Saturday, June 14, 2014

የኢትዮ-ኤርትራ የድንበር ጉዳይ ለምን አይቋጭም?


"የለዘብተኞችና የእስስት” ፖለቲካ ልዩነት እየፈጠረ ነው

ethio er
መለስ በሁለቱ አገሮች ድንበር ላይ “የጅራፍ ድምጽ እንኳን አይሰማም” በማለት ሲመጻደቁበት የነበረው የኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት በ”ወረራ” እና “ወረራን መቀልበስ” በሚል ድራማ ተጀምሮ ከተቋጨ አስራ አምስት ዓመት አልፎታል። ኢህአዴግና ሻዕቢያ ጉዳያቸውን በጠረጴዛ ዙሪያ ወይም በጡንቻ መቋጨት ያልቻሉበት ምክንያት ለብዙዎች እንቆቅልሽ ሆኖ እስካሁን አለ። ሁለቱም ወገኖች ድንበር ላይ ወታደር አፍስሰው መቀመጣቸውን አስመልከቶ “አውቀው ነው” ከሚለው ውሃ የማይቋጥርአስተያየት ጀምሮ በርካታ ጉዳዮች በገሃድና በሹክሹክታ ሲሰማ ቆይቷል።
ጎልጉል የዜና ምንጮች ሰሞኑን ከአዲስ አበባ የላኩት መረጃ ግን በይዘቱ የተለየ ነው። ይህንኑ አዲስ ጉዳይ የሚመለከታቸው ክፍሎች አስተያት እንዲሰጡበት ያደረግነው ሙከራ ባይሳካም ዜናው ለውይይት የሚጋብዝ በመሆኑ አትመነዋል
የድንበር ውዝግቡ አንዲቋጭ ይፈለጋል?
የኢትዮ-ኤርትራ የድንበር ውዝግብ ጦርነት ከኢትዮጵያ ወገን ብቻ ከ100 ሺህ በላይ ጉዳዩ በውል ያልገባቸው ወገኖች ህይወት የተገበረበት ነው። የአይደር ትምህርት ቤት ህጻናትን ጨምሮ የበርካታ ሰላማዊ ዜጎችንና ህጻናትን ህይወትም ቀጥፎ አልፏል። አቶ መለስ ለዚህ ሁሉ ቀውስ ተጠያቂ ቢሆኑም በድንገት ተስፈንጥረው ፍርድ ቤት ህግ ሳይጠቀስባቸው አልፈዋል። “ታላቁ መሪ” በህይወት እያሉ በኤርትራ ጉዳይ በተፈጠረ አለመግባባት ትግራይ ውስጥ እስከመታገት ቢደርሱም ከጥንቃቄ ጉድለት በአንጋቾቻቸው ፈጥኖ ደራሽነት ተርፈው ተቃዋሚዎቻቸውን “ውህዳን” በማለት በየተራ አራግፈው ብቻቸውን “ውርስና ቅርስ” ለመሆን በቅተዋል።
ayider
አይደር
ከህንፍሽፍሽ፣ የልዩነት ጊዜ ጀምሮ አደባባይ የወጣው የልዩነት መሰረት በወቅቱ ይፋ ሲደርግ ኢትዮጵያውያንን አሳዝኖና አስቆጥቶ እንደነበር በወቅቱ በስፋት የተዘገበበት ጉዳይ ነው። ዛሬም ይህ ወቅት ዳግም እየተመለሰ እንደሆነ እየተሰማ ነው። “የኤርትራን ጉዳይ እንቋጭ” የሚሉ የከረረ አቋም ያላቸው ተነስተዋል። እነዚህ ወገኖች ሁለት አማራጭ በማቅረብ ሃሳባቸው ተግባራዊ ሊሆን እንደሚችል እየወተወቱ ነው።
የመጀመሪያው አሁን ያለው የመከላከያ አቅም የድንበሩን ውዝግብ በሃይል ለመቋጨት አቅም እንዳለው እየታመነ ለምን “ቸልተኛነት ተመረጠ” በሚል በቂ ጡንቻ ስለመገንባቱ አበክረው የሚከራከሩበት አግባብ ነው። ሁለተኛው ደግሞ “የኤርትራን ተቃዋሚዎች አደራጅተናል፤ ለምን እነሱ ወደ ኦፕሬሽን አይገቡም” የሚል እንደሆነ መረጃዎቻችን ያስረዳሉ።
ቸልተኞቹ ምን ይላሉ?
በዚህ ጉዳይ ቸልተኛ የሚባሉት የተለየ ምክንያት ያላቸው፣ ነገር ግን “ጦርነት አያዋጣም” በሚል በገሃድ የሚከራከሩ ወገኖች ናቸው። እነዚህ ውስን የብአዴንና የህወሃት ቁልፍ ሰዎች በትግራይ ድንበር አካባቢ አስተዳደር የሚሰሩትን ጨምሮ የኤርትራ ደም አላቸው። በደህንነትና በጸጥታ ክፍሉ አጠቃላይ መዋቀር ላይ ቁልፍ ቦታ ተጎናጽፈዋል። የመረጃ ምንጮቹ ማብራሪያ እንደሚያመለክተው እነዚህ ወገኖች “ኢሳያስን የክፉ ቀን መጠባበቂያ” ነው የሚሏቸው። ሰዎቹ ኢህአዴግ ላይ አንዳችም አይነት ስጋት እንደማይሆኑ የሚታወቅ ሲሆን ዋና ዓላማቸው “ከመሃል አገር ወይም ከመካከል ለውጥ ካልተነሳ አርፈህ ተቀመጥ” የሚል ዓይነት መንገድ የሚከተሉ ናቸው።

ያለሽ መስሎሻል ተበልተሽ አልቀሻል


(ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው)

Ethiopia_Crying
ባለፈው ሰሞን አንድ ከ “ሰማእታት” የመታሰቢያ ሐውልቶች ጋር በተያያዘ ታሪክ ቀመስ ጽሑፍ መጻፌ ይታወሳል “አሳ ጐርጓሪ ዘንዶ ያወጣል” እንዲሉ ይህ ጽሑፍ ለንባብ ከበቃ በኋላ በፊት ለምን እንደሆነ በቅጡ የማይገቡኝ የነበሩ እጅግ የሚገርሙ ነገሮች ለምን ይደረጉ እንደነበር ከተለያየ አቅጣጫ በአካልና በመልእክት ካገኘኋቸው ግብረ መልሶች ተረዳሁ፡፡ በዚያ ጽሑፍ ላይ ኦሮሞና ትግሬ ነን የሚሉ ካድሬዎች በተለየ ሁኔታ ትኩረታቸው ተስቦ ነበር፡፡ አንዳንዶችም አነጋግረውኝ ነበር፡፡ በንግግራችን ውስጥ ከዚህ በፊት ያልተረዳኋቸው ነገሮች ግልጽ ሆኑልኝ፡፡ ለነገሩ ያልተረዳኋቸው ማለት ይከብዳል ነገሩ እጅግ የማገርምና ለማመንም የሚቸግር በመሆኑ ሁል ጊዜ እንግዳ ሰለሚሆንብኝና ለጉዳዩ ሁሌም አዲስ እንግዳ ስለሚያደርገኝ ነው፡፡ ባይሆን ስጠረጥራቸው የነበሩ ብል ይሻል ይመስለኛል፡፡
እናም እጅግ ገረመኝ በእርግጠኝነት እንደኔ ሁሉ ብዙው ሰው የሚደረጉ ነገሮች ዓላማቸው የገባው አይመስለኝም፡፡ ወያኔ ለካ አማራን እንዳያንሠራራ አድርጌ ሠብሬዋለሁ እንዳይነሣ አድርጌ አድክሜዋለሁ ብሎ ያምን ኖሯል፡፡ መቸም ሥራቸውን ያውቃሉና ነው እንዲህ ሊያስቡ የቻሉት፡፡ ለካ እንዲያው ሳናውቀው ገለውናል ጃል! ታዲያ እላቹህ እንዲህ ብለው እያሰቡ እያመኑ እያለ ይህ ጽሑፍ በዚያ ቅኝትና ይዘት መጻፉ አማራን በተመለከተ የነበራቸው ግምትና እምነት እንዳሰቡት ሳይሆን ቀርቶ ከ 20ዓመታት ቅጥቀጣና ድቆሳ በኋላ እንደነሱ አባባል እንደዚህ ዓይነት ጽሑፍ በእኔም ብቻ ሳይሆን ከእኔም በኋላ በሌሎች ወገኖችም በአጋጣሚ ተከታትሎ በአንድ ሰሞን በተለያዩ የብዙኃን መገናኛዎች መንጻባረቁና በአንባቢያን መወደዱ ለመግለጽ እጅግ በሚያስቸግር የመደነቅ ድባብ ውስጥ ከቷቸው ነበር፡፡
ይሄን ሁሉ ጉድ የማላውቀው የዋሁ የእግዚአብሔር በግ እኔ ደግሞ መደነቅ መገረማቸውን ሳይ እንዴ ይሄም ኖሯል ለካ ብዬ ሁኔታቸውና አስተሳሰባቸው ሁሉ እኔንም በተራዬ ከከባድ ድንጋጤ ጋር እጅግ እጅግ እጅግ አስደነቀኝ አስገረመኝ አዘንኩም፡፡ እንዲያው ሰው በተለያየ ምክንያት ዝም ሲል ጊዜ እጅ ሰጥቶ ተንበርክኮ መሰላቸውና ጭራሽም እንደሞተ ያህል ቆጥረውት ቁጭ አሉ፡፡ ወያኔ አማራን በተመለከተ አይቅበሩት እንጅ እንደሞተ እንዳበቃለት አድርገው ማሰባቸው ስሕተት እንደነበረ ከመጸጸት ጋር ይቆጩ ይዘዋል፡፡ እነሱ ዘመትንበት አጥፍተነዋል ያሉት ይህ ለሀገር፣ ለቅርስ፣ ለታሪክ፣ ለመለያ፣ ለማንነት፣ ለሃይማኖት ተቆርቋሪ የመሆንን ስሜት ወዴት ተደብቆ እንደተረፈ በአንከሮ እያጠኑት ይገኛሉ፡፡ በተለያዩ የብዙኀን መገናኛች  ለመረዳት እንደቻላቹህት ማኅበረቅዱሳን አንዱ መደበቂያ መሸሸጊያ ነው ብለው በማመናቸው ማኅበሩን ለማፍረስ ለመዝጋት ሴራ እየጠነሰሱ ነው፡፡ በእርግጥ ይህ ማኅበር ከዚህ ቀደምም ቢሆን በወያኔ የዓይነ ቁራኛ የቅርብ ክትትል ስር የነበረ ማኅበር ነው፡፡ ማኅበሩን አቅጣጫውን ለማሳትና ወደ ሚፈልጉት መንገድ ለመውሰድ በርካታ ጥረቶችን ሲየደርጉ ቆይተዋል፡፡

የትግራይ ብሄርተኝነት እንዴት ወደ ፋሽስት ስርዓትነት እያመራ እንደሆነ ለማሳየት እንሞክር (ክፍል 1)


ዶ/ር አሰፋ ነጋሽ
tplf12
የሰው ልጆች አብረው በማህበረሰብ ለመኖር ይቻላቸው ዘንድ ለአብሮ መኖር ፀር የሆኑ ምግባሮችንና ባህሪዎችን ማስቀረት መቻል አለባቸው። አለበለዚያ ማህበራዊ ኑሮ ሊታሰብ አይችልም። ሰውን ከእንሰሳ የሚለየው ከስሜት ባሻገር የማሰብና የማመዛዘን ክህሎቱ ነው። ህሊና አንድ ሰው በጎና ክፉውን፤ መጥፎና ጥሩውን፤ ትክክለኛና ሃሰተኛውን ነገር ለይቶ እንዲያውቅ የሚያስችለውን ችሎታ ወይም ክህሎት አመልካች ነው። የሰው ልጅ የማሰብና የማሰላሰል ልዩ ችሎታ ስላለው በሚኖርበት ማህበራዊ ስፍራ የሚከሰቱትን ነገሮች ሊገነዘብና ሊዳኝ ይችላል። ልጅ ሲያድግ በጎውና ክፉውን እየለየ የሚያውቀው ከአሳዳጊ ቤተሰቦቹ፣ ከጎረቤቱ፣ በሚኖርበት አካባቢ ከሚገኙ ሰዎች፣ ተቋሞች፣ ትምህርት ቤት፣ መስጊድ፣ ቤተ ክርስቲያን ወዘተ ነው። የህሊና ዳኝነትና ለሱ መገዛት መቻል የአንድን ሰው ነፃ መሆንና በራሱ ነፃነት በጎና ክፉውን የመወሰን ችሎታን ያሳያል።
በጎሳ ብሄርተኝነት የተለከፈ አንድ ሰው አንደ ራስ-በቅ (self reliant) ሰው በራሱ ሀሳብና ፈቃድ ተመርቶ ማህበራዊ ህይወቱን ሊመራ አይችልም። በዚህ አይነት በጎሳ ብሄርተኝነት አይምሮአቸው የተመረዙ ሰዎች የግል ማንነታቸው መገለጫ የሆነውን እንደ ሰው የማሰብ ችሎታቸውን ለጎሳ መሪዎቻቸው አሳልፈው ስለሚሰጡ የአንድ በጎሳ ብሄርተኝነት አስተሳሰብ የተመረዙ ሰዎች በሙሉ የጎሳ መሪዎቻቸው የሚነግሯቸውን እየሰሙና እየተከተሉ እንደ አንድ ሰው ወይም እንደ ጎሳ መሪያቸው ማሰብ ይጀምራሉ። ይህ ፈረንጆች “group thinking” የሚሉትና የአንድ አክራሪ የጎሳ ድርጅት ተከታዮች አንድ ወጥ የሆነ አስተሳሰብ (homogenization of thought) ተሸካሚዎች የሚሆኑበት ሂደት ነው። በዚህ ምክንያት በአክራሪ የጎሳ አስተሳሰብ የተመረዙ ሰዎች በጎሳ መሪዎቻቸው ትዕዛዝ(ውሳኔ) ህይወታቸውን እንዲመሩ ይደረጋል። የጎሳ መሪዎቹ የወደዱትን ይወዳሉ የጠሉትን ይጠላሉ። የጎሳ መሪዎቹ የመረጡለትን ነገር ሁሉ አንድ ሰው ለመቀበል ይገደዳል። ምን እንደሚያስብ፤ ከማን ጋር ቡና መጣጣት እንዳለበት፤ ከማን ጋር መወያየት፤ ማንን ማፍቀር ማንን መጥላት፤ በየትኛው የፖለቲካ ስብሰባ ላይ መሳተፍ ወይም አለመሳተፍ እንደሚገባው ወዘተ የጎሳ መሪዎቹ ይነግሩታል። በዚህ አይነት የግል ማንነቱን ያጣ ሰው ይሆናል።

Wednesday, June 4, 2014

አባ ዱላና ከንቲባ ድሪባ የቁም እስረኛ ሆኑ፣ ፓስፖርታቸው ተቀማ


“የኢህአዴግ በርዕዮተዓለም መበላላት ይፋ እየሆነ ነው”

abadulla and deriba
አባ ዱላ ገመዳና የአዲስ አበባ ከንቲባ ድሪባ ኩማ ፓስፖርታቸውን ተነጥቀው የቁም እስረኞች መሆናቸው ከተለያዩ ምንጮች እየወጡ ያሉ መረጃዎች አመልከተዋል። የጎልጉል ምንጮች ግን ኦህዴድ ውስጥ በከፍተኛ አመራሮች ደረጃ እየተካሄደ ያለው ግምገማ ሲጠናቀቅ በርካታ ባለስልጣኖች ክስ እንደሚመሰርትባቸው ተናግረዋል።
በቀድሞው የኦሮሚያ ፕሬዚዳንት አባ ዱላ ገመዳና በአቶ ድሪባ ላይ ይህ ውሳኔ የተላለፈው አገር ጥለው እንዳይወጡ በሚል ነው። ጎልጉል በቅርቡ ካገር መውጣት የማይችሉ ባለሥልጣኖች እንዳሉ ጠቅሶ መዘገቡ ይታወሳል። ውሳኔው የተላለፈው ሰሞኑን የአዲስ አበባን አዲስ ማስተር ፕላን ለመተግበር የኦሮሚያ ክልል ከተሞች መካተታቸው ይፋ መሆኑን ተከትሎ ከተነሳው ተቃውሞ ጋር በተያያዘ ነው። ከሁለቱ ባለስልጣናት በተጨማሪ ከፍተኛ የክልልና የዞን የኦህዴድ አመራሮችም በደህንነት ቅርብ ክትትል እየተደረገባቸው መሆኑ ተሰምቷል። ካገር መውጣት የማይችሉም አሉ።