንስ የሁለቱ ሃገራት አለመረጋጋት በእዚሁ ከቀጠለ የአካባቢ ትናንሽ ጉልበተኞች የመፈጠራቸው አባዜ ብቻ ሳይሆን ከፍተኛ የጦር መሳርያ ንግድ የሚደራባቸው ሃገራት የመሆናቸው ፋይዳ ውሎ አድሮ እንደ ኢትዮጵያ ላለች ሃገር አይነተኛ ፈተና መሆኑ አይቀርም።ፈተናውም ከሃይማኖታዊ ነውጠኞች እስከ ንግድ አዋኪዎች ድረስ የሚፈጥረው ተፅኖ ቀላል አይደለም።
የአፍሪካ ቀንድን እና ቀጠናውን ስንመለከት በብዙ ፖለቲካዊ፣ምጣኔ ሃብታዊ እና ማህበራዊ ችግሮች የተወጠረ በመለስተኛ የነገሮች ክስተት ከባድ ስብአዊ ቀውስ የመድረሱ ዕድል ከፍተኛ እንደሆነ እንመለከታለን። የአሁኑ ጊዜ የአካባቢው የፖለቲካም ሆነ የወታደራዊ  ኃይላት(የኢህአዲግ መንግስትም ሆነ ተቃዋሚ ኃይሎች) ነገሮችን በአንክሮ አይተው አማራጩን እና አዋጪውን የፖለቲካ መስመር የመቀየሻ ወሳኝ ጊዜ ላይ  መሆናቸውን ቢረዱት ለሀገራችን አንዱን የፈተና ወቅት የምታልፍበት ጊዜ ሆነላት ነበር።ብልህ እና ቆራጥ መሪ የሚናፈቀው የእዚህ ጊዜ ነው። ከእዚህ ባለፈ ግን ውጥረቶችን ለማርገብ በመሞከር መተኮር በሚገባው በዋናው እና እጅግ አደገኛው ሁኔታ ላይ ማትኮር ካልተቻለ ተያይዞ መጥፋት ብቸኛ ዕጣ መሆኑ የማይቀር መሆኑን መረዳት ብዙም ብልህነት አይጠይቅም።

ዋስትናችን እርቅ ብቻ ነው!


“እኛ የእሳት አደጋ ብርጌድ የለንምና ዋ!!'' ኦባንግ

recon-e


እሳት ሲነሳ የመጀመሪያው ተግባር እሳቱን በፍጥነት ማጥፋት ለሚችለው የእሳት አደጋ ብርጌድ መደወል ሲሆን፣ ቀጣዩ ተግባር እሳቱ በተነሳበት አካባቢ ያሉ ነዋሪዎች ነፍስ አትርፈው እሳቱን በተገኘው መንገድ ለማጥፋት መረባረብ ነው። ይህ የተለመደው ተግባር ዛሬ በኢትዮጵያ ስለመስራቱ የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ /አኢጋን/ ዋና ዳይሬክትር ስጋት አላቸው። እናም “እኛ የእሳት አደጋ ብርጌድ የለንምና ዋ!!” የሚል ማስጠንቀቂያ አዘል ጥሪ ያሰማሉ።
“አሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ እሳቱ ፊትና መልክ ይዞ ሲቀጣጠል አላነውም እንጂ በርካታ የማቀጣጠያ ቅመሞች ተዘጋጅተውለት ለመንደድ በዝግጅት ላይ ነው። መንደዱ የማይቀረው ይህ እሳት ቢነሳ የሚያጠፋው የለም” የሚሉት አቶ ኦባንግ ሜቶ፣ ጥላቻው በሰፈር ደረጃ ከርሯል ይላሉ። በየመንደሩ ህዝብ እንዲቧደን ተደርጓል። ሚና ለይቷል። አገር የሚመራው መንግሥትም ችግሩን ከመፍታትና አገሪቱን ከስጋት ከማላቀቅ “ጥሪ አይቀበልም” በሚል የሃይል ርምጃ መምረጡ ነገሮችን ይበልጥ እንዳወሳሰበ ይናገራሉ።
በየአቅጣጫው ያሉ ወገኖች ቆም ብለው ሊደበቁት ከማይችሉት ከህሊናቸው ጋር ሊነጋገሩ እንደሚገባ ያመለከቱት አቶ ኦባንግ “ግብጾች ግብጾችን ገደሉ፣ ገና ቀውሱ ይቀጥላል። ይህ እጅግ ዘግናኝ የሆነው ቀውስ እኛ ዘንድ ሳይደርስ ወደ እርቅ እናምራ። ለእውነተኛ እርቅ ጊዜው አሁን ነው” በማለት አንገብጋቢ ያሉትን ጥሪ ያስተላልፋሉ።
“ላለፉት 22 ዓመታት ኢትዮጵያ ላይ ከየአቅጣጫው የተረጨው መርዛማ ፖለቲካና፣ ሰብአዊነት የጎደለው አስተዳደራዊ መዋቅር የፈጠረው ውጥረት ወደ መፈረካከስ እየነዳን ነው” በማለት የስጋቱን መጠን የሚጠቁሙት አቶ ኦባንግ ፣ በግብጽ የተፈጠረው ቀውስ በሃይል ሊቆም የማይችልበት ደረጃ ሲደርስ ምዕራባዊያንም ሆኑ አሜሪካ የሃዘን መግለጫ ከማውጣት የዘለለ ስራ አለመስራታቸው ለኢትዮጵያዊያን ታላቅ ትምህርት ሊሆን እንደሚገባ ያሰምሩበታል።
በሩዋንዳ ለቁጥር የሚያዳግቱ ሰዎች አልቀዋል። በኮሶቮ ህዝብ ተጨፍጭፏል። ዳርፉር ንጹሃን የጥይት ራት ሆነዋል። ይህ ሁሉ ከመሆኑ በፊት ሃያላን መንግስታትና “ድርጅቶቻቸው” በእነዚህ አገራት ውስጥ ነበሩ። እያወቁት ነው የሆነው። ግን ጉዳዩ የጥቅም ችግር ስለማይፈጥርባቸው አገራቱ በደም ጎርፍ ሲታጠቡ በዝምታ ተመልክተው እንደነበር ያስታወሱት አቶ ኦባንግ፣ “ሶሪያ ስትፈርስ፣ ከ100 ሺህ ሰው በላይ ሲያልቅና አሁንም እያለቀ ባለበት ሁኔታ እልቂቱን ማስቆም እየቻሉ ዝምታን መርጠዋል” በማለት አቶ ኦባንግ ከነዚህ አገሮች፣ በተለይም “አሁን ግብጽ ላይ በተፈጠረው ችግር ካልደነገጥንና ለሚቀርበው የእርቅ ጥያቄ መልስ ለመስጠት የማንዘጋጅ ከሆነ አደጋው የከፋ ሊሆን ይችላል” ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

Tuesday, August 13, 2013

ታላቅ ሃገራዊ መልዕክት ለክርስቲያን ወገኖቻችን

August 12, 2013

ይህንን ታላቅ ሃገራዊ መልዕክት ለሁሉም በማዳረስ ሃሰትን ለማንገስ የሚደረገውን ሩጫ ያጋልጡ!!!

እኛ ኢትዬጲያውያን ሙስሊሞች በሃገራችን ኢትዬጲያ ለረጅም ዘመናት ከክርስትና እምነት ተከታዬች እና ከሌላ እምነት ተከታዬች ጋር ተከባብረን እና ተደጋግፈን ስንኖር መቆየታችን ይታወሳል፡፡
ይህም የመቻቻል እና የመደጋገፍ ባህላችን ዛሬም መልኩን ሳይቀይር አለምን በሚያስደንቅ ሁኔታ እንደቀጠለ ይገኛል፡፡ሆኖም ይህንን ተቻችሎ እና ተከባብሮ በሰላም የመኖር ባህላችንን ለማደፍረስ የኢህአዴግ መንግስት በሃይማኖታችን ላይ ጣልቃ በመግባት ከሊባኖስ አህባሽ የተሰኘ ከእስልምና አስተምህሮ ያፈነገጠ ባዕድ እምነት በማስመጣት በሙስሊም ወገኖቻችሁ ላይ በግዳጅ እምነታችንን ለማስቀየር እየሞከረ ይገኛል።
For Ethiopian muslims and chrstians
እኛም ሙስሊሞች መንግስት በሃይማኖታችን ላይ ጣልቃ አትግባብን ከጥንት ጀምሮ በሃገራችን የነበረውን አስልምና መንግስት ባስመጣው አህባሽ በተሰኘ አዲስ ሃይማኖት አንቀይርም በማለታችን አክራሪዎች፣አሸባሪዎች ናችሁ በማለት በመንግስት እየተደበደብን እየተገደልን እና እየታሰርን እንገኛለን፡፡
መንግስት በሃማኖታችን ላይ ጣልቃ አይግባብን በማለት በሰላማዊ መንገድ መቃወም ከጀመርን ድፍን ሁለት አመት ሊሞላን ጥቂት ጊዜያት ብቻ ይቀሩታል፡፡ በሁለት አመት የሰላማዊ ትግላችን ሂደት ውስጥ ከጅማሮ አንስቶ አስካሁን ድረስ ሶስት መሰረታዊ ጥያቄዎችን ለመንግስት አቅርበን ምላሽ እስኪሰጠን እየጠበቅን ብንገኝም መንግስት እንደመንግስት በሚሊዬን የሚቆጠረውን የሃገሪቷን ሙስሊሞች ድምፅ ከመስማት ይልቅ ጥያቄዎቻችንን በማድበስበስ እና ሃላፊነት በጎደለው መልኩ የጠየቅናቸውን 3 ቀላል ጥያቄዎችንን በማጣመም በሃሰት ፐሮፖጋንዳ ላይ ተጠምዶ ይገኛል፡፤

ሌሊሴ ተፈታች! ቀጥሎስ?


lelissie


ላለፉት 5 ዓመታት ያህል ከልጆቿና ባለቤቷ ተለይታ በእስር ስትማቅቅ የነበረችው ሌሊሴ ወዳጆ መፈታቷ በርካታ ኢትዮጵያውያንን ማስደሰቱ ተጠቆመ፡፡
የጋዜጠኛ ሌሊሴን መፈታት አስመልክቶ Ayyaantuu News Online ለንባብ ባበቃው ዜና እንዳመለከተው በስደት አውስትራሊያ ከሚኖረው ከባለቤቷና ከልጆቿ ጋር ተቀላቅላለች፤ ድረገጹ ዜናውን በምስል በማስደገፍም አቅርቦታል፡፡
በጋዜጠኝነት ሲያገለግል የነበረው ባለቤቷ ዳቢሣ ዋቅጂራ አገር ጥሎ መሰደዱን ተከትሎ በማታውቀው ምክንያት የኦነግ አባል ነሽ በማለት ኢህአዴግ 10ዓመት ያለ አመክሮ ፈርዶ ወኽኒ እንዳወረዳት ይታወሳል፡፡ ይህንን ህዝብን ያበሳጨና ያስቆጣ ጉዳይ ሌሊሴ ከታሰረችበት ጊዜ ጀምሮ አምነስቲ ኢንተርናሽናልና ዓለምአቀፉ የጋዜጠኞች መብት ጥበቃ ድርጅት (CPJ) ጨምሮ በርካታ ኢትዮጵያውያን ሲያወግዙትና እንድትፈታ ሲሟገቱ መቆየታቸው ይታወሳል፡፡
በኢትዮጵያ የፖለቲካ እስረኛ የለም” በማለት ጠ/ሚ/ር ሃይለማርያም ደሳለኝ የተናገሩትን ተከትሎ ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ታህሳስ 24፤2005ዓም (January 2, 2013) በዘገበበት ወቅት፤ ጋዜጠኛ ሌሊሴ ወዳጆን የሰው ልጆችን ኅሊና ከሚፈታተኑት የማኅበራዊ ጉዳዮች ጋር በማያያዝ የግምባር ዜና አድርጓት እንደነበር ይታወሳል፡፡
ከአብራኳ የወጡትን ልጆቿን የማሳደግ ወግ የተነፈገችው እናት ከ3 ልጆቿ ጋር ሆና የሚያሳየውን ምስሏ አስደግፎ ጎልጉል በወቅቱ ሲዘግብ ጠ/ሚ/ር ሃይለማርያም ለተናገሩት ቅጥፈት ማጣፊያ በማድረግ ነበር፡፡
ከኦነግ ጋር ግንኙንት አለሽ ተብላ ከ3 ለጆችዋ ተነጥላ 10 ዓመት ጽኑ እስራት የተፈረደባት ሌሊሴ ወዳጆ
ከኦነግ ጋር ግንኙንት አለሽ ተብላ ከ3 ለጆችዋ ተነጥላ 10 ዓመት ጽኑ እስራት የተፈረደባት ሌሊሴ ወዳጆ
በእስር ቤት ታጉረው ከሚገኙት በርካታ የኢትዮጵያ ውድ ልጆች መካከል አንዷ ስለሆነችውና ስለአጠቃላይ የግፍ ቀንበር የተጫነባቸው ወገኖች በወቅቱ ለጎልጉል አስተያየት የሰጡት የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዋና ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ ሜቶ የአቶ ሃይለማርያምን ንግግር “በእውነቱ ይህ ፍጹም ቅጥፈት የተሞላበትና አጸያፊ ነው፤ እነዚህ እስረኞች እኮ በቁጥር የሚታወቁ ብቻ ሳይሆኑ ስም፣ ቤተሰብ፣ ልጅ፣ ዘመድ፣ ወዘተ አላቸው፡፡ እናውቃቸዋለን፤ ዓለም ያውቃቸዋል፤ እንግዲህ ጠ/ሚ/ሩ ለእነዚህ ልጆችና ቤተዘመዶች ነው አባታችሁ/እናታችሁ/ዘመዳችሁ ወንጀለኛ አሸባሪ ነው እንጂ የፖለቲካ እስረኛ አይደለም እያሉ ነው ያሉት፤ … ይህ ሥነምግባር የጎደለው ንግግር ነው” በማለት ዕርቃኑን አስቀርተውት ነበር፡፡
“ሌሊሴ ከዚህ ቀጥሎስ?” በሚል በህይወት የተፈተነችበትን የእስርቤት ቆይታዋና በተመሳሳይ ሁኔታ በእስር የሚማቅቁትን ኢትዮጵያዊ ወገኖቿን አስመልክቶ የሚደርስባቸውን ከአንደበቷ ለመስማት የሚጠብቁ ወገኖች እንደሚሉት ከሆነ “ሌሊሴ ጭንቀቷን ለተጨነቀላት የኢትዮጵያ ህዝብ የመፈታቷን ዜናና የእስር ቤት ቆይታዋን ከራሷ አንደበት እንሰማለን” ብለው እንደሚጠብቁ ይናገራሉ፡፡

Monday, August 12, 2013

አውራውን ፍለጋ… – በተመስገን ደሳለኝ


‹‹በድብልቅልቁ አምላክ››
መግቢያ
ዛሬ በስሱ ላነሳው ያሰብኩትን አጀንዳ አለቃ አፅሜ በምኒልክ ዘመን ካሳተሙት አንድያ መጽሐፋቸው ላይ ባገኘሁት ታሪክ ልጀምር፤ እንዲህም ይነበባል፡-
‹‹በሸዋ መርድ አዝማች ኃይሌ፣ በሣህለ ሥላሴ አልጋ ከተቀመጡ በኋላ ከአቶ ሰይፉ ጋር ቂሙ የማይበርድ የቅድስት ኃይማኖት ጦርነት ተጀመረ፡፡ ቀሪውን በPDF ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ
Journalist Temesgen Desalegn
Journalist Temesgen Desalegn

ግልጽ ደብዳቤ ለአቶ ሀይለ ማሪያም ደሳለኝ


August 12, 2013
ከብርሃኑ ተስፋዬ
ይድረስ ለአቶ ሀይለ ማሪያም ደሳለኝ
ፖ.ሳ. ቁ. 1031
አዲስ አበባ

ጉዳዩ፣ የተደናበረው ማነው!
እንደ ጠቅላይ ሚኒሰትር ሳይሆን እንደ ተራ ካድሬ ከዋልታ ኢንፎርሜሽን ጋር ያደረጉትን ቃለ ምልልስ አዳመጥሁት ገረመኝ፣ ፣ አግራሞት የፈጠረብኝ ደግሞ ከአፋዊ ህግ መንግስት አንቀጽ ቀንጨበው ጉዳዩን ለማስረዳት መሞከርዎ ሳይሆን ጠያቂዎ ያጎረሰችዎትን ቃላት እንዴት ለመጠቀም መሞከርዎ እሱዋ ሃላፊዎት እንጂ ጠያቂዎት ሳትሆን መሪ ካድሬዎት መሆኑዋን ማረጋገጥዎ ነው።
Ethiopian PM Hailemariam Dessalege chauvinism ideology
ይህ የተደናበረ መልስዎ ያጫረብኝ በሃይማኖት ሺፋን የፖሊቲካ እንቀስቃሴ ሃገሪቱ ውስጥ አለ ብለው አፍዎን ሞልተው የሸሪያ መንግስት ለመመስረት የተነሱ ናቸው ብለው መናገርዎ አንድን ጣልቃ አትግቡን የራሳችንን መጅሊሰ ያለ መንግስት ጣልቃ ገብነት ራሳችን እንምረጥ ያለን የሙስሊም ማህበረ ስብ ጥያቄ እንደዚህ ከፖሊቲካ ሃሳብ ጋር ማጋባተዎ የባጃጅነትዎን መጋረጃ ቀደው ለህዝብ ባደባባይ ራስዎን ያሳዩበትን በማየቴ ነው።
ለመሆኑ እየመራሁት አለሁት የሚሉትን መንግስት በዝርዝር እንመልከተው እስቲ፣
ገና ተጠባባቂ ተብለው ባቶ በረከት ስምኦን ከተሰየሙና የዱዳ ፓርላማ ማህተም ከማድረጉ በፊትና ካደረገልዎት ወቅት ጀምሮ የተዘጉ የሜዲያ ዉጤቶች ከደቡብና ሌሎች ክልሎች የተፈናቀሉ ኢትዮጵያዉያን ሁኔታ በመንግስት ወጪና ከቀረጥ ነጻ መብት ያለው ሃገሪቱን ያለወደብ ላስቀረና ማህበረ ሰባችንን በጎሳ ላከፋፈለ ህዝቡን አፈናቅሎ በሳንቲም ደረጃ መሬታችንን ላከራየና ለገደለ አርዮስ መታሰቢያ ድርጅት ለፓርላማ አቅርበው እንዲጸድቅ ማድረግዎ የሚጠቀሱት ናቸው።

Sunday, August 11, 2013

የመንግስት ጥቃት ቀድሞ ከፍተኛ ዝግጅት የተደረገበት ነበር!

August 10, 2013

ድምፃችን ይሰማ

‹‹እኛ ልጆቻችንን ይዘን ለዒድ በዓል ወጣን፣ እነሱ ግን በዒድ በዓላችን መሳሪያ ይዘውብን ወጡ፡፡››
ሐሙስ እለት የተከበረውን የዒድ በዓል አክብረው ይመለሱ የነበሩ ዜጎች ላይ መንግስት የወሰደው እርምጃ ቀድሞ ከፍተኛ ዝግጅት የተደረገበት እነደነበር ታውቋል፡፡ በእለተ ሀሙስ የተከበረውን የዒድ አል-ፊጥር በአል ለማክበር በሰላት ማካሄጃ አደባባዮች የተገኙ በርካታ ቁጥር ያላቸው ሙስሊሞች በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች ከፍተኛ ድብደባ እንደተፈጸመባቸው ይታወቃል፡፡ በዚህ ድብደባ ከቀላል የአካል ጉዳት አንስቶም እስከ ሞት የደረሰ ጉዳት በሰፊው ሙስሊም ማህበረሰብ ላይ ደርሷል፡፡ በዚህ ጥቃት በተለይ ሴቶች፣ እናቶች እና አባቶች ከፍተኛውን ድርሻ ይዘዋል፡፡
Ethiopian Muslims
መንግስት ከዒድ በዓል ቀድም ባሉት ቀናት ‹‹ሰላም ወዳዱ ሙስሊም ማህበረሰብ›› በሚል ብሂል ሰፊ ፕሮፖጋንዳ በመስራት ለሙስሊሙ ኅብረተሰብ ‹‹ተቋርቋሪ›› መሆኑን ለማሳየት ሲጥር ሰንብቶ ነበር፡፡ ከዒድ ቀደም ብሎ ባሉት ጊዜያትም የአንዋር መስጂድን እና የመካ ተራዊህ ሰላትን በቀጥታ በኢቴቪ በማስተላለፍ የሙስሊሙን ልብ ለመደልል ሞክሯል፡፡ ከዚያ በተጨማሪም እስከአሁን ባልታየ መልኩ ከፌዴራል ፖሊስ የ‹‹እንኳን አደረሳችሁ›› የመልካም ምኞት መግለጫም ተብሎ በሚዲያዎች ተበትኗል፡፡ እነዚህ ሁሉ ግን ባዶ ሽንገላዎች መሆናቸውን ለማረጋጋጥ ቀናት እንኳ አልዘገዩም፡፡
ሆኖም መንግስት በሚዲያው ይህን አይነቱን ጉዳይ እያቀረበ በተቃራነው አቅጣጫ ግን መንግስት ሙስሊሙ ላይ ጥቃት የሚፈጽምበትን ስልት እያሰላ ነበር፡፡ ከፍተኛ የመንግስት እና የደህንነት ሀላፊዎች በወታደራዊ የጦር ስታራቴጂ የአዲስ አበባ ስተዲየምና አካባቢውን በጦር ቀጠና በመክፈልና ሙስሊሙ ላይ ጥቃት መፈጸሚያ ስልት በመንደፍ ላይ ነበሩ፡፡ ከስታዲየም እስከ 7 ኪሎ ሜትር ራዲየስ ርቀት ድረስ የሚገኙ አካባቢዎችና የውስጥ መንገዶችን ለዚህ ጥቃት በማመቻቸት ለዒድ አሰቃቂ ጥቃት የተዘጋጀው መንግስት በቴሌቪዥኑ ግን ሙስሊሙን ‹‹ሰላም ወዳዱ ማህብረሰብ እያለ›› እያፌዘበት ነበር፡፡

በማሸበር የሚኖሩ በመግደል የሚከብሩ የሰው አረሞች

August 9, 2013

ዳኛቸው ቢያድግልኝ

አረም ማለት ያልተዘራበት የሚበቅል ገበሬ የዘራውን ሰብል የሚሻማ፣ ውሀውን የሚጠጣበት፣ ለበሽታና ተባይ መጠለያ በመሆን ለሰብል ጉዳት ምክንያት የሚሆን እጽዋት ማለት ነው። አረም በስሮቹ አማካይነት የሰብሉን ስር አንቆ የሚገድል፣ አንዳንዱም እንደ ፓራሳይት ሰብል ላይ ተጣብቆ የሚበቅል እንደ አቀንጭራ ያለ ማለት ነው። አረሞች በፈጣን አስተዳደጋቸው ሳቢያ አልሚ ንጥረ ነገሮችን ከመሬት የፀሀይ ብርሃን ከሰማይ በመሻማት የሚያቀጭጩና የሚገድሉ ናቸው። የስንዴ ማሳ ውስጥ የበቀለ በቆሎም እንኳ ቢሆን አረም ነው፣ ገብስም ቢሆን አረም ነውና ተነቅሎ ይጣላል።
Tigray People Liberation Front Split
አረም ዘሩን በማባዛትና የመኖር እድሉን ለማራዘም በርካታ ዘዴዎችን እየተጠቀመ በብዛት የሚንሰራፋና በወቅቱ ካልታረመ ሰብል የሚያጠፋ ነው። ጎበዝ ገበሬ አርሞና ኮትኩቶ ሰብሉን ካልተንከባከበ በሰብል ምርት ምትክ አረሙን ማፈስ ይገደዳል። ልክ እንደ ምሳሌው ኢትዮጵያዊነትን የሰው አረም ውጦታል። ፀረ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት አቋምን የያዘ በሌሎች ስም ይልቁንም በትግሬ ስም ኢትዮጵያዊነት ላይ ተጣብቆ አገር እያፈረሰ ያለ የዘራፊ ቡድን አገርና ሕዝብ እያቀጨጨ ነው። ወያኔ በቆሎና ማሽላ ላይ ተጣብቆ እንደሚበቅል አቀንጭራ (ፓራሳይት፣ ጥገኛ አረም) ኢትዮጵያዊነትን ተጣብቶ ኢትዮጵያን እየገደለ ያለ ቡድን ነውና ተነቅሎ መጥፋት አለበት። በምስሉ የተቀረጹ ‘ኦፖርቹኒስት’ ገንጣዮችና ከፋፋይ ድርጅቶችም እንዲሁ።

Saturday, August 10, 2013

ከፖለቲከኞች በላይ ገኖ የወጣው “ድምጻችን ይሰማ”

ኢህአዴግ አክራሪነትን እየጋበዘ ነው!!


1


”የሰላማዊ ትግል ምንነት ለማይረዱ ትልቅ ትምህርት የሰጠ፣ ኢህአዴግ ፍጹም የሆነ ልምድ ባካበተበትና ኤክስፐርት በሆነባቸው የትግል ስልቶች ብልጫ ወስዶ ለማንበርከክ እንደሚያስቸግር፣ ሰላማዊ ትግል ከራስና ከስሜት ጋር የሚደረግ ታላቅ አስተምህሮት መሆኑን ለማረጋገጥ ተችሏል። የድምጻችን ይሰማ ትግል በዚህ መልኩ በኢትዮጵያ ቀዳሚ ሆኖ ይቆያል” በግል አድራሻ ከተላከ አስተያየት የተወሰደ።
በአሃዝ፣ ጉዳቱ በሚገለጽበት መጠን፣ ጉዳቱ የሚገለጽበት ደረጃና የቋንቋው አቅም ልዩነት ካልሆነ በስተቀር ሁሉም ወገኖች፣ የውጪ ታዛቢዎች፣ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት፣ ራሱ ኢህአዴግ፣ ህወሃትና መላው ወዳጆቹ በአንድ እውነት ይስማማሉ። እሱም ህወሃት ራሱ ባመጣው ጣጣ፣ ራሱ ትዕዛዝ ሰጪ ሆኖ ያደረሰው ሰብአዊና በቀላሉ ሊበርድ የማይችል መከራ እንደሆነ በየአቅጣጫው አስተያየት እየተሰጠ ነው።
ያለ ምንም ማጋነን ኢህአዴግ ደም አፍሷል፣ ህይወት ቀጥፏል፣ አስሯል፣ ገርፏል፣ ፈንክቷል፣ ጣጣው ለሌሎች የሚተርፍ አካሄድ በመከተሉ ችግሩን አወሳስቦታል። ኢህአዴግ ይህንን ሁሉ ርምጃ የሚወስደው “ከብዙ ትዕግስት” በኋላ መሆኑን “በመንግሥት ወግ” ቢገልጽም “የሚያምነው ያገኘ አይመስልም” የሚል ወቀሳም ይሰነዘርበታል። እንደውም “ለየትኛዋ የሚወዳት አገር” በሚል ለፕሮፓጋንዳ አፉን በከፈተ ቁጥር ዘለፋ እየወረደበት ነው።

“ኢህአዴግ ጉልበት አልባ ተደረገ!”

ኢህአዴግ አቅም አልባ ሆኗል የሚሉ ወገኖች አሉ። እነዚህ ወገኖች ገለጻቸው ለሌላው ግራ የሚያጋባ አባባል ሊሆን እንደሚችል ይገምታሉ። ግን በነሱ እምነት ኢህአዴግ አቅም አልባ ሆኗል። አቅም አልባ ያደረገው “የድምጻችን ይሰማ” የትግል ስልት ነው። ኢህአዴግ ያለውና 4የሚታወቅበት መለያው የታጠቀው መሳሪያ፣ ወታደሩ፣ የፌደራል ሃይሉ፣ የክልል ፖሊስ፣ ፈጥኖ ደራሹ፣ የሰላምና መረጋጋቱ ፣ የስለላ ሃይሉ፣ የአጋዚ ጦሩ፣ የአንድ ለአምስት አወቃቀሩ … ከሁሉም በላይ ደግሞ ጉልበተኛነቱን የሚቆጣጠሩለት የአንድ ብሔር “ታማኝ” ሃይሎች መሆናቸው እንደሆነ አብዛኞች ይስማማሉ።3
“ኢህአዴግ አለኝ የሚለውን ጉልበቱን መጠቀም ቢፈልግም መድረኩን ‘በተጠና’ የትግል ስልት በሚፈልገው ደረጃ ሊጠቀም አለመቻሉ በደጋፊዎቹና በራሱ ዘንድ ስጋት ፈጥሯል” የሚሉት አስተያየት ሰጪ “የሙስሊሞች እንቅስቃሴ፣ የዕዝ ሰንሰለታቸውን ጠብቀው የሚያካሂዱት ትግል ኢህአዴግ ጉልበቱን እንዳይጠቀም ከልክሎታል። አሁን እየወሰደ ያለውና የወሰደው የሃይል ጥቃት ሊወስድ ከሚፈልገው ጋር ሲነጻጸር ሃይሉ ሽባ መደረጉን ያሳያል፤ ይህ ደግሞ የሰላማዊ ትግል ውበት ነው” ሲሉ ኢህአዴግ በገባው ጭንቅ መጠን ርምጃ ባለመውሰዱ እንደሚቆጭ ይናገራሉ። በሌላ አነጋገር የሽብር፣ የማሸበርና የመግደል “ጠቢብ” ለሆነው ኢህአዴግ አሁንም ችግሩ የሚፈታው በሃይል፣ በባሰ ሃይል እንደሆነ ከማመን አላፈገፈገም ሲሉ ያብራራሉ።

Friday, August 9, 2013

ደሴን ልክ እንደ ጦር አውድማ ! ደካማዎች ሴቶችና ህፃናት ተጎድተዋል

(ይህ ከደሴ የደረሰን ዘገባ ነው)

ንፁሀን በደላቸውን ለማሰማት በዳዮችም የግፍ ሴራዎችን ሲያጤኑ ከርመው ኢድ ቀን የተወሰነው ፍጥጫ በሙሊሙና በመስጂድ ነጣቂዎች በአሳሪ አሳሳሪዎች በደብዳቢ አስደብዳቢዎቹ ካድሬዎች ዛሬ ቀኑ ደርሶ መንግስታዊ እስልምና አራማጆችና ካድሬዎች ፈጥነው የሰላቱን የመጀመሪ ሶፍች በለሊት ተቆጣጠሩ፡፡ ህዝበ ሙስሊሙ ልክ ከዚህ በፊት እንደሚደረገው የከረጉቱ ሜዳን ሞልቶ ተቀመጠ እዚህ ጋር ነው የተሸረበው ሴራ ፡፡
Dessei_Eid_aug8_2013
የአንድ ሰፈር ሙስሊም ሊያሰግድ የማይችል ሰማይ ቢደፋ የደሴን ሙስሊም ሊይዝ እንደማይችል እየታወቀ ሙስሊሙን ለሁለት ለመክፈልና ካድሬና አህባሾችን ከጥቃጡ ለመጠበቅ ብሎም ከጠባቧ ሜዳ መውጫ እንዳያገኛ ከመስጊዱ ጎን ተደርጎ በማይታወቅ ሁኔታ በአጥር የተከለው ጠባብ ሜዳ ላይ ህዝቡን በፖሊስና ልዩ ሀይል እየፈተሹ ማስገባት ጀመሩ፡፡ ያቺ ጠባብ ሜዳ ሞልታ ህዝቡ በአግራሞት ይመለከት ጀመር፡፡ ከኢድ ሰላት በፊት የሰላተል ጀናዛ ስግደት ነበር፡፡ የተከለለችው ሜዳ ውስጥ ያሉት ወንድሞች ብቻ ሰላቱን ቆሙ ወዲያው የኢዱን ሰላት ኢማሙ ሲጀምሩ ሰፊውና ነባሩ ሜዳ ላይ የተሰበሰበው ህዝብ ተክቢራ ጀመረ በዛች ጠባብ መሬት ላይ ከፊሉ የኢዱን ሰላት ጀምሯል ከፊሉ የወንድሞቹን የእህቱን ቁጣን ያዘለ የተቃውሞ ድምፅ ሰምቶ ከጠባቧ በአጥር የተከበበች ሜዳ መውጣት ጀመረ፡፡

Thursday, August 8, 2013

በአዲስ አበባ ሰላማዊ ሙስሊሞች ላይ ፖሊስ ጥቃት እየፈጸመ እንደሆነ ሰማሁ!


17737_491880560901490_24279230_nበአዲስ አበባ ሰላማዊ ሙስሊሞች ላይ ፖሊስ ጥቃት እየፈጸመ እንደሆነ ሰማሁ!
በአዲስ አበባ ስታድየም አመታዊውን የኢድ በዓል አክብረው እግረመንገዳቸውንም በሰላማዊ መንገድ ተቃውሟቸውን ሲገልፁ የነበሩ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች በፖሊስ የድብደባ ጥቃት እየደረሰባቸው እንደሆነ እየሰማሁ ነው፡፡
በተለያዩ የአዲስ አበባ ክፍሎች እንዲሁም በሌሎች ክልሎች ከኢድ በዓል ጋር ተየያይዞ የተሰማውን ተቃውሞ ለምን አሰማችሁ ያለው መንግስት ርምጃዎችን እየወሰደ ነው፡፡
ሙስሊም ኢትዮጵያውያን በዛሬው ተቃውሟቸው ባለፈው ወቅት አንድ ግለሰብ አሮጌ ባንዲራ ሲያውለበለበ  እያሳየ የድምጻችን ይሰማ አባላት ባንዲራ እንዳቃጠሉ አድርጎ ሲዘግብ የነበረውን የመንግስት ሚዲያ ዘገባ ፉርሽ በሚያደርግ መልኩ በባንዲራ አጊጠው ነበር የወጡት፡፡
መንግስት ጥቃት እየፈጸመ ለው ለምን ባንዲራ ያዛችሁ ብሎ ይሁን፣ ለምን አላህ አክበር አላችሁ ብሎ ይሁን፣ ለምን ድምጻችን ይሰማ አላችሁ ብሎ ይሁን ለማጣራት ያደረኩት ሙከራ የለም… ብቻ ወገኖቻችን በአሁኑ ሰዓት በፖሊስ መከራ እያዩ ነው፡፡

Amnesty International: Ethiopian repression of Muslim protests must stop

August 8, 2013

Amnesty International on Ethiopian Muslims
Young Ethiopian Muslim girl, attacked by Ethiopian government forces during Eid al-Fitr celebrations in Addis Ababa. August 08, 2013
The Ethiopian government must end its use of repressive tactics against demonstrators, following initial reports of widespread arrests of Muslim protestors during this morning’s Eid al-Fitr celebrations, said Amnesty International today.
“We are extremely concerned at reports coming out of Ethiopia this morning of further widespread arrests of Muslim protesters. The Ethiopian government’s  ongoing repressive crackdown on freedom of speech and the right to peacefully protest has to end now,” said Claire Beston, Amnesty International’s Ethiopia researcher.
Last week, another incident related to the protests reportedly ended in the deaths of an unconfirmed number of people in the town of Kofele in Oromia region.

ሰበር ዜና! የፌደራል ፕሊስ እርምጃ እየወሰደ ነው!

August 8, 2013

ድምፃችን ይሰማ
እስከ አሁን ባለው መረጃ በአዲስ አበባ፣ በወልቂጤ፣ በደሴ፣ በአዳማ፣…የመንግስት ታጣቂዎች የዒድ ክብረ በዓልን ለመፈጸም የወጡ ሰላማዊ ዜጎች ላይ ከፍተኛ ኃይል የተቀላቀለበት ድብደባ ፈጽመዋል፡፡ መንግስት ለኢትዮጵያውያን ሙስሊም ዜጎቹ ያለውን ከልክ ያለፈ ጥላቻ በዛሬውም በኢድ በዓል ቀን አሳይቷል፡፡

Ethiopian Muslims
Ethiopian Muslims

Wednesday, August 7, 2013

ሰበር ዜና! የኢትዮጵያ መንግስት ኢትዮጵያ የሽብር ጥቃት ኢላማ ሊሆኑ ከሚችሉ አገራት መካከል ባለመመደቧ ከፍተኛ ብስጭት ውስጥ ገባ!


August 6, 2013
ድምፃችን ይሰማ
ማክሰኞ ሐምሌ 30/2005
መንግስት በመጪው አርብ በኢትዮጵያ የሽብርተኞች ጥቃት ሊፈጸም ስለሚችል ተገቢውን ጥንቃቄ አድርጉ ሲል ለበርካታ ኤምባሲዎችና ቆንስላዎች የቅድመ ማስጠንቀቂያ መልክት (ኬብል) ላከ!
የዩናይትድ ሰቴትስ መንግስት በመላው ዓለም የሚገኙ 22 ኤምባሲዎቹና የቆንስላ ጽ/ቤቶቹ የድንገተኛ ሽብር ጥቃት ሊፈጸምባቸው ይችላል በሚል ባወጣው የቅድመ ማስጠንቀቂያ መረጃ ኢትዮጵያ ባለመካከተቷ የኢትዮጵያ መንግስት ከፍተኛ ብስጭት ውስጥ መግባቱ ታወቀ፡፡ ዩናይትድ ስቴትስ በስለላ መረጃዎች ተመርኩዛ በተለያዩ አገራት በሚገኙ ጥቅሞቿ ላይ በአሸባሪዎች ሊፈጸም ይችላል በሚል ባወጣችው መረጃ 22 አገራት የሚገኙ የአሜሪካ ጥቅሞች ቦታ የተጠቀሰ ሲሆን፤ በእነዚህ ዝርዝር ውስጥ ኢትዮጵያ ውስጥ መሰል የሽብር ጥቃት ሊፈጸም እንደሚችል የሚያሳይ መረጃ ባለመገኘቱ ኢትዮጵያ ሳትካተት ቀርታለች፤ በዚህም መንግስት ከፍተኛ ብስጭት ውስጥ መግባቱ ተረጋግጧል፡፡
Ethiopian Musilms
ይህ ያልተሰበ ጥቃት ሊፈጸምባቸው ነው ተብሎ ዝርዝር ውስጥ የተካተቱ አገራት ውስጥ ያሉ የዩናይትድ ስቴትስ ጥቅሞች አስፈላጊውን ጥንቃቄ ለማድረግ ሲባል እስከ መጪው ቅዳሜ ነሀሴ 4 ድረስ ዝግ እንደሚሆኑ ተነግሯል፡፡ በዚህም መሰረት የአሜሪካ ውጪ ጉዳይ መስሪያ ቤት በአራት አፍሪካ አገራት ማለትም በማዳጋስካር፣ በብሩንዲ፣ በርዋንዳና በሞሪሺየስ የሚገኙ ኤምባሲዎች እንደሚዘጉ ገልጿል፡፡ የአንዳንዶቹ ኤምባሲዎች እና ቆንስላዎች መዘጋት እስከ ፈረንጆቹ ኦገስት ወር መጨረሻ ድረስ ሊዘልቅ እንደሚችልም መስሪያ ቤቱ አስታውቋል፡፡ ሆኖም ይህ የሽብር ስጋት አለባቸው በተባሉ አገራት ውስጥ ኢትዮጵያ መካተት አለመቻሏ በኢትዮጵያ መንግስት በኩል በበጎ ካለመታየት አልፎ ከፍተኛ ቅራኔ እና ብስጭት እንደፈጠረ የዲፕሎማቲክ ምንጮች ገልጸዋል፡፡