Tuesday, November 4, 2014

ጎተራው ወዴት ነው?¡


(ጌታቸው አበራ)

gettera
ሀገር በብረት ሲታጠር — ‘ግንቦት ሃያህ’ ሲከበር፤
አዲስ ዓመት በመጣ ቁጥር — ዘመን በዘመን ሲቀየር፤
የስራ-ፈቶች ስብስብ መንጋ — ‘ፓርላማህ‘ሲከፈት ሲዘጋ..፤
ሱፍህን ገጥግጠህ — ከረባትህን ጠፍረህ፣
ወዝህን አሳምረህ — ካሜራ ፊት ቀርበህ፣
ጉሮሮህን..ጠርገህ — ፊትህ የከመርከውን ‘ሃያ ገጽ’ ገልብጠህ፣
ቁጥር እየቆጠርክ፣ አሃዝ እየጠራህ…፣
“ምናምን..ሺ.ቶን፣ ሚሊዮን ስልቻ፣
አምርተን አስገባን በዚህ ዓመት ብቻ…”፣
እያልክ ስትደሰኩር — ትንፋሽህ እስኪያጥር፣
ሰምቼህ ሳበቃ፣ የግርምት ጥያቄ እስኪማ ልሰንዝር፤
በልበ-ሙሉነት “ጠግብን በላን” ያልከው፣
ሕዝቡን ቆጥረህ ይሆን? ወይስ የቤትህን ያንተኑ ግሳት ነው?!