Tuesday, August 6, 2013

ለዜጎች የሚቆረቆሩ የመንግስት ተወካዮችን አፋልጉኝ!


ኮንትራቱስ ይቁም፣ የቀሩትን ዜጎች መብት ማን ያስከብር?
haile saudi


ሳውዲዎች ከኢትዮጵያ ከኬንያና ከኢንዶኖዥያ የቤት ሰራተኛ ቅጥር ካቆሙ ሰነባበተ! ይህነኑ ተከትሎ የቤት ሰራተኛ እጥረት የሳውዲዎች መነጋገሪያ ሆኗል። ባለጸጎቹ የሳውዲ ዜጎች በያዝነው የረመዳን ወር ብቻ 32 ቢሊዮን ሪያል የሚገመት ገንዘብ በሃገር ውስጥ ገበያ ልውውጥ ላይ እንደዋሉ በሰማን መባቻ የሳውዲዎች ችግር ሆኖ በመነገር ላይ ያለው የቤት የሰራተኛ አቅርቦቱን ጉዳይ ነው። ይህንንም የሃገሪቱ ታዋቂ መገናኛ ብዙሃን ሰፊ ሽፋን ሰጥተው በመዘገብ ላይ ናቸው ። በሰራተኛ አያያዝ በኩል አለም አቀፍ ውግዘት ተለይቷቸው የማያውቁት ሳውዲዎች እንደ ኢትዮጵያ መንግስት ተወካዮች ለዜጎቹ መብት ተከራካሪ የሌላቸውን ዜጎችን ጩኽት መስማት ተስኗቸዋል። “ስብአዊ መብት ገፈፋ ደረስብን!” ሲሉ የዝሆን ጀሮ ይስጠኝ ብለው ይስተዋላሉ ፣ ይህም የሚጠፋው ጥፋት እንደዳይታረም አድርጎታል። የአሁኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ክብር አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እያሉ ከሳውዲዎች ጋር በህግ ማዕቀፍ ሳይስማሙ መንገዱን ከከፈቱት ወዲህ ባለፉት ሶስት አመታት ከግማሽ ሚሊዮን ያላነሱ ኢትዮጵያውያን በኮንትራት ስራ ስም ወደ ሳውዲ ገብተዋል። ሳውዲዎች ከዛሬ ከሶስት አመት በኋላ በአያያዝ ጉድለት ጥፋትና ወንጀል ሲከተል ጤናቸው ተሟልቶ የተቀበሏቸውን ዜጎች በሽተኛ ላካችሁብን እስከሚል ቧልት ተሻግረዋል። ዜጎች ባለፉት አመታት ህጋዊ ተብለው እየመጡ ህገ   ወጥ የመብት ገፈፋ ይፈጸምባቸዋል።
ለዚህ ሁሉ በደል ግን ሳውዲዎችን ብቻ መውቀስ ሚዛናዊ አያደርግም ባይ ነኝ! ይህን የምልበት ዋንኛ ምክንያት ከኢትዮጵያ በኩል የሚላኩት ሰራተኞች ያለ በቂ ቅድመ ዝግጅትና ህጋዊ የሁለቱ ሃገራት የኮንትራት ውል ካለመላካቸው ባሻገር ስለመጡበት ስራ ፣ ስለመጡበት ሃገር፣ አረብኛ ቀርቶ የሃገራችን ብሔራዊ ቋንቋ አማርኛ መናገር የማይችሉ ከገጠሩቱ የሃገራችን ክፍል ተግዘው የመጡ መገኘታቸውን አውቃለሁና ነው! ለ ስራ ያልደረሱ ታዳጊዎች እንደሚላኩ አይቻለሁና ነው! በዚህ መሰል መንገድ የመጡት ዜጎች የት እንደሚገቡ? የት እንደሚድርሱና ምን እንደሚፈጸምባቸው አለመታወቁ ሳውዲ ሲገቡ ክትትል ተደርጎ አይመዘገቡምና ነው! በተባራሪ የምናየው የመብት ገፈፋ በመቶ ሽዎች የሚቆጠሩ ዜጎችን እንደጨው በየ ሳውዲው ገጠር ከተማ ተበትነው ሊደርስባቸው የሚችለውን አደጋና ተደራሽ አለመሆናቸውን በግልጽ ያሳይ ይመስለኛል።  ይህን ስል ሰብአዊ መብታቸው ተጠብቆ በሰላም መስራት የቻሉ በሽዎች የሚቆጠሩ መኖራቸውን ጭምር በመጠቆም ነው። ስለሚደርሰው በደል ስናወራ ግን ከላይ እንዳስቀመጥኩት ለዚህ የመብት ጥሰት ዋና ተጠያቂ አሰሪዎች ቢሆኑም የኢትዮጵያ መግስት ተወካዮች ለተሰየሙበት የዜጎች መብት ጥበቃ ዋና አላማ ትግበራ ዳተኛ መሆናቸው በተጠያቂነቱ ረድፍ ያሰልፋቸዋል። ይህ ዳተኝነትም ችግሩ ከመቀነስ እንዲስፋፋ ምክንያት ሆኗል!

ከኮፈሌ የደረሰኝ መልዕክ እንደወረደ!


1001208_607380952625743_728919177_n
ይህ ፎቶግራፍ በአዲስ አበባ ያለፈው ሳምንት ጁምዓ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን ሲቃወሙ ርምጃ እንዲወስዱ የተላኩ ፌደራል ፖሊሶችን የሚያሳ ነው!
ከኮፈሌ የደረሰኝ መልዕክ እንደወረደ!
ሃይ አቤ ሰላም ነዉ ? ይገርምካል በኮፈሌ ከተማ ዉስጥ እየሆነ ያለዉ ክሰተት ግራ እያጋባን ነዉ; የኢህአዴግ ቅጥር ነፍሰ ገዳዮች ! ሰላማዊዉን ህዝብ ግራ እያጋቡት ነዉ ! በየ ሆቴሉ በየካፌዉ ; በይ ሻይቤቱ ; እየገቡ ዝም በሉ ; በአንድ ላይ ተሰብሰቦ መቀመጥ አይቻልም; እያሉ የመታወቂያ ካርድ ሁሉ እየጠየቁ ነዉ ; እኔ እንደሚመስለኝ ሙሉ የጦር መሳሪያቸዉን ታጥቀዉ በየቤቱ እየገቡ የሰላሙን ህዝብ ቆሌ የሚገፉት ለሌላ ነገር ሳይሆን እንዲህ ስራ ፈተን ከምንቀመጥ ለምን በየቤቱ እየገባን በማሰፈራራት ልጅ አገረድ ሴቶችን አናጠምድም በለዉ በማሰብ ነዉ !! በአሁን ሰአት በተለምዶ ኑ ቡና ጠጡ በሚል ሰም በየ መንገዱ ዳር ቡናቸዉን እየቸረቸሩ የእለት ጉሮራቸዉን ለመሸፈን ና በዚዉ ስራ ቤተሰቦቻቸዉን እየረዱ ያሉ በርካታ የከተማዋ ሴቶች ; አመንዝራ በጠማቸዉ ;በኢህአዴግ ወታደሮች ተከበዋል; በራሳቸዉ ግዜ ምንም የማያዉቀዉን መንገደኛ በመጥራት በያዙት ሰደፍ እየደበደቡ < ቀጥ> ብለክ ሂድ እያሉ ያሳድዳሉ ; ይገርምካል አባቴ እነዚህን ጋጥ ወጥ የሆኑትን የመንግስት ቅጥረኞች ፍረሃት 3 እህቶቼን ወደ ሻሸመኔ ሊልካቸዉ ተዘጋጅቱዋል ;; በአጠቃላይ በከተማዋ ያሉ ሴቶች በፍረሃት ተዉጠዋል ; ነገሩ እንዴት ነዉ ??
አቤ ለህዝብ አቅርበለኝ !
(በዚህ መልዕክት ውስጥ ማስተካከያ ያደረኩት፤ መልዕክቱን ያደረሰችኝ ወዳጄ የወያኔ ወታደሮች ያለቻቸውን እኔ ደግሞ “የኢህሀዴግ” በሚል መተካቴ ብቻ ነው፡፡ ምክንያቱም እንደኔ እምነት ወታደሮቹ የሚወክሉት ወያኔን (ህውሃትን) ብቻ ሳይሆን… ኦህዴዱንም፣ ደህዴኑንም፣ ብአዴኑንም፣ አጋሩንም ነው፡፡ በጥቅሉ የኢትዮጵያን መንግስት ነው!)
አረ ይሄንን መንግስቴን ተው በሉት… እነ እንትናም ጉድ የሆኑት እንዲሁ ሲደርጉ ነው….!

Monday, August 5, 2013

የሚፈራው መጣ!!


ማጣፊያው ሳያጥር ቅድሚያ ለእምዬ ኢትዮጵያ!! (ርዕሰ አንቀጽ)

prayer


ኢትዮጵያችን ታማለች። ኢትዮጵያችን ተወጣጥራለች። ኢትዮጵያችን በአደገኛ መርዝ ተበክላለች። ኢትዮጵያችን ውስጧ ነፍሯል። ኢትዮጵያችን እየቃተተች ነው። ቆዳዋ ሳስቷል። የሚሰማትና የሚደርስላት ስላጣች የያዘችውን ይዛ ልትነጉድ ከጫፍ ላይ ነች። እናም ቅድሚያ ለመቀመጫ፤ ቅድሚያ ለእምዬ ኢትዮጵያ!! ማጣፊያው ሳያጥር ሁሉም መንገዱን ይመርምር!!
ኢትዮጵያ በጭንቀት ጣር ውስጥ ስለመገኘቷ ማብራሪያ የሚጠይቁ ዜጎች ያሉ አይመስለንም። ምናልባት ሳያውቁ እየተፈረደባቸው ያሉ ህጻናት ካልሆኑ በስተቀር፤ ችግር ፈጣሪውም፣ የችግሩ ሁሉ ሰላባ የሆነው ህዝብ፤ ሁሉም ከበቂ በላይ መረጃ አላቸው። ኢትዮጵያ ህመሟ ወደ “ሚድን ካንሰርነት” መቀየር የሚችል ስለመሆኑ ዜጎች ያለ “ሰበር ዜና” ይረዱታል።
የሚድን ስንል በቀላል አገላለጽ ችግር ፈጣሪው ኢህአዴግ፣ የኢህአዴግ ሾፌር ህወሃት፣ የህወሃት አገልጋዮች፣ በህወሃት የበላይነት ከበሮ የሚደልቁ ወንድምና እህቶች፣ ጊዜ የሚያረጅና እራፊ ሆኖ የሚያልፍ የማይመስላቸው የትዕቢት ውጤቶች፣ ይህንን ሁሉ ታግለን “ዴሞክራሲ እናወርዳለን” የሚሉ ወገኖች በልዩነት “አንድ” በመሆን ኢትዮጵያን ለህዝብ ውሳኔ አሳልፈው መስጠት ሲችሉ ነው።
“የጦርነት አባቱ እኔ ነኝ፣ እኔ ከሌለሁ አገር ትከስማለች፣ ኢትዮጵያ በደም ትታጠባለች፣ እኔ ወደ ሰሜን እሸሻለሁ … ” እያለ የቀን ቅዠት ቃዥቶ እወክላቸዋለሁ የሚላቸውን ወገኖች በስጋት ጤና እየነሳ ያለው ኢህአዴግ፣ በተለይም ህወሃት ቀን በጨመረ ቁጥር በእሳት እየተጫወተ ነውና የራሱ ደጋፊዎች ወደ ሰላም መንገድ እንዲመጣ ሊያስገድዱት ይገባል።

በኮፈሌ የሟቾችና ቁስለኞች ቁጥር ግልጽ አልሆነም


በዋቤ መስጊድ ማን ቦንብ አፈነዳ? ለምን?

kofelie


ባለፈው ዓርብ በመላው አገሪቱ አንድ ወጥ የ”ድምጻችን ይሰማ” የተቃውሞ ድምጽ ለማሰማት የወጣውን መርሃ ግብር ተከትሎ የፌደራል ፖሊስ እስከ ግድያ ሊደርስ የሚችል ርምጃ ለመውሰድ እንደሚገደድ የሚያመላክት መግለጫ አውጥቶ ነበር። የድምጻችን ይሰማ አመራር መሆናቸውን የሚገልጹት ክፍሎች ፌደራል ፖሊስ ያወጣውን መግለጫ ተከትሎ ተቃውሞው እንዲቀር መመሪያ ማስተላለፋቸውን ይናገራሉ። በዋቤ መስጊድ ቦንብ ያፈነዳው ማን ነው? ለምን እንዲፈነዳ ተደረገ?
ፖሊስ በከረሩ ቃላቶችና በማስጠንቀቂያ አጅቦ ባወጣው መግለጫ  ” … አክራሪ ወሃቢ ሰለፊዎች ላይ ተገቢውን ክትትል በማድረጉ ፖሊስ ለሚወስደው ርምጃ ተገቢውንና የተለመደውን ትብብር እንዲያደርግ ጥሪያችንን በድጋሚ እናቀርባለን” በማለት አስፈራርቶ ነበር። “ምንደኛ፣ ከውጪ በሚላክላቸው ንዋይ ዓይናቸው ታውሮ አርብ በመጣ ቁጥር በተመረጡ መስጊዶች ሁከትና ብጥብጥ ለመፍጠር ጥረት የሚያደርጉ …” በማለት በመግለጫው አስቀድሞ እንደፎከከረው በኮፈሌ ብቻ ከፍተኛ ሰብዓዊና ቁሳዊ ጥፋት መድረሱ ተረጋግጧል።
አስፈላጊውን ድርጊት መርሃ ግብርና የተቃውሞ ደንብ በማስተዋወቅ ከአዲስ አበባ ለአሜሪካ ሬዲዮ መግለጫ የሰጡት አስተባባሪ ኮሚቴ እንዳሉት አቶ መለስ በህይወት እያሉ በ1997 ተቃዋሚዎች ላይ ርምጃ እንዲወሰድ ከሰጡት ትዕዛዝ ጋር ተመሳሳይነት ያለው መግለጫ በመተላለፉ ተቃውሞው እንዲቀር ተደርጓል።
ሰላማዊ የተባለውን ተቃውሞ ከማከናወን ቢቆጠቡም ከአርብ የጁምአ ስግድት አስቀድሞ በየቤቱ በመዘዋወርና በሰላማዊ መንገድ የአምልኮ ስርአታቸውን ለመፈጸም ወደ ተለያዩ መስጊዶች ካቀኑ ምዕመናን መካከል ቀላል ቁጥር የሌላቸው ታስረዋል። ለቪኦኤ መግለጫ የሰጡት የድምጻችን ይሰማ ተወካይ ካንድ ሺህ በላይ ሰዎች መታሰራቸውን አመልክተዋል።

Saturday, August 3, 2013

ጥያቄው ዛሬም የሕዝብ ጥያቄ ነው! ከኢትዮጵያ ድንበር ጉዳይ ኮሚቴ የተሰጠ መግለጫ


August 3, 2013
ከኢትዮጵያ ድንበር ጉዳይ ኮሚቴ የተሰጠ መግለጫ
ሐምሌ 27 ቀን 2005 ዓ. ም.
የኢትዮጵያ ድንበር ጉዳይ ኮሚቴ የፀረ-ኢትዮጵያው ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) አገዛዝ ለሱዳን መንግሥት በድብቅ አሳልፎ የሰጠውን የእርሻና ከፍተኛ የተፈጥሮ ሃብት ክምችት ያለውን ለም የድንበር መሬት አስመልክቶ በተደጋጋሚ መግለጫዎችን በማውጣት የኢትዮጵያ ሕዝብና የዓለም-አቀፍ ሕብረተሰብ እንዲያውቀውና ሴራውንም እንዲያወግዝ ከፍተኛ ጥረት ማድረጉ ይታወቃል።Ethiopian Territorial Integrity and Ethiopiawinet Sudan annexing Ethiopian Territory
በአገር ውስጥና በውጭ የሚገኙ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች፤ድርጅቶችና የሲቪክ ማኅበራት የወያኔ ገዥ ቡድን ለሱዳን በገፀ-በረከትነት የሰጠውን እርዝመቱ 1600 ኪ/ሜትር የጎን ስፋቱ ከ30 እስከ 60 ኪ/ሜትር የሆነውን የዳር-ድንበር መሬት ጉዳይ እንደ አንዱ ሕዝባዊ ጥያቄአቸው አድርገው እንዲይዙትና ይህ ከኢትዮጵያ ሕዝብ በስተጀርባ የተፈፀመው ውልና ስምምነት ሕገወጥና ተቀባይነት እንደማይኖረው ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ ድምጻቸውን እንዲያሰሙ ማስገንዘባችን የሚታወስ ነው።
ከዚህ መነሻነት፤ ለሱዳን ፕሬዚዳንት ዑመር አል-በሽር፣ ለተባበሩት መንግሥታት ዋና ጸሐፊ ባን ኪ-ሙን፣ለአፍሪካ ሕብረትና ለሌሎች በርካታ ዓለም-አቀፍና አህጉራዊ ድርጅቶች የጉዳዩን አሳሳቢነት በተመለከተ የተለያዩ ደብዳቤዎች በመላክ በሁለቱ አገሮች መካከል የተደረገውን የድንበር ስምምነት የኢትዮጵያ ሕዝብ ሳያውቀው በድብቅ የተደረገ ስለሆነ ተቀባይነት እንደማይኖረው በጥብቅ አሳስበናል።

የግሎባላይዜሽን ውጤቱ

ያበጠው ሲፈነዳ፣ ህብረተሰቦች ሲተረማመሱ! ለኛም ሲተርፈን!! (ዶ/ር ፈቃዱ በቀለ)

globalization_dark


መግቢያ
በዘጠናዎቹ ዐመታት ግሎባላይዜሽን የሚባለው ጽንሰ-ሀሳብ በዜና ማሰራጫዎች ሲወራ፣ ለዓለም ማህበረ-ሰብ ጠቃሚነቱን ለማስረዳት የምዕራብ አገር ኤክስፐርቶች ወዲህና ወዲያ ውርውር ሲሉና የሶስተኛው ዓለም አገሮችም ሊካተቱ የሚችሉበትን ሁኔታ ለመፍጠር ጥድፊያ ሲደረግ፣ በብዙ መቶ ሚሊዮን የሚቆጠር ህዝብ አዲስ የቀን ብርሀንን የሚያይ መስሎት በጉጉት ይጠባበቅ ገባ። ከእንግዲህ ወዲያ ዓለም ወደ „መንደርነት“ እየተለወጠች ነው፤ እዚያ ውስጥ ገብቶ መወዳደርና ብቁነትንም ማሳየት ነው፤ በየቦታው የሚመረተውን ምርት ብቻ ሳይሆን ይህንንም ያሚያሽከረክረውን የፊናንስ ካፒታል ተካፋይ መሆንና በደስታ ዓለም ውስጥ እየተዝናኑ መኖር ነው የሚለው ብዙዎችን ወደ ማሳመን እንደገባ የማይታበል ሀቅ ነው። በመሆኑም ግሎባላይዜሽን አማራጭ የሌለው ነው፤ ይህንን ሀቅ አለመቀበልና በርን መዝጋት ለብዙ መቶ ዐመታት ተኝቶ እንደ መቅረት ይቆጠራል፤ ልናልፈው የማንችለው ታሪካዊ ግዴታ ነው ብለው የኒዎ ሊበራል ኢኮኖሚስቶችና የምዕራብ መንግስታት ለማሳመን የማያደርጉት ግፊትና የማያሰራጩት ዜና አልነበረም። ግሎባላይዜሽን ጥቂቱን የሚጠቅም ሌላውን ደግሞ የሚጎዳ (Zero-Sum game) ነው ብሎ ብዙ ሰዎችን ለማሳመን በጣም ከባድ ነበር። ስለዚህም ግሎባላይዜሽንን የሚቃወሙ፣ ኢኮኖሚያዊ ዕድገትን የሚያዛባና ሀብት በጥቂት ሰዎች ቁጥጥር ስር እንዲውል የሚያደርግ ነው፤ አካባቢ እንዲቆሽሽ የሚያደርግና ህብረተሰብአዊ መመሰቃቀል የሚያመጣ ነው ብለው ለማስተማር የሚጥሩትን እንደ ዕብድ የሚታዩበት፤ ግሎባላይዜሽንን መቃወም ማለት እንዳለ ካፒታሊዝምን መቃወምና እንደ መዋጋት የታመነበት ጊዜ ነበር። በግሎባላይዜሽን አራማጆች ዕምነት እነዚህን ተቃዋሚ ኃይሎች አጥብቆ መዋጋት እንደሚያስፈልግ የታመነበትና ከፍተኛ ቁጥጥር የሚደረግበት ጊዜም ነበር።
ዛሬ በግልጽ እንደሚታየው ግሎባላይዜሽን እራሳቸውን ሰባኪዎችንንም እያስደነገጠ የመጣበት ወቅት ነው። ካለፈው ዐመት ከሰኔ 2007 ጀምሮ በአሜሪካን አገር በግልጽ እየታየ የመጣው በዕዳ የተገዙ ቤቶችና የአበዳሪ ባንኮች ቀውስ፣ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ የአሜሪካ ዜጎች ቤት ገዛን፣ እፎይ ከእንግዲህ ወዲያ ተዝናንተን በቤታችን ውስጥ እንኖራለን ሲሉ ቀውሱ ሳይታስብ የዱብ ዕዳ ሆኖባቸው ቤታችን ነው ከሚሉት ውስጥ እየተፈናቀሉ በመውጣት በመኪኖቻቸው ውስጥ እንዲያድሩ መገደዳቸው፣ ግሎባላይዜሽን የተጠበቀውን ውጤት እንዳላመጣና እንደተወራለት ለሁሉም ደስታን እንዳላጎናጸፈ የዛሬው ተጨባጭ የዓለም ኢኮኖሚ ሁኔታ ያረጋግጣል። መኪኖቻቸውን ወደ ቤቶቻቸው የቀየሩና በየመንገዱ እንዲያድሩ የተገደዱ፣ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ውሾችም ባለቤት አጥተው በየቦታው እንደሚንቀዋለሉ በየሬዲዮውና በየቴሌቪዥኑ የምንሰማውና የምናየው ነው። በአሜሪካን ፣ በካናዳና በሜክሲኮ መሀከል በተፈጸመው የነፃ ንግድ ስምምነት መሰረት የኢንዱስትሪ ባለቤቶች ርካሽ የስራ ጉልበት ለማግኝት ሲሉ ኢንዱስትሪዎቻቸውን እየነቀሉ ወደ ካናዳና በተለይም ወደ ሜክሲኮ በመውሰዳቸው አሜሪካን በብዙ መቶ ሺህ የሚቆጠሩ የስራ መስኮች እንደ ወደሙ የሚታወቅ ነው። ዐይን ተጨፍኖ የታመነበትና የተሰበከለት የነፃ ንግድ መፈክር ብዙ ህብረተሰብአዊ ቀውሶችን እያደረሰ ለመሆኑ ዜናዎችን ለሚከታተል፣ ኤንፎርሜሽኖችን ለሚሰበስብና ለሚመራመር ግልጽ እየሆነለት መጥቷል።

Friday, August 2, 2013

ግመል ሰርቆ ማጎንበስ አይቻልም


meles at g20


የአሜሪካ የውጭ ዕርዳታ ድረገጽ (http://www.foreignassistance.gov/) መረጃ እንደሚለው ከሆነ ከሰሃራ በታች ከሚገኙ አገራት መካከል የአሜሪካንን ዕርዳታ በመቀበል ቀዳሚነቱን ሥፍራ የያዘችው ኢትዮጵያ ነች፡፡
የአስቸኳይ ጊዜ ዕርዳታ ወይም በጀት ከተደረገው ውጪ የሚሰጠውን ተጨማሪ ዕርዳታና ድጎማ ሳይጨምር ከ2009 – እስከ 2012 ባሉት ዓመታት ብቻ ኢትዮጵያ ከ3.3ቢሊዮን ዶላር በላይ (በወቅቱ ምንዛሪ ከ60ቢሊዮን ብር በላይ) ዕርዳታ ተቀብላለች፡፡
ገንዘቡ የሚሠጠው ሰላምና ደኅንነት ለማስጠበቅ፤ ለዴሞክራሲ፣ ሰብዓዊ መብቶችና መልካም አስተዳደር፤ ለጤና፤ ለትምህርትና ማኅበራዊ አገልግሎቶች፤ ለኢኮኖሚ ልማትና ለአካባቢ ጥበቃ እንደሆነ ድረገጹ ያስረዳል፡፡ (በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ የተቀናበረ – AP Photo/Steve Parsons/pool)