Sunday, August 11, 2013

በማሸበር የሚኖሩ በመግደል የሚከብሩ የሰው አረሞች

August 9, 2013

ዳኛቸው ቢያድግልኝ

አረም ማለት ያልተዘራበት የሚበቅል ገበሬ የዘራውን ሰብል የሚሻማ፣ ውሀውን የሚጠጣበት፣ ለበሽታና ተባይ መጠለያ በመሆን ለሰብል ጉዳት ምክንያት የሚሆን እጽዋት ማለት ነው። አረም በስሮቹ አማካይነት የሰብሉን ስር አንቆ የሚገድል፣ አንዳንዱም እንደ ፓራሳይት ሰብል ላይ ተጣብቆ የሚበቅል እንደ አቀንጭራ ያለ ማለት ነው። አረሞች በፈጣን አስተዳደጋቸው ሳቢያ አልሚ ንጥረ ነገሮችን ከመሬት የፀሀይ ብርሃን ከሰማይ በመሻማት የሚያቀጭጩና የሚገድሉ ናቸው። የስንዴ ማሳ ውስጥ የበቀለ በቆሎም እንኳ ቢሆን አረም ነው፣ ገብስም ቢሆን አረም ነውና ተነቅሎ ይጣላል።
Tigray People Liberation Front Split
አረም ዘሩን በማባዛትና የመኖር እድሉን ለማራዘም በርካታ ዘዴዎችን እየተጠቀመ በብዛት የሚንሰራፋና በወቅቱ ካልታረመ ሰብል የሚያጠፋ ነው። ጎበዝ ገበሬ አርሞና ኮትኩቶ ሰብሉን ካልተንከባከበ በሰብል ምርት ምትክ አረሙን ማፈስ ይገደዳል። ልክ እንደ ምሳሌው ኢትዮጵያዊነትን የሰው አረም ውጦታል። ፀረ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት አቋምን የያዘ በሌሎች ስም ይልቁንም በትግሬ ስም ኢትዮጵያዊነት ላይ ተጣብቆ አገር እያፈረሰ ያለ የዘራፊ ቡድን አገርና ሕዝብ እያቀጨጨ ነው። ወያኔ በቆሎና ማሽላ ላይ ተጣብቆ እንደሚበቅል አቀንጭራ (ፓራሳይት፣ ጥገኛ አረም) ኢትዮጵያዊነትን ተጣብቶ ኢትዮጵያን እየገደለ ያለ ቡድን ነውና ተነቅሎ መጥፋት አለበት። በምስሉ የተቀረጹ ‘ኦፖርቹኒስት’ ገንጣዮችና ከፋፋይ ድርጅቶችም እንዲሁ።

Saturday, August 10, 2013

ከፖለቲከኞች በላይ ገኖ የወጣው “ድምጻችን ይሰማ”

ኢህአዴግ አክራሪነትን እየጋበዘ ነው!!


1


”የሰላማዊ ትግል ምንነት ለማይረዱ ትልቅ ትምህርት የሰጠ፣ ኢህአዴግ ፍጹም የሆነ ልምድ ባካበተበትና ኤክስፐርት በሆነባቸው የትግል ስልቶች ብልጫ ወስዶ ለማንበርከክ እንደሚያስቸግር፣ ሰላማዊ ትግል ከራስና ከስሜት ጋር የሚደረግ ታላቅ አስተምህሮት መሆኑን ለማረጋገጥ ተችሏል። የድምጻችን ይሰማ ትግል በዚህ መልኩ በኢትዮጵያ ቀዳሚ ሆኖ ይቆያል” በግል አድራሻ ከተላከ አስተያየት የተወሰደ።
በአሃዝ፣ ጉዳቱ በሚገለጽበት መጠን፣ ጉዳቱ የሚገለጽበት ደረጃና የቋንቋው አቅም ልዩነት ካልሆነ በስተቀር ሁሉም ወገኖች፣ የውጪ ታዛቢዎች፣ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት፣ ራሱ ኢህአዴግ፣ ህወሃትና መላው ወዳጆቹ በአንድ እውነት ይስማማሉ። እሱም ህወሃት ራሱ ባመጣው ጣጣ፣ ራሱ ትዕዛዝ ሰጪ ሆኖ ያደረሰው ሰብአዊና በቀላሉ ሊበርድ የማይችል መከራ እንደሆነ በየአቅጣጫው አስተያየት እየተሰጠ ነው።
ያለ ምንም ማጋነን ኢህአዴግ ደም አፍሷል፣ ህይወት ቀጥፏል፣ አስሯል፣ ገርፏል፣ ፈንክቷል፣ ጣጣው ለሌሎች የሚተርፍ አካሄድ በመከተሉ ችግሩን አወሳስቦታል። ኢህአዴግ ይህንን ሁሉ ርምጃ የሚወስደው “ከብዙ ትዕግስት” በኋላ መሆኑን “በመንግሥት ወግ” ቢገልጽም “የሚያምነው ያገኘ አይመስልም” የሚል ወቀሳም ይሰነዘርበታል። እንደውም “ለየትኛዋ የሚወዳት አገር” በሚል ለፕሮፓጋንዳ አፉን በከፈተ ቁጥር ዘለፋ እየወረደበት ነው።

“ኢህአዴግ ጉልበት አልባ ተደረገ!”

ኢህአዴግ አቅም አልባ ሆኗል የሚሉ ወገኖች አሉ። እነዚህ ወገኖች ገለጻቸው ለሌላው ግራ የሚያጋባ አባባል ሊሆን እንደሚችል ይገምታሉ። ግን በነሱ እምነት ኢህአዴግ አቅም አልባ ሆኗል። አቅም አልባ ያደረገው “የድምጻችን ይሰማ” የትግል ስልት ነው። ኢህአዴግ ያለውና 4የሚታወቅበት መለያው የታጠቀው መሳሪያ፣ ወታደሩ፣ የፌደራል ሃይሉ፣ የክልል ፖሊስ፣ ፈጥኖ ደራሹ፣ የሰላምና መረጋጋቱ ፣ የስለላ ሃይሉ፣ የአጋዚ ጦሩ፣ የአንድ ለአምስት አወቃቀሩ … ከሁሉም በላይ ደግሞ ጉልበተኛነቱን የሚቆጣጠሩለት የአንድ ብሔር “ታማኝ” ሃይሎች መሆናቸው እንደሆነ አብዛኞች ይስማማሉ።3
“ኢህአዴግ አለኝ የሚለውን ጉልበቱን መጠቀም ቢፈልግም መድረኩን ‘በተጠና’ የትግል ስልት በሚፈልገው ደረጃ ሊጠቀም አለመቻሉ በደጋፊዎቹና በራሱ ዘንድ ስጋት ፈጥሯል” የሚሉት አስተያየት ሰጪ “የሙስሊሞች እንቅስቃሴ፣ የዕዝ ሰንሰለታቸውን ጠብቀው የሚያካሂዱት ትግል ኢህአዴግ ጉልበቱን እንዳይጠቀም ከልክሎታል። አሁን እየወሰደ ያለውና የወሰደው የሃይል ጥቃት ሊወስድ ከሚፈልገው ጋር ሲነጻጸር ሃይሉ ሽባ መደረጉን ያሳያል፤ ይህ ደግሞ የሰላማዊ ትግል ውበት ነው” ሲሉ ኢህአዴግ በገባው ጭንቅ መጠን ርምጃ ባለመውሰዱ እንደሚቆጭ ይናገራሉ። በሌላ አነጋገር የሽብር፣ የማሸበርና የመግደል “ጠቢብ” ለሆነው ኢህአዴግ አሁንም ችግሩ የሚፈታው በሃይል፣ በባሰ ሃይል እንደሆነ ከማመን አላፈገፈገም ሲሉ ያብራራሉ።

Friday, August 9, 2013

ደሴን ልክ እንደ ጦር አውድማ ! ደካማዎች ሴቶችና ህፃናት ተጎድተዋል

(ይህ ከደሴ የደረሰን ዘገባ ነው)

ንፁሀን በደላቸውን ለማሰማት በዳዮችም የግፍ ሴራዎችን ሲያጤኑ ከርመው ኢድ ቀን የተወሰነው ፍጥጫ በሙሊሙና በመስጂድ ነጣቂዎች በአሳሪ አሳሳሪዎች በደብዳቢ አስደብዳቢዎቹ ካድሬዎች ዛሬ ቀኑ ደርሶ መንግስታዊ እስልምና አራማጆችና ካድሬዎች ፈጥነው የሰላቱን የመጀመሪ ሶፍች በለሊት ተቆጣጠሩ፡፡ ህዝበ ሙስሊሙ ልክ ከዚህ በፊት እንደሚደረገው የከረጉቱ ሜዳን ሞልቶ ተቀመጠ እዚህ ጋር ነው የተሸረበው ሴራ ፡፡
Dessei_Eid_aug8_2013
የአንድ ሰፈር ሙስሊም ሊያሰግድ የማይችል ሰማይ ቢደፋ የደሴን ሙስሊም ሊይዝ እንደማይችል እየታወቀ ሙስሊሙን ለሁለት ለመክፈልና ካድሬና አህባሾችን ከጥቃጡ ለመጠበቅ ብሎም ከጠባቧ ሜዳ መውጫ እንዳያገኛ ከመስጊዱ ጎን ተደርጎ በማይታወቅ ሁኔታ በአጥር የተከለው ጠባብ ሜዳ ላይ ህዝቡን በፖሊስና ልዩ ሀይል እየፈተሹ ማስገባት ጀመሩ፡፡ ያቺ ጠባብ ሜዳ ሞልታ ህዝቡ በአግራሞት ይመለከት ጀመር፡፡ ከኢድ ሰላት በፊት የሰላተል ጀናዛ ስግደት ነበር፡፡ የተከለለችው ሜዳ ውስጥ ያሉት ወንድሞች ብቻ ሰላቱን ቆሙ ወዲያው የኢዱን ሰላት ኢማሙ ሲጀምሩ ሰፊውና ነባሩ ሜዳ ላይ የተሰበሰበው ህዝብ ተክቢራ ጀመረ በዛች ጠባብ መሬት ላይ ከፊሉ የኢዱን ሰላት ጀምሯል ከፊሉ የወንድሞቹን የእህቱን ቁጣን ያዘለ የተቃውሞ ድምፅ ሰምቶ ከጠባቧ በአጥር የተከበበች ሜዳ መውጣት ጀመረ፡፡

Thursday, August 8, 2013

በአዲስ አበባ ሰላማዊ ሙስሊሞች ላይ ፖሊስ ጥቃት እየፈጸመ እንደሆነ ሰማሁ!


17737_491880560901490_24279230_nበአዲስ አበባ ሰላማዊ ሙስሊሞች ላይ ፖሊስ ጥቃት እየፈጸመ እንደሆነ ሰማሁ!
በአዲስ አበባ ስታድየም አመታዊውን የኢድ በዓል አክብረው እግረመንገዳቸውንም በሰላማዊ መንገድ ተቃውሟቸውን ሲገልፁ የነበሩ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች በፖሊስ የድብደባ ጥቃት እየደረሰባቸው እንደሆነ እየሰማሁ ነው፡፡
በተለያዩ የአዲስ አበባ ክፍሎች እንዲሁም በሌሎች ክልሎች ከኢድ በዓል ጋር ተየያይዞ የተሰማውን ተቃውሞ ለምን አሰማችሁ ያለው መንግስት ርምጃዎችን እየወሰደ ነው፡፡
ሙስሊም ኢትዮጵያውያን በዛሬው ተቃውሟቸው ባለፈው ወቅት አንድ ግለሰብ አሮጌ ባንዲራ ሲያውለበለበ  እያሳየ የድምጻችን ይሰማ አባላት ባንዲራ እንዳቃጠሉ አድርጎ ሲዘግብ የነበረውን የመንግስት ሚዲያ ዘገባ ፉርሽ በሚያደርግ መልኩ በባንዲራ አጊጠው ነበር የወጡት፡፡
መንግስት ጥቃት እየፈጸመ ለው ለምን ባንዲራ ያዛችሁ ብሎ ይሁን፣ ለምን አላህ አክበር አላችሁ ብሎ ይሁን፣ ለምን ድምጻችን ይሰማ አላችሁ ብሎ ይሁን ለማጣራት ያደረኩት ሙከራ የለም… ብቻ ወገኖቻችን በአሁኑ ሰዓት በፖሊስ መከራ እያዩ ነው፡፡

Amnesty International: Ethiopian repression of Muslim protests must stop

August 8, 2013

Amnesty International on Ethiopian Muslims
Young Ethiopian Muslim girl, attacked by Ethiopian government forces during Eid al-Fitr celebrations in Addis Ababa. August 08, 2013
The Ethiopian government must end its use of repressive tactics against demonstrators, following initial reports of widespread arrests of Muslim protestors during this morning’s Eid al-Fitr celebrations, said Amnesty International today.
“We are extremely concerned at reports coming out of Ethiopia this morning of further widespread arrests of Muslim protesters. The Ethiopian government’s  ongoing repressive crackdown on freedom of speech and the right to peacefully protest has to end now,” said Claire Beston, Amnesty International’s Ethiopia researcher.
Last week, another incident related to the protests reportedly ended in the deaths of an unconfirmed number of people in the town of Kofele in Oromia region.

ሰበር ዜና! የፌደራል ፕሊስ እርምጃ እየወሰደ ነው!

August 8, 2013

ድምፃችን ይሰማ
እስከ አሁን ባለው መረጃ በአዲስ አበባ፣ በወልቂጤ፣ በደሴ፣ በአዳማ፣…የመንግስት ታጣቂዎች የዒድ ክብረ በዓልን ለመፈጸም የወጡ ሰላማዊ ዜጎች ላይ ከፍተኛ ኃይል የተቀላቀለበት ድብደባ ፈጽመዋል፡፡ መንግስት ለኢትዮጵያውያን ሙስሊም ዜጎቹ ያለውን ከልክ ያለፈ ጥላቻ በዛሬውም በኢድ በዓል ቀን አሳይቷል፡፡

Ethiopian Muslims
Ethiopian Muslims

Wednesday, August 7, 2013

ሰበር ዜና! የኢትዮጵያ መንግስት ኢትዮጵያ የሽብር ጥቃት ኢላማ ሊሆኑ ከሚችሉ አገራት መካከል ባለመመደቧ ከፍተኛ ብስጭት ውስጥ ገባ!


August 6, 2013
ድምፃችን ይሰማ
ማክሰኞ ሐምሌ 30/2005
መንግስት በመጪው አርብ በኢትዮጵያ የሽብርተኞች ጥቃት ሊፈጸም ስለሚችል ተገቢውን ጥንቃቄ አድርጉ ሲል ለበርካታ ኤምባሲዎችና ቆንስላዎች የቅድመ ማስጠንቀቂያ መልክት (ኬብል) ላከ!
የዩናይትድ ሰቴትስ መንግስት በመላው ዓለም የሚገኙ 22 ኤምባሲዎቹና የቆንስላ ጽ/ቤቶቹ የድንገተኛ ሽብር ጥቃት ሊፈጸምባቸው ይችላል በሚል ባወጣው የቅድመ ማስጠንቀቂያ መረጃ ኢትዮጵያ ባለመካከተቷ የኢትዮጵያ መንግስት ከፍተኛ ብስጭት ውስጥ መግባቱ ታወቀ፡፡ ዩናይትድ ስቴትስ በስለላ መረጃዎች ተመርኩዛ በተለያዩ አገራት በሚገኙ ጥቅሞቿ ላይ በአሸባሪዎች ሊፈጸም ይችላል በሚል ባወጣችው መረጃ 22 አገራት የሚገኙ የአሜሪካ ጥቅሞች ቦታ የተጠቀሰ ሲሆን፤ በእነዚህ ዝርዝር ውስጥ ኢትዮጵያ ውስጥ መሰል የሽብር ጥቃት ሊፈጸም እንደሚችል የሚያሳይ መረጃ ባለመገኘቱ ኢትዮጵያ ሳትካተት ቀርታለች፤ በዚህም መንግስት ከፍተኛ ብስጭት ውስጥ መግባቱ ተረጋግጧል፡፡
Ethiopian Musilms
ይህ ያልተሰበ ጥቃት ሊፈጸምባቸው ነው ተብሎ ዝርዝር ውስጥ የተካተቱ አገራት ውስጥ ያሉ የዩናይትድ ስቴትስ ጥቅሞች አስፈላጊውን ጥንቃቄ ለማድረግ ሲባል እስከ መጪው ቅዳሜ ነሀሴ 4 ድረስ ዝግ እንደሚሆኑ ተነግሯል፡፡ በዚህም መሰረት የአሜሪካ ውጪ ጉዳይ መስሪያ ቤት በአራት አፍሪካ አገራት ማለትም በማዳጋስካር፣ በብሩንዲ፣ በርዋንዳና በሞሪሺየስ የሚገኙ ኤምባሲዎች እንደሚዘጉ ገልጿል፡፡ የአንዳንዶቹ ኤምባሲዎች እና ቆንስላዎች መዘጋት እስከ ፈረንጆቹ ኦገስት ወር መጨረሻ ድረስ ሊዘልቅ እንደሚችልም መስሪያ ቤቱ አስታውቋል፡፡ ሆኖም ይህ የሽብር ስጋት አለባቸው በተባሉ አገራት ውስጥ ኢትዮጵያ መካተት አለመቻሏ በኢትዮጵያ መንግስት በኩል በበጎ ካለመታየት አልፎ ከፍተኛ ቅራኔ እና ብስጭት እንደፈጠረ የዲፕሎማቲክ ምንጮች ገልጸዋል፡፡