(ሠዓሊ አምሣሉ ገ/ኪዳን አርጋው)
በዚህ ርእሰ ጉዳይ ላይ አስቀድሞ ደራሲ በዓሉ ግርማ በኋላም ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ ግጥሞቻቸውን ጽፈው ነበር፡፡ ሌላም የጻፈ ይኖራል፡፡ ነገር ግን እነኝህ የሥነ-ጽሑፍ ሰዎች ግጥሞቻቸውን ሲጽፉ የተቆነጸለ ወይም የተሳሳተ ትርጉም ሊያሰጥ በማያስችል ሁኔታ ግጥሞቻቸውን ባለመጻፋቸው እንደምገምተው እነሱም ሊሉ ባልፈለጉት መንገድ ተተርጉሞ የቅጥረኞች መጠቀሚያ እስከመሆን ድረስ በቃና ሕዝብን ለማደናገሪያ አገለገለ፡፡ ከሕዝቡ ጥቂት የማይባል ወገንም በመወናበድ ይሄንን የተሳሳተ ትርጉም ይዞ ማንጸባረቅ ያዘ፡፡ ይህም መሆኑ ሀገር በሕዝብ ልብ ውስጥ የነበራት ቦታና ትርጉም ከመዛባቱም ባሻገር በወደፊት የሀገር ህልውና ላይ ከባድ አደጋ የጋረጠ ሆኖ ቁጭ አለ፡፡ እናም እንደዜጋ አሳሰበኝና ይሄንን የተሳሳተ ትርጉም ለማረም የሀገርን ትርጉም ሳይቆነጸል ሳይጎነጠል ለማስፈር ተገደድኩና ይህችን ግጥም ጻፍኩ፡፡ ግጥሙ እንዳልኩት የሀገርን ምንነትና ሙሉ ትርጉም ለማስቀመጥ ሲባልና ሁሉም ሰው ሊገባው ሊረዳው በሚችል አገላለጽ ሲገለጽ ትንሽ ሊረዝም ችሏል፡፡ ለዚህ ይቅርታ እጠይቃለሁ፡፡ በግጥሙ ላይ የተገለጹትን ተግሳጾችንና ስድቦችን ሁሉንም በግጥሙ ላይ ከተወከለው ገጸ ባሕርይ ተውሻለሁ ለራሱ ለባለቤቱ መመለስ ይኖሩባቸዋልና፡፡