Saturday, June 29, 2013

ተመስገን ደሳለኝ ለማን ደስ ይበለው ብሎ ጠፋ!?


ተሜተመስገን ደሳለኝ ለማን ደስ ይበለው ብሎ ጠፋ!?
ባለፈው ጊዜ አንድ ወዳጄ ጋር አዲሳባ ስልክ ደውዬ ሳናግረው በአካባቢው ከእርሱ ድምጽ ጎልቶ የሚሰማ የመኪና ጥሩንባ ሰማሁና ይሄ ሁሉ የመኪና ጥሩምባ ምንድነው… ብዬ ጠየኩት፡፡
ሃይለማሪያም ደሳለኝ እየገቡ ወይም እየወጡ ነው መሰለኝ መንገድ ተዘጋግቷል፡፡ አለኝ፡፡
ወዲያውም ቀጠል አድርጎ፤  እንደ ሀቁ ቢሆን ኖሮ መንገድ መዘጋጋት የነበረበት ለሀይለማሪያም ደሳለኝ ሳይሆን ለተመስገን ደሳለኝ ነበር… አለኝና በቁጭት፤ ይሄው የሚያጅቡትን አያቀውቁምና… እልኩ እያታዘብኩ ነው…! ሲል አወጋኝ!
ተመስገን ደሳለኝ ገዢውም ተገዢውም ፓርቲ ሊያመሰግነው የሚገባ ጋዜጠኛ ነው፡፡ ነገር ግን ገዢዎቻችን ማመስገን የሚቆጥር ይመስል ሰውን ማመስገን አይወዱም፡፡  ስለዚህ ተሜንም በማመስገን ፈንታ ከሰሱት፡፡ ጎሽ በማለት ፈንታ እንደ ጎሽ ሊወጉት ቀንዳቸውን አሾሉበት፡፡ እሰይ በማለት ምትክ ሰይ ባንከረባብት ብለው ለሁለቱም አሰቡት፡፡ (ለማሰርም ለማሰደድም) (ሰይ ባንከረባብት በልጅነታችን ብይ ጨዋታ ላይ ተወርዋሪዋ ብይ ጉድጓዳ ውስጥ ብትገባም የተቃራኒውን ብይ ብትመታም ነጥቡ እንዲያዝልን ውል የምንገባባት ቃል ነበረች፡፡)
ተመስገን ደሳለኝ እንዲሰደድ መንግስት ከፀሎት ጀምሮ ሁሉንም አይነት የትግል ስልቶችን እንደተጠቀመበት ትዝ ይለኛል፡፡ ለምሳሌ ባለፈው ጊዜ ምንም የቀጠሮ ወረቀት ወይም መጥሪያ ሳይሰጠው በራዲዮን፤ “ተመስገን ደሳለኝ በሌለበት የፍርድ ሂደቱ ታየ ለሚቀጥለው ጊዜ ፖሊስ ይዞ እንዲያቀርበው ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ ሰጥቷል!” የሚል አይነት ዜና በሰላም ቁጭ ብሎ ሻይ በሚጠጣበት ካፌ ውስጥ ሰማ፤ (እናጋን ካልን ደግሞ ዜናውን እንደውም ያነበቡት ተሜ ልክ ዜና ሲሰማ አይተው ነው…! ማለት እንችላለን…) የዚህ ዜና አላማ ግልፅ ነበር፡፡ ተሜ ደንግጦ ፖሊስ ሳይዘው በፊት መንገዱን እንዲያያዘው ማድረግ ነበር፡፡ ወዳጃችን ግን፤ ብታስሩኝ ባለ ጊዜም ባለ ብረትም ናችሁና እግሬ እምቢ ማለት አይቻለውም፡፡ ለመሰደድ ግን እሺ የሚል እግር የለኝም፡፡ ብሎ እንቅጩን ነገራቸው እና የመጣው ምጣ ብሎ ቁጭ አለ…
በነገራችን ላይ ተመስገን እስከ አሁን ድረስ በመንግስት የተሰነዘረበት ክስ ስፍር ቁጥር የለውም፡፡ እንደው የሪከርድ መዝጋቢ መስሪያ ቤቶች የሚያስታውሳቸው አጥተው እንጂ ከዚህ ሁሉ ክስ ጋር አብሮ መኖር የቻለ ጋዜጠኛ ብለው ድንቃድንቅ መዝገብ ላይ የሚያሰፍሩት ሁሉ ይመስለኛል፡፡ መንግስታችን በክስ ላይ ክስ ሲደራርብ ሲደራርብ ክሱ ተቆልሎ አለመናዱም የእግዜር ተዓምር ነው፡፡ አንዱ ሳይቋጭ አንዱን አንዱ ሳይቋጭ አንዱ ክስ ሲመጣ በአሁኑ ሰዓት ተመስገን ደሳለኝ ከሃምሳ በላይ ክሶች ጋር ተመስገን ብሎ እየኖረ ነው፡፡

ኦባማ – “ዴሞክራሲ ከራባችሁ ኬክ ብሉ”


“ግብረሰዶማዊነት ወደፊት!”

obama in senegal


በድጋሚ ከተመረጡ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ አፍሪካን እየጎበኙ ያሉት የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ በሴኔጋል ጉብኝት ባደረጉት ወቅት የግብረሰዶማውያን መብት ሊከበር እንደሚገባው አስታወቁ፡፡ የአገራቸው ጠቅላይ ፍርድቤት ሰዶማውያንን የሚደግፍ ውሳኔ ሰሞኑን በማሳለፉ ደስታቸውን ገለጹ፡፡ የሴኔጋሉ አቻቸው ግብረሰዶማውያን እንዳይወነጀሉ ለማድረግ አገራቸው ዝግጁ አለመሆኗን ተናገሩ፡፡
ሰሞኑን በአፍሪካ ጉብኝት እያደረጉ የሚገኙት ፕሬዚዳንት ኦባማ ጉብኝታቸውን በጀመሩባት ሴኔጋል የግብረሰዶማውያንን መብት በተመለከተ ለአፍሪካውያንና ለመሪዎቻቸው ማብራሪያና “ትምህርት” ሰጥተዋል፡፡ “መንግሥታት ዜጎቻቸውን እንዴት ሊያስተናገዷቸው ይገባል፤ ሕጉስ እንዴት ሊያያቸው ይገባል ለሚለው ጥያቄ መልሱ ሁሉም ሰው በእኩልነት ሊስተናገድ ይገባዋል” በማለት “ግብረሰዶማዊነት ወደፊት” የሚያስብል ንግግር አድርገዋል፡፡
አፍሪካን እየጎበኙ የሚገኙት ኦባማ የአገራቸው ጠቅላይ ፍርድቤት የግብረሰዶማውያንን መብት ሊያስከብር የሚችል ውሳኔ ማስተላለፉ እንዳስደሰታቸው በጉብኝታቸው ወቅት ጠቁመዋል፡፡ ፍርድ ቤቱ ያስተላለፈው ውሳኔ ለጋብቻ መጠበቅ ከለላ የሚያደርገውን Defense of Marriage Act (DOMA) የተባለው ሕግ ለወንድና ሴት ተጋቢዎች ብቻ በማለት ያስቀመጠው ከለላ የግብረሰዶማውያንን መብት ይጻረራል በማለት ነበር፡፡ ስለሆነም በፍርድቤቱ ውሳኔ መሠረት  በተመሳሳይ ጾታዎች መካከል የተፈጸመ “ጋብቻ” ከፌዴራል መንግሥት የሚሰጡ ጥቅማጥቅሞችን ሊያስከለክል አይገባም በማለት ወንድ ሚስትም ሆነ ሴት ባል ያላቸው ሁሉ የጥቅሙ ተካፋይ እንዲሆኑ ፈቅዶላቸዋል፡፡ እንዲሁም በካሊፎርኒያ ጠቅላይ ግዛት የሰዶማውያን ጋብቻ እንዲቀጥል ፈቃድ የሚሰጥ ውሳኔ ጠቅላይ ፍርድቤቱ አስተላልፏል፡፡

Wednesday, June 26, 2013

“ምስጢር ካወጣህ ቤተሰቦችህን እንፈጃቸዋለን”


“ብዙ አይነት የድብደባና የስቃይ መአት ደርሶብኛል”

tesfaye
June 26, 2013 07:44 am By  Leave a Comment
“የደረሰብኝን ስቃይ ለማንም ብናገር ቤተሰቦቼን በሙሉ እንደሚፈጁ አስጠንቅቀውኛል”
ወጣት ተስፋዬ ተካልኝ በዝዋይ እስር ቤት ለወራት ስቃይ የተፈፀመበት
ወጣት ተስፋዬ ተካልኝ መኮንን ይባላል፤ አርሲ አርባ ጉጉ ተወልዶ አዳማ/ናዝሬት አድጎ፣ በ1998 ዓ.ም ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሶሲዮሎጂ ተመርቋል፡፡ በ2000 ዓ.ም በባህልና ቱሪዝም ሚ/ር በሲኒየር ካልቸራል ኤክስፐርትነት የስራ መደብ እስከ ሚያዝያ 2003 ሰርቷል፡፡ ሚያዝያ 12 ቀን 2003 ዓ.ም በግልፅ ባልተረዳው ምክንያት የመንግስት ደህንነት ሀይሎች ተያዞ ለ23 ወር በዝዋይ እስር ቤት ከፍተኛ ስቃይ እየተፈፀመበት መቆየቱን ይናገራል፡፡ መጋቢት 26 ቀን 2005 ዓ.ም ከእስራት ሲለቀቅም አንድ ጊዜም እንኳን ፍርድ ቤት እንዳልቀረበ ለፍኖተ ነፃነት አስረድቷል፡፡ ከወጣት ተስፋዬ ተካልኝ መኮንን ጋር ያደረግነውን ቆይታ ተከታተሉን፡፡

ፍኖተ ነፃነት፡- ማን ነበር ያሰረህ?
ወጣት ተስፋዬ:- ሚያዝያ 12 ቀን 2003 ዓ.ም በማለዳ ቤቴ ተንኳኳ፤ ተነስቼ ከፈትኩኝ፡፡ የማላውቃቸው ሰዎች ናቸው፡፡ “ና ውጣ፤ ልብስህን ለብሰህ ውጣ” አሉኝ፡፡ እኔ እናቴ ሞታ ሊያረዱኝ የመጡ መስሎኝ “ምነው ቤተሰብ ደህና አደለም? የተፈጠረ ችግር አለ?” አልኳቸው “ዝም ብለህ ናውጣ” አሉኝ፡፡ ልብሴን ለበስኩኝና ወጣሁ፤ አንቀው መኪና ውስጥ ከተው ወደ ማዕከላዊ ወሰዱኝና 3 ወር አሰሩኝ ከዛም አንድ አመት ከ8 ወር ዝዋይ ማረሚያ ቤት፡፡

Tuesday, June 25, 2013

ኦባንግ ከቴላቪቭ ባለስልጣናት ጋር ይመክራሉ


“መኖር አለ፣ መሞት አለና ወደ ህሊናችን እንመለስ"

obang-in-israel-edited


እስራኤል ኢትዮጵያ ውስጥ በህዝብ ፍላጎት የሚመረጥ የተረጋጋ መንግስት እንዲቆም ከመቼውም ጊዜ በላይ የምትንቀሳቀስበት ወቅት ላይ መሆኗን ለማሳሰብ በነገው እለት ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር እንደሚመክሩ አቶ ኦባንግ ሜቶ አስታወቁ። የሒብሩ ዩኒቨርስቲ ምሁራንና ማህበረሰብ ለአቶ ኦባንግ መልክት ድጋፍ እንዲያደርጉ የሚጠይቅ ንግግር ያደርጋሉ። በእስራኤል የሚኖሩ ስደተኛ ወገኖችን አስመልክቶ ቃል እንደተገባላቸውም አመልክተዋል። አቶ ሳሙኤል አለባቸው “መኖርና መሞት ስላለ ወደ ህሊናችን ልንመለስ ይገባል” አሉ።
የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) ዋና ዳይሬክተር የአሜሪካ እንደራሴ (ኮንግረንስማን) ክሪስ ስሚዝ በመሩት የምክክር ሸንጎ ላይ ንግግርና ማብራሪያ ካሰሙ በኋላ ወዲያውኑ በቀጥታ ወደ እስራኤል አምርተው ነበር። ለሁለት ጉዳዮች ወደ እስራኤል ያመሩት አቶ ኦባንግ የኢትዮጵያን ወቅታዊ ሁኔታ አስመልክቶ ከእስራኤል ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር በነገው ዕለት እንደሚመክሩ ለጎልጉል ሲያስታውቁ ስለሚናገሩበት ጉዳይም ፍንጭ ሰጥተዋል።
የሚያገኟቸውን ባለስልጣናት ሳይዘረዝሩ ስለ ምክክሩ የተናገሩት አቶ ኦባንግ “ዛሬ እስራኤል ኢትዮጵያ ላይ ህዝብ አምኖና መርጦ የሚያቆመው መንግስት እንዲመሰረት ከማንም በላይ መስራት እንዳለበት ወቅታዊ እውነቶችን በማንሳት አሳስባለሁ” ብለዋል። “እስራኤል” አሉ ጥቁሩ ሰው “እስራኤል አሁን ባለው የኢህአዴግ ተጨባጭ ሁኔታ ዝምታን አትመርጥም። ዝም ልበል ካለች የመጀመሪያዋ ተጎጂ አገር ትሆናለች። የምንግባባበት ወቅት ላይ ስለደረስን በማስረጃ እንነጋገራለን። ቀና ምላሽ እንጠብቃለን” በማለት አስረድተዋል፡፡hebrew-university
ምክክሩ እንዴት ሊዘጋጅ እንደቻለ ተጠይቀው “እቅድ ተይዞለት የተሰራ፣ ጊዜው ሲደርስ የተደረገ” ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል። በሒብሩ ዩኒቨርስቲ የሕግ ፋኩልቲ ተገኝተው ለምሁራኖችና ተተኪ ፖለቲከኞችና የአዲሱ ትውልድ አባላቶች ንግግር እንደሚያቀርቡ አቶ ኦባንግ አስገንዝበዋል።
በዩኒቨርስቲው በሚያደርጉት ንግግር የሁሉንም ስሜት የሚነካ፣ ከራሳቸውና ከኢትዮጵያ ህዝብ ፍላጎት አንጻር  የወደፊቱን በመተንበይ መንግስታቸው ኢትዮጵያ ላይ ያለውን አቋም በተረጋጋ መሰረት ላይ እንዲተክል የቀረበለትን ጥሪ እንዲቀበል ድጋፍ እንዲያደርጉ እንደሚጠይቁ ታውቋል።
በህንድ አገር ያቀረቡትን የትግል ጥሪ ተቀብለው ካራቱሪ ላይ ዘመቻ የጀመሩ “የመሃትማ ጋንዲ ፍሬዎች“  መገኘታቸውን አቶ ኦባንግ አስታውሰዋል። አሁንም በነጻ አውጪ ሰም አገር እየመራ ያለው ህወሃት እየፈጸመ ያለውን አሰቃቂ ተግባር ናዚ ከፈጸመው ተግባር ጋር እንዲመዝኑት በስፋት በመረጃ የተደገፈ ንግግር እንደሚያደርጉ ከገለጻቸው ለመረዳት ተችሏል። ስራቸውን ካጠናቀቁ በኋላ ዝርዝር ማብራሪያ እንደሚያቀርቡም አመልክተዋል።

Monday, June 24, 2013

ምነዋ ማንዴላ!?


June 24, 2013

የግርጌ ማስታዎሻ : ከዘጠኝ አመት በፊት ያጣሁት አንድ ወንደም ነበረኝ ፣ ጋዜጠኛና ደራሲ መጽሐፈ ሲራክ የሚባል። መጽሐፈ የሃገር ፍቅር ልክፍቱን ብቻ አልነበረም ጥሎብኝ እስከ
Former South African president Nelson Mandela
ወዲያኛው ያሸለበው ፣ የዘመናቸን ታላቅ የጥቁር ህዝብ የነጻነት ታጋይ ኔልሰን ማንዴላን አበክሬ እንዳውቀው የረዳኝ ፣ ለነጻነት ክብር ለዲሞክራ ከቆሙት ጎን እንድቆም ፣ ሰብአዊ መብት ሲዳጥ ዝም እንዳልል፣ የግፉአንን ድምጽ እንዳሰማ የህይወትን ውርስ ያወረሰኝ ወንድሜ ለጥቁር ህዝብ አርበኛው ለኔልሰን ማንዴላ የነበረው ክብር ከፍ ያለ ነበር ! መጽሐፈ “ማንዴላ” እያለ በቀድሞው ለገዳዲ እና የኢትዮጵያ ራዲዮ ተወዳጁ የእሁድ መዝናኛ ተቀኝቶላቸውም ነበር ። ነፍሱን ይማረው እና ዛሬ ያ ወንድሜ በአካል ከእኛ ጋር የለም ! ማንዴላም ሁላችንም እሱ ወደ ሔደበት መጓዛችን ባንቀርም የታለቁ አባትን በጸና መታመም ስሰማ ወንድሜን አስታውሸ ፣ ማንዴላን ለማዘከር በፍጹም ስሜት “ምነዋ ማንዴላ ! ” ብየ ገጠምኩ !

“አሜሪካ አቋማን የምትፈትሽበት ወቅት ላይ ናት” ክሪስ ስሚዝ


"አሸባሪነትን መዋጋት የግፍ ማከናወኛ ሽፋን አይሆንም"
gear 1
June 24, 2013 08:31 am By  Leave a Comment
ኢህአዴግ ሽብርተኝነትን በመዋጋት ስም ከአሜሪካ ጋር የመሰረተውን ግንኙነት አስታክኮ የሚፈጽመው ኢሰብዓዊ ድርጊት ሙሉ በሙሉ ተቀባይነት የሌለው እንደሆነ ተገለጸ። አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ የምትከተለውን ፖሊሲ የምትመረምርበት ወቅት ላይ ትገኛለች ተባለ። ኢህአዴግ ጸረሽብርተኝነትን ለአፈናና ለበጀት ማሟያ እየተጠቀመበት እንደማይቀጥል ተመለከተ።

አሜሪካና ሌሎች ለሰብአዊ መብት መከበር ዋጋ የሚሰጡ አገሮች በሙሉ በ”አዲስ አበባው” አገዛዝ ላይ ጠንካራ አቋም መያዛቸውን ያለ አንዳች ማወላወል ማሳየት እንደሚገባቸው እንደራሴ (ኮንግረስማን) ክሪስ ስሚዝ ያስታወቁት ሽብርተኛነትን አስመልክቶ ጠንካራ ማሳሰቢያ በማስቀመጥ ነው።

እንደራሴ ስሚዝ የኢትዮጵያ ጉዳይ የተደመጠበትን የምክክር ሸንጎ ከዘጉ በኋላ በተለይ ለጀርመን ድምጽ ሬዲዮ በሰጡት ቃለ ምልልስ እንደተናገሩት “አሜሪካ በኢህአዴግ ላይ ያላትን አቋም የምትመረምርበት ወቅት ላይ ትገኛለች” ብለዋል።

Sunday, June 23, 2013

የኢትዮጵያዊያን ትግል


(ከአንዱ ዓለም ተፈራ - የእስከመቼ አዘጋጅ)

eskemechie
June 22, 2013 07:40 am By  Leave a Comment
ክፍል አንድ

የመድረክ የአደባባይ ውይይትን በመንተራስ

የአንድነት ፓርቲ ግምገማዉንና የመድረክ አመራር መልሱን በአደባባይ ማቅረባቸው ታላቅ በር ከፋች ጥረት ነው። አንድነት መድረክን ብቻ ሳይሆን፤ የራሱን አመራር አካላትም ገምግሞ ለኢትዮጵያዊያን ማሳየቱ፤ ብስለቱንና ጥንካሬውን አመልካች ነው። ከመድረክ በኩል የተሠጠውም መልስ፤ በድብቅ ሳይሆን በአደባባይ መውጣቱ የሚያኮራ ነው። እዚህ ላይ አንዱም ሆነ ሁለቱ ትክክል ናቸው ወይንም ስህተተኞች ናቸው ማለቴ አይደለም። ጥረታቸው የሚያኮራ መሆኑን ለመጠቆም ነው። በዴሞክራሲያዊ ማዕከልነት ስምና በፓርቲ አባልነት ግዴታ ማነቆ ልሳናቸው ሳይዘጋ የተጻጻፉበት ምልልስ፤ ትልቅ ትምህርት ለሁላችን ሠጥቷል። እስከዛሬ ያልተለመደው ግልፅነት በሩ ተከፈተለት። ራሳችንን መገምገም ራሳችንን ዝቅ እንደማድረግ ስለሚወሰድና ይኼን ማድረግ እንደተቸናፊነት ስለሚወሰድ፤ ከትናንት ትምህርት የመውሰዱ ሂደት በሩ ዝግ ነበር። አሁን በሩ ተከፈተ። ሀቅ ይረዳል እንጂ ማንንም አይጎዳም። ይኼ ግን ባህላችን አልነበረም። ጥሩ ነገር ስናይ ደግሞ፤ ማንም ይሥራው ማንም ይበል ማለት ተገቢ ነው።

ጉዳዩ የሁላችን ነው

የተወያዩባቸው ጉዳዮች የግላቸው ሳይሆኑ፤ ሁላችን ኢትዮጵያዊያንን የሚነኩና እኩል እንደነሱ ልንወያይባቸው የሚገባ ነው። ትኩረቱ እከሌ እንዲህ አለ፤ ሌላው ደግሞ ይኼን መለሰለት ለማለት ሳይሆን፤ ባደረጉት ምልልስ የተነሱት ነጥቦች በሁላችንም ዘንድ መልስ ፈላጊ በመሆናቸው፤ በየበኩላችን እንድንወያይበት ይገፋናልና የበኩሌን ለመለገስ ነው። አሁንም እንደገና፤ ግልፅ ውይይት ማድረግ በማንኛውም ወቅት የጥንካሬ፣ በተጨማሪም ራስን ደግሞ ደጋግሞ በየደረሱበት ደረጃ መመርመር፤ ለትግሉ ውጤት ያለንን ቁርጠኝነት መለኪያ መሣሪያዎች ናቸው።

ግንቦት 20 ቀን 1983 ዓ.ም. እና ኢትዮጵያ


tplf addis


ወደ ግንቦት 20ቀን, 1983 ዓ.ም. ከመግባታችን በፊት ትንሽ ወደ ኋላ መለስ በማለት የደርግ ስርዓትን በትንሹ እንቃኘው::
ደርግ
የካቲት ወር 1966 ዓ.ም. የዘውድ አገዛዙን ስርዓት በመቃወም በአርሶ አደሩ ፣ በተማሪው ፣ በአስተማሪው ፣ በመንግስት ሰራተኛው ፣ በወዛደሩ ፣ በነጋዴው እና በመለዮ ለባሹ ወዘተ ፣ ወዘተ የተቀጣጠለው ህዝባዊ አመጽ ጊዜ ሳይወስድበት በ6 ወራት ውስጥ የተነሳው ህዝባዊ አመጽ ግቡን መታ::
ህዝባዊ አመጹን የሚመራው የተደረጀ ፓርቲ ባለመኖሩ በር የተከፈተለት መለዮ ለባሽ አመቺ ሁኔታ በማግኘቱ በፍጥነት ተደራጅቶ ከተራ ወታደር ጀምሮ የተለያዩ ማእረግ ያላቸው አባላቱን አስመርጦ ወደ 120 የሚጠጉ ተወካዮቹን አዲስ አበባ በሚገኘው አራተኛ ክፍለጦር አሰባሰበ::
ከጦር ሃይሎች ፣ ከክቡር ዘበኛ እና ከፖሊስ የተውጣጡት እንኚሁ መለዮ ለባሾች በሰኔ ወር 1966 ዓ.ም. ተሰብስበው ብሄራዊ አስተባባሪ ኮሚቴ መስርተው “ኢትዮጵያ ትቅደም ፣ አቆርቋዥ ይውደም” በሚል መርህ ስር ሰፊ ሊባል የሚችል የህዝብ ድጋፍም አግኝተው ነበር::
መስከረም 2 ቀን 1967 ዓ.ም. የተመሰረተው አስተባባሪ ኮሚቴ ንጉሱን ከስልጣን አውርዶ “ጊዜያዊ ወታደራዊ አስተዳደር ደርግ” የሚል ስም በመያዝ ኢትዮጵያን ማስተዳደር ጀመረ:: ቀስ በቀስም ደርግ የስልጣን ወንበሩን በማመቻቸት የሃገሪቷ መንግስት ለመሆን ቻለ::
በወቅቱ በኢትዮጵያም ሆነ በሌሎች ሃገራት ሶሻሊዝም ወይም ህብረተሰባዊነት በሚባል ርዕዮተ አለም እድገት እና ብልጽግና የማይገኝበት “ላም አለኝ በሰማይ ወተቷን የማላይ” ስርዓት በቀድሞዋ ሶቭየት ህብረት እና ቻይና ፕሮፖጋንዳ አለምን እንደማዕበል ሲወዘውዛት የነበረበው ሁኔታ ሆኖ በደርግ የተመሰረተው መንግስት ግራና ቀኙን ሳይመለከት ሶሻሊዝም በኢትዮጵያ ህዝብ የሚፈጥረውን ቀውስ እና ችግር ሳያጤን እና ኢትዮጵያውያን ሊቃውንትን ሳያማክር በ1972 ዓ.ም. ኢሰፓአኮን(የኢትዮጵያ ሰራተኞች ፓርቲ አደራጅ ኮሚሽን) መሰረተ:: ይህንን ምስረታ ተከትሎም ደርግ አንድ እግሩን ገደል ከተተው::

Saturday, June 22, 2013

የትኛው አማራጭ ለአሜሪካ?


“ኢህአዴግን ምን እናድርገው? ንገሩን!”

hearing3


አሜሪካ ከመቼውም ጊዜ በላይ ደንግጣለች። ኦባንግ እንዳሉት ለህዝባቸው “ሬት” ለምዕራባውያንና “ማር” (የቤት ቀጋ፤ የውጭ አልጋ) የነበሩት አምባገነን በድንገት እንደ ተነቀለ ቡሽ ተስፈንጥረው ከሲስተም መውጣታቸው አሜሪካንን አስጨንቋታል። በተለይም እሳቸው አፍነው የያዙት የስርዓቱ “ክፉ ጠረን” አሁን እነርሱ (አሜሪካውያኑ) ደጅ የደረሰ ያህል መፍትሄ ለመፈለግ የወሰኑ ይመስላሉ። አውቀውና ፈቅደው ሲታለሉ የቆዩበትን ጊዜ አስልተው መንገዳቸውን የማስተካከል ስራ የጀመሩት ዛሬ አይደለም። አንዳንድ ምንጮች እንደሚሉት ከመለስ ሞት በኋላ አሜሪካ በምስራቅ አፍሪካ ላይ ሚዛኗን ሊያስታት የሚችል ውድቀት የሚደርስባት ኢትዮጵያ ላይ ያላትን አቋም ማስተካከል ሲያቅታት ብቻ እንደሆነ ይናገራሉ።
“… ሆን ተብሎ በተቀነባበረ እቅድ ህወሃት አዲስ አበባን እንዲቆጣጠር የተወሰነው ውሳኔ አሳዛኝና ከቶውንም ሊታመን የማይችል ነው። የሰከረ ርዕዮት ዓለም የሚከተሉ፣ በብሄርና በጎሳ ፖለቲካ ላይ የተተከሉ ጠባብ ቡድኖች፣ በስታሊናዊ መርህ የተጠመቁ፣ እንኳንስ 50 ሚሊዮን ህዝብ ያላት አገር ቤተሰብን የመምራትና የማስተዳደር ተሞክሮ የሌላቸው፣ አገርን መምራትን የሚያክል ታላቅ ሃላፊነት ማሸከም ለኔ ከአእምሮ በላይ ነው …” የዛሬ 22ዓመት ኮሎኔል ጎሹ ወልዴ ከተናገሩት፡፡
“አሜሪካኖች ነጻ እንድታወጡን አንጠይቃችሁም። የኢትዮጵያ ህዝብ እንዴት ነጻ እንደሚወጣ ያውቃል። እናንተ ግን በነጻነት መንገዳችን ላይ ዕንቅፋት አትሁኑብን፤ (የነጻነት መንገዱን አትዝጉብን)። ከመንገዱ ላይ ገለል በሉ … እስካሁን ያልተሞከረ መንገድ አለ … እሱም እርቅ ነው … ከመንግሥትም ሆነ ከተቃዋሚው በኩል ዓመኔታ የሚጣልባቸው አሉ … ” አቶ ኦባንግ ሜቶ፡፡
“የሚታየኝ ጦርነት ነው፣ የርስ በርስ ግጭት ነው። የርስ በርስ ግጭት በኢትዮጵያ የመነሳቱ ጉዳይ የማይቀር ነው። አገሪቱ ላለፉት 21 ዓመታት በተጓዘችበት መንገድ አትቀጥልም። … ሕዝብ በጭቆና አገዛዝ እየተገዛ ዝም ብሎ የማይኖርበት ደረጃ ላይ ደርሷል … ዝም ብሎ ግን አይቀመጥም … ይፈነዳል … ይህን እንድትገነዘቡ እፈልጋለሁ” ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ፡፡
አቶ መለስ “አሮጋንት /እብሪተኛ/፤ የፈለገውን ነገር በፈለገው ጊዜ የሚያደርግ ሰው … እንደነበር አዲስ አበባ ሄጄ ባነጋገርኩበት ወቅት አረጋግጫለሁ” ክሪስ ስሚዝ፡፡
“እድሜ ልካችሁን አትገዙም ብለን መክረናቸዋል” ዶናልድ ያማሞቶ፡፡
 hearing1የምክክሩ መድረክ
“ኢትዮጵያ ድኅረ መለስ፤ የዴሞክራሲና ሰብዓዊ መብቶች የወደፊት ዕጣ በኢትዮጵያ” በሚል ርዕስ፤ ከኢትዮጵያ ሁለት ተናጋሪዎች ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ እና አቶ ኦባንግ ሜቶ፤ በኢትዮጵያ የአሜሪካን አምባሳደር የነበሩትና በአሁኑ ወቅት በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚ/ር የአፍሪካ ጉዳዮች ተጠባባቂ ጸሐፊ ዶናልድ ያማሞቶ፣ የአሜሪካ የዓለምአቀፍ የልማት ተራድዖ የአፍሪካ ቢሮ ረዳት አስተዳዳሪ ኤሪል ጋስት፤ የማይክል አንሳሪ የአፍሪካ ተቋም ዳይሬክተር ዶ/ር ፒተር ፓሃም እንዲሁም በአምነስቲ ኢንተርናሽናል የመንግሥት ጉዳዮች ዋና ዳይሬክተር አዶቴ አክዌ የተጋበዙበት የምክክር ሸንጎ ላይ የቀረቡት ሃሳቦች በርካታ ጉዳዮችን የዳሰሱ ነበሩ። ሰብሳቢው በአሜሪካ የተወካዮች ምክርቤት በአፍሪካ፣ በዓለምአቀፍ ጤናና ሰብዓዊ መብቶች እንዲሁም ዓለምአቀፋዊ ድርጅቶች ንዑስኮሚቴ ሰብሳቢ ክሪስቶፈር ስሚዝ ደግሞ ኢህአዴግ ከፍተኛ ገንዘብ አፍስሶ ያኮላሽው ኤችአር2003 የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ረቂቅ ህግ ከሟቹ ዶናልድ ፔይን ጋር በማዘጋጀት በምክርቤት ለማስወሰን ያስቻሉ ነበሩ።

Friday, June 21, 2013

The Humanitarian Aid-Corruption Nexus in Ethiopia


(Seid Hassan - Murray State University)

aid and corruption


A.     Introduction
The Amharic version of the Voice of America (journalist Solomon Abate serving as moderator) entertained a discussion on corruption which was broadcast on May 17 and 18, 2013. Participants included Messrs. Mulugeta Aragawi of Addis Ababa University, Abebe Gutta (attorney at law in Addis Ababa), Berhanu Assefa (Ethical Education and Communication Affairs Director of the Federal Ethics and Anti Corruption Commission-FEACC) and I. The first two gentlemen who really knew the sources, extent and potential solution to the rampant Ethiopian corruption politely provided their views, including the approaches that the government has to take to fight the corruption that the government has admitted to be rampant. As expected and is customary of the members of the EPRDF, Mr. Berhanu Assefa of the FEACC was on the defensive and mostly on the attack mode, instead of listening to the complaints and suggestions of the two citizens.  As those who listened to the debate can easily attest, Mr. Assefa spent most of his time talking about unrelated to the topic of discussion –yes, you guessed it right: the same old and tired double digit growth rates that all EPRDFites like to parrot each other ad nauseam.  He also suggested that the current decision to fight against corruption is for real and the arrest of Minister Melaku Fenta, director general of the revenue and customs authority and his deputy Gebrewahed Woldegiorgis along with several officials and businessmen merchants should serve as proof and we ought not to discourage it.  I partially agreed with Mr. Assefa’s suggestion in that all of us have to encourage the fight against corruption, if indeed it is for real while at the same time expressing my serious doubts.

የአባይ ግድብ ዲፕሎማሲ አጀንዳ!


(ግርማ ሞገስ)

Egyptian Foreign Minister Kamel Amr and his Ethiopian counterpart Adhanom attend a session of the talks over the Nile Dam in Ethiopia's capital Addis Ababa
June 21, 2013 07:17 am By  Leave a Comment
በአለም አቀፍ ደረጃ እንደ አባይ ግድብ አወዛጋቢ የሆኑ ጉዳዮች ተፈጻሚነት የሚያገኙት አለም አቀፍ የዲፕሎማሲ ትግል በማድረግ አለም አቀፍ ደጋፊ ማብዛት ሲቻል ነው። የዲፕሎማሲ ትግል ደግሞ ሰላማዊ ትግል ትግል በመሆኑ ብስለት እንጂ ክፉ ቃል አይሻም። ቀረርቶ ደጋፊን አስበርግጎ እንደሚያርቅ እና ለባላንጣ የማጥቂያ ቀዳዳ እንደሚከፍት ግልጽ ነው። የሆነው ሆኖ ይኽን ጽሁፍ እንድጽፍ ያነሳሳኝ የህውሃት ውጭ ጉዳይ ቴዎድሮስ እና አቻው የግብጹ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ሰኔ 11 ግድም ዲፕሎማሲያዊ ውይይት አደረጉ ከተባለ በኋላ ቴዎድሮስ “አብረን እንዋኛለን ወይንም እንሰምጣለን” ማለቱን ካነበብኩ በኋላ በዚህ ጉዳይ ላይ ከኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ኃይሎች ጋር ውይይት መክፈት ያስፈልጋል የሚል እምነት ስላደረብኝ ነው።

“አብረን እንዋኛለን ወይንም እንሰምጣለን” የሚለው የቴዎድሮስ አባባል “ግብጽ እና ኢትዮጵያ ላይፋቱ ተጋብተዋል” ከሚለው የአምባገነን መሰል አባባል ብዙም የራቀ አይደለም። ሁለቱም ህውሃታዊ አነጋገሮች ናቸው። ስሜት በመቀስቀስ ኢትዮጵያውያንን ለማስከተል እና ስልጣን ለማጠናከር። የቀድሞው የህውሃት ውጭ ጉዳይ ስዩም መስፍን በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ወቅት ምን ሲል እንደነበር፣ በመጨረሻ ግን ጦርነቱ እና የባድመ ጉዳይ እንዴት እንዳከተመ እናስታውሳለን። ቴዎድሮስም ከስዩም መስፍን የተለየ አደለም። ትናንት ኤርትራን አስገነጠሉ። በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነትም አብረው ነበሩ። ዛሬም አብረው ናቸው። የሆነው ሆኖ የዲፕሎማሲ ትግል ‘አብረን እንዋኛለን ወይንም እንሰምጣለን” ከሚለው  አባባል ባሻገር እጅግ ሰፋ ያለ ነው። የዲፕሎማሲ ትግል ህግ፣ ፍትህ፣ ታሪክ፣ ሳይንስ፣ ፖለቲካ፣ ኢኮኖሚ፣ ማህበራዊ፣ ሰበዓዊ እና ግብረገባዊ አድማሶች ያሉት የትንታኔ፣ የክርክር፣ የማግባባት፣ የማሳመን ትግል ነው። በተጨማሪ በኢትዮጵያዊነት መንፈስ ከልብ መደረግም አለበት።

“Ethiopia After Meles: The Future of Democracy and Human Rights”


Obang O. Metho's Testimony

obang at hearing


Testimony before the Subcommittee on Africa, Global Health, Global Human Rights and International Organizations
Date:
June 20, 2013
Given by:
Mr. Obang O. Metho, Executive Director
Solidarity Movement for a New Ethiopia
 “Ethiopia After Meles:
The Future of Democracy and Human Rights”
I would like to thank the Chairman of the Committee on Foreign Affairs, Congressman Edward Royce, and all ranking members of the Subcommittee on Africa, Global Health, Global Human Rights and International Organizations for this important opportunity to examine the Ethiopian Government’s observance of democratic and human rights principles in post-Meles Ethiopia.
I want to especially thank Congressman Christopher Smith, the Chairman of the Subcommittee on Africa for his extraordinary leadership in bringing the case of Ethiopia to the attention of this subcommittee once again; particularly in light of the many pressing global issues. In 2006, Congressman Smith worked hard to bring this issue all the way from subcommittee to the House, where it faced obstacles and died. I hope this time, something more concrete and productive can be accomplished for the betterment of both our countries.
In 2006, I gave testimony at that previous hearing in regards to the massacre of 424 members of my own ethnic group, the Anuak, in 2003, perpetrated by members of the Ethiopian National Defense Forces. I also testified regarding the ongoing crimes against humanity and destruction of property and infrastructure in the Gambella region of Ethiopia; however, because similar abuses were being perpetrated in other places in the country, I also spoke of the 193 peaceful protestors who were shot and killed as they peacefully protested the results of the flawed 2005 national election and the repression in Oromia. This also included testimony regarding the imprisonment of opposition leaders, including Dr. Berhana Nega, who is sitting next to me today.
Now I am here once again to testify about these same kinds of issues because Ethiopians have only seen increasing restrictions to their freedom and a continuation of government-sponsored human rights violations in every region of the country. This includes the illegal eviction of great numbers of Ethiopians from their ancestral homes and land, causing great hardship to the people. It also includes egregious human rights atrocities in places like the Ogaden [Somali] region, which is blocked from the outside world by the regime. It has obstructed the media from reporting on the great suffering of the people being perpetrated by government forces, which has been described as a silent genocide. Two Swedish journalists were arrested, detained and charged as terrorists before being released last year.  However, the Ogaden is not alone for every region of the country has become a victim to this regime.

Thursday, June 20, 2013

ቀን የጎደለብን ስደተኞች ቀን!


Boat_loaded_with_Ethiopian_and_Somali_immigrants_in_the_Gulf_of_Aden_yemen
ቀን የጎደለብን ስደተኞች ቀን!
ዛሬ የስደተኞች ቀን መሆኑን ወዳጄ ሰሚር ፌስ ቡክ ላይ ባጋራን ማስታወሻ እና የአልጀዚራ ድረ ገፅ ማስፈንጠሪያ አስታወስኩ፡፡ አንዳንዱ ቀን “እንኳን አደረሳችሁ” ተባብሎ ቢቻል ጠላ ተጠምቆ ድፎ ዳቦ ተደፍቶ እና ዶሮ ወጥ ተወጥውጦ ያከብሩታል፡፡ አንዳንዱ ቀን ደግሞ በሀዘን “ምን ይሻላል ምን ይበጃል” የሚለውን እያንጎራጎሩ ያከብሩታል፡፡ ታድያ “ቀን የጎደለብን ስደተኞች ቀን” በተለይ ለእኛ ኢትዮጵያያን የሀዘን ቀናችን አይደለምን!?
የአልጀዚራ ድረ ገፅ፤ በግብጽ ውስጥ ያሉ ኢትዮጵያውያን የተጋረጠባቸውን ስጋት ያስነብባል፡፡ ግብፃዊያን ሆዬ፤ “ከአባይ ትነኩ እና ደማችሁን ነው የምንጠጣው” አይነት ዛቻ ኢትዮጵያውያን ላይ እየዛቱባቸው እንደሆነ አልጀዚራ ነገረኝ፡፡

ግብፃዊያኑ የሚያደርጉትን ሲያሳጣቸው እንጂ እነዚህ ዜጎች ላይ የፈለጉትን ያህል መጥፎ ነገር ቢያደርሱ የኢትዮጵያ መንግስት ምንም ግድ አይሰጠውም፡፡ መንግስታችን እንደ ሰካራም አባት ነው፡፡ ውጪ ስንደበደብ እንዴት ተመትተህ ትመጣለህ… ብሎ መልሶ ይደበድበናል እንጂ ልጆቼን ለምን ነካችሁ ብሎ ጥያቄ እንኳ አይጠይቅም፡፡

የአባይ ጉዳይ የዛፍ ላይ እንቅልፍ የሆነባት ግብጽ እና ለስልጣን ጸብ ጫሪው ህውሃት!


(ግርማ ሞገስ)

nile dam


የአባይ ጉዳይ ለግብጽ የዛፍ ላይ እንቅልፍ ነው። ዛፍ ላይ ሆነህ እንቅልፍ ይወስድሃል? ሸለብ እንኳን ያደርግሻል ዛፍ ላይ ሆነሽ? እነደዚያ ነው የአባይ ጉዳይ ለግብጽ። ይኽ እንቅልፍ ማጣት እና ስጋት ዛሬ የጀመረ አይደለም። ባጭሩ ልተርክ። ሪቻርድ ፓንክረስት በግብጽ የተገኙ መረጃዎችን መሰረት በማድረግ ክርስቶስ ከመወለዱ ከ3 ሺ አመቶች በፊት ጀመሮ የግብጽ ነጋዴዎች በእግራቸው የአባይን ወንዝ ዳርቻ ተከትለው እንዲሁም በቀይ ባህር በነፋስ በሚገፉ ጀልባዎች ዛሬ ኢትዮጵያ (ያኔ የፐንት ግዛት) በሚባለው ግዛት ውስጥ ከሚኖረው ህዝብ ጋር የንግድ ልውውጥ ማድረጋቸውን እና ግዛቱን ምድረ ታ-ኔትጄሩ (Land Ta-Netjeru) ማለትም “ምድረ አማልዕክት” እንደሚሉት እና “የመጀመሪያ አገራችን ነው” ይሉም እንደነበር የኢትዮጵያውያን ድንበር-መሬቶች (The Ethiopian Borderlands) በሚለው መጽሐፉ ዘርዘር አድርጎ ጽፏል። የቅርቡን ብንመለከት ደግሞ በተለይ ከ1813 ዓ. ም. ጀመሮ ግብጽ የኢትዮጵያ ባለቤትነቷን በጦርነት ለማረጋገጥ የዮሐንስን ኢትዮጵያ ከሱዳን ቀላቅላ ለመግዛት በአራት አቅጣጫዎች ወረራዎች ከፍታ ሳይሳካለት ወደ መጣችበት መመለሷን ተክለ ጻዲቅ መኩሪያ “ዐፄ ዮሐንስ እና የኢትዮጵያ አንድነት በሚለው መጽሐፉ በሰፊው ተርኳል። በኃይለስላሴ እና በደርግ ዘመንም ለኢትዮጵያ ተቃዋሚዎች የጦር መሳሪያ እና ስልጠና በማቀነባበር፣ ገንዘብ በመለገስ፣ በመካከለኛው ምስራቅ አረብ አገሮችን በማስተባበር፣ የአማርኛ ስርጭት ሬዲዮ በመክፈት ድጋፍ ማድረጓን እናውቃለን። ህውሃት ከተጠቃሚዎቹ ተቃዋሚዎች ውስጥ አንዱ ነው። በአባይ ጉዳይ ከጥንት ጀምሮ ግብጽ ከስጋት ነፃ የሆነ እንቅልፍ የለታም። ዛሬም ሆነ ወደፊት ግብጽ የሰላሙን መንገድ ትታ የጸበኛነቱን መንገድ ከመረጠች እንቅልፍ አይኖራትም። ይኽን የግብጽ ጭነቀት እና ስጋት ህውሃት ጠንቅቆ ያውቃል። ስለዚህ ግንቦት 20 ቀን ጸብ ጫረ። ላብራራ።
የጥናቱን ውጤት ተቀበለችውም አልተቀበለችው ስለ አባይ ጉዳይ በጥናት ላይ የተሰማራው ኤክስፐርቶች ቡድን ሪፖርት እየጠበቀች ሳለች ድንገት ግንቦት 20 ቀን 2005 ዓ. ም. ህውሃት የአባይ ወንዝ የፍሰት አቅጣጫ መቀየሩን ሰበር ዜና ተሰራጨ። የኢትዮጵያ ሽብርተኛው ኢ.ት.ቭ. አስተጋባ። ዜናው ግብጽ ደረሰ። ከጥንት ጀምሮ የአባይ ጉዳይ የዛፍ ላይ እንቅልፍ የሆነባት ግብጽ ተደናገጠች። አምባገነኑ ሞርሲ ከገበባት የውስጥ ችግር ለማምለጥ የህውሃትን ቁስቆሳ ተጠቀመ። አካራሪ የግብጽ ተቃዋሚ ፖለቲከኞችን ጋበዞ ‘እኔ ሳልሞት ግብጽ አትጠማም’ አለ። ያጀቡት አክራሪዎችም ‘ግፋ’፣ ‘በርታ’፣ ‘አይዞህ ከጎንህ ነን’ አሉት። ይኽ  ምክክራቸው ዜና ሆኖ አደባባይ ወጣ። ህውሃት ሁካታውን ያልጫረ መስሎ ለኢትዮጵያ ህዝብ ግብጽ ልትወጋህ ነው የሚል ፕሮፖጋንዳ ጀመረ። የቀድሞ አባቶቻችን ድሎች ሳይቀሩ እየተጠቀሱ የቀረርቶ ድምጽ በአዲስ አበባ እየጎላ መጣ። አልባራዳይን የመሰሉት የግብጽ ዴሞክራሲ ኃይሎች የግብጽን መንግስት ወቀሱ። የኢትዮጵያ ዴሞክራሲ ኃይሎችም ቀረርቶው ገደብ ይበጅለት አሉ። የኢትዮ-ግብጽ የጦርነት ሁካታ አነሳሱ ይኽን ይመስል ነበር። ህውሃት የማያስፈልግ ጸብ ጭሯል።

Wednesday, June 19, 2013

ከአረብ ሃገራት ሰማይ እስከ ሚሊንየም አዳራሽ!


frontJune 19, 2013 08:03 am By  Leave a Comment

እኔን ያሰፈራኝ ጎርበጥባጣው መንገድ . . .  ኢትዮጵያውያን በግብጽ . . .ሰሞነኛ የማለዳ ወጌን ወደ እናንተ ላደርስ አንዱን አንስቼ አንዱን ስጥል አንድ ወዳጀ ስልክ ደውሎ በግብጵ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የአባይን ግድብ ውዝግብ ተከትሎ አደጋ ላይ መሆናቸውን መረጃ ቢጤ አቀበለኝ ። በማስከተልም ከጥቆማ መረጃው ጋር በቀጣዩ ቀን ነዋሪዎች በነቂስ ሰላማዊ ስልፍ ለማደረግ እንዳቀዱ በመግለጽ እንዳነጋግራቸው መከረኝ ። መረጃ ለመሰብሰብ የሚረዱኝን ወንድሞች አድራሻ የሰጠኝን ወንድም አመስግኜ ወደ ሃገረ ግብጽ ካይሮ ደጋግሜ ደወልኩ። ከብዙ ጥረት በኋላ ግን የፈለግኩትን መረጃ ሙሉ በሙሉ ባላገኝም ያገኘሁትን ሰባስቤ ለተጨማሪ መረጃ የሚረዱኝን ተጨማሪ ስልክ ቁጥሮች ሰባሰብኩ። ያሰባሰብኳቸው መረጃዎች ግን ለኢትዮጵያ መጻኤ ህይወት እንድሰጋ እንድፈራ አድርገውኛልና ፈራሁ! ልቤ እንቢ እያለኝ ጥረቴን ገፋሁበት  . . . “ (ሙሉው ጽሁፍ እዚህ ላይ ይገኛል)

Tuesday, June 18, 2013

የሙስና ምርመራ እየተወሳሰበ ነው!


"መበላላት እንዳይጀመር ስጋት አለ"

sheraton
June 18, 2013 08:08 am By  Leave a Comment
በጉምሩክና ገቢዎች ባለስልጣን የተጀመረው የጸረ ሙስና ዘመቻ ተከትሎ እየተካሄደ ያለው ምርመራ እየተወሳሰበ መሔዱ ተሰማ። በከፍተኛ የሙስና ወንጀል የተጠረጠሩ ተከሳሾች የሚሰጡት መረጃ መበላላት ያስነሳል የሚል ፍርሃቻ እያስነሳ ነው። “ሰፈር የለየው” የጸረ ሙስና ዘመቻ የፈጠረው ስጋት የሃይል ሚዛን የያዙትንም ስጋት ውስጥ ከትቷል።

በኢትዮጵያ ባለፉት 10 ዓመታት ውስጥ የታየው የውስን ሰዎች በድንገት በመበልጸግ ከባለስልጣኖችና ከከፍተኛ የስርዓቱ ሰዎች ቤተሰቦች ጋር በሚከናወን መተሳሰር አማካይነት እንደሆነ ከህዝብ የተሰወረ አይደለም። ሰሞኑንን ይፋ የተደረገው የባንክና የንብረት እግድ እንዳመለከተው የዝርፊያው ሰንሰለት በቤተሰብ የታጠረ መሆኑን ነው።

አቶ መለስ ከድነው ያቆዩትና የሳቸውን ሞት ተከትሎ ከፖለቲካው ልዩነት ጋር በተያያዘ እንደተጀመረ የሚነገርለት የጸረ ሙስና ዘመቻ፣ በመንግስት በኩል “ቆራጥ” አቋም የተያዘበት እንደሆነ ቢነገርም አስጊ ሁኔታ እየተፈጠረ ስለመሆኑ የጎልጉል የጸረ ሙስና ኮሚሽን ምንጮች ይናገራሉ።

Monday, June 17, 2013

የቢሮ ኃላፊው በሙስና ላይ ምስክር ሳይሆኑ ተገደሉ


“ብዙ ሳይታወቅ የተገደሉ ተስፋዬዎች አሉ”

food
June 17, 2013 07:55 am By  1 Comment
በነበራቸው የስራ ሃላፊነት በድብቅ መረጃ ሲያሰባስቡ ቆይተው ለመንግስት ካጋለጡ በኋላ ራሳቸውን ደብቀው የነበሩት አቶ ተስፋዬ ኢሬሣ ምሳ እየተመገቡ ህይወታቸው ማለፉ ተሰማ። አቶ ተስፋዬ ሰኞ ለጸረ ሙስና ኮሚሽን የምስክርነት ቃላቸውን ለመስጠት ከኮሚሽነር አሊ ሱሌማን ጋር ቀጠሮ ይዘው ነበር።

በቅርቡ ወደ ፌደራል መንግስት የተዛወሩት የጋምቤላ የቀድሞ ፕሬዚዳንት የነበሩት አቶ ኡሞት ኦባንግ፣ ከ83 ሚሊዮን ብር በላይ አላግባብ ለግል ጥቅማቸው ማዋላቸውን፣ እንዲሁም በክልሉ የሚፈጸሙትን የተጭበረበሩ የበጀት አፈጻጸሞችንና ምዝበራዎችን የሚያጋልጡ ሰነዶችን በሚስጥር በማደራጀት ለኢህአዴግ ያቀረቡት አቶ ተስፋዬ አሟሟታቸው አነጋጋሪ ሆኗል።

አቶ ተስፋዬ ኢሬሳ ከፍተኛ ምስጢር ያላቸውን ሰነዶች በመያዝ ከመታሰራቸው በፊት መሰወራቸውን፤ “የቢሮ ሃላፊው ይዘው የተሰወሩት መረጃ አቶ ኦሞት የፈረሙባቸው ከፍተኛ የገንዘብ ሰነዶችና ሙስና የተከናወነባቸው የኮንስትራክሽንና የተለያዩ መረጃዎች ናቸው። መረጃዎቹ አንድ ቀን ህዝብ ፍርዱን ይሰጥ ዘንድ ይፋ ይሆናሉ” በሚል ጎልጉል ምንጮቹን ጠቅሶ በ (ጥቅምት 19፤2005/October 29, 2012) መዘገቡ ይታወሳል

Sunday, June 16, 2013

አገር በቤተሰብ ስትዘረፍ ኢህአዴግ የት ነበር?


“አዲስ አበባ የተገተሩት ህንጻዎችስ?”

የሁለት አገር ነዋሪዎችJune 15, 2013 03:49 am By  Leave a Comment

በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉት ባለስልጣናት፣ ባለሃብት፣ ደላሎችና ባለድርጅቶች በልጆቻቸውና በቤተሰቦቻቸው ስም “ዘርፈው አስቀመጡት” የተባለው ንብረታቸውና የባንክ ሂሳባቸው መታገዱ ታወቀ። የዜናውን ይፋ መሆን ተከትሎ አዲስ አበባን ያጥለቀለቋት ህንጻዎችና የንግድ ድርጅቶች ጉዳይ ለምን ዝም ተባሉ የሚል ጥያቄ እየተሰነዘረ ነው።

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ምክትል ፕሬዚዳንት የነበሩት አቶ ነጋ ገብረ እግዚአብሔር 54 ተሽከርካሪዎች ተይዘውባቸዋል። ገንዘቡን ሳይጨምር 54 ተሽከርካሪዎች በስማቸው ተመዝግበው የተያዙባቸው አቶ ነጋ ፣ የወ/ሮ አዜብ መስፍን የንግድ ሽሪክ እንደሆኑ የሚያውቋቸው ይገልጻሉ። 

በኢህአዴግ ጉባኤዎች ላይ የማይቀሩት አቶ ነጋ በየስብሰባው ወቅት ሻይና ቡና ሲሉ ከወ/ሮ አዜብ ጋር አብረው እንደሆነ የሚገልጹት ታዛቢዎች፣ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን “አትሌት ናቸው” በሚል ወደ ውጪ በጉቦ የላካቸው ሰዎች ጉዳይም ከሳቸው ጋር እንደሚያያዝ ይጠቁማሉ።  ከጨው ንግድ፣ ከካሜራ ፊልም ብቸኛ አስመጪነት ሌላ በአሁኑ ወቅት ሂልተን ጀርባ፣ አዲስ አበባ ስታዲየም ቪክ ሬስቶራንት ጎን ግዙፍ ህንጻ ያስገነቡት አቶ ነጋ ቃሊቲ ባላቸው የነዳጅ ማደያ የከፈቱት ብቸኛ የክብደት መለኪያ/የከባድ የጭነት መኪኖች የክብደት መለኪያ “የገንዘብ ማምረቻ ማሽን” አግባብነት የሌለው ቢዝነስ እንደሆነ ቅሬታ ሲቀርብበት የቆየ የግል የንግድ ተቋማቸው ነው። ቀደም ሲል ከኤርትራዊያን ጋር አብረው ሲሰሩ የነበሩት አቶ ነጋ ሃብታቸው በድንገት የተመነጠቀው ከ1991 ኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ጀምሮ እንደሆነ የሚያውቋቸው ይናገራሉ።

Friday, June 14, 2013

ይድረስ ለአባይ ባለበት… (ከአቤ ቶኪቻው)


June 13, 2013
አቤ ቶኪቻው
ጉዳዩ፤ በጣም አበዛኸው…!

Abe Tokichaw's letter to Abbay (Nile) River.
ይቺ ለአባይ የተፃፈች ደብዳቤ ናት፡፡ አፃፃፏ “ስዲ ወ ግጥሚ” አይነት ናት፡፡ ትንፋሽ ያለው ሰው እንደ ግጥም ቢወርዳት ግጥም ግጥም ትመስላለች፡፡ ትንፋሽ የሌለው ሰው ደግሞ እንዲሁ ቢዘልቃት ስድ ንባብ ትሆናለች፡፡ እስቲ እንደዚህ አዳዲስ ፈጣራዎችን እናስተዋውቅ… ብዬ አካብጄ በአዲስ መስመር እጀምራታለሁ ትድላችሁ…!!
ውድ አባይ፤ ከእናታችን ማህጸን ተገኝተህ ገና በቅጡ ሳትጠና እና ሳትጠናና በልጅነት አፍላ ፍቅር ድንገት አየተሃት ከወደድካት ግብጽ ጋር ከተጋባህባት ዕለት አንስቶ ለጤናህ እንደምን አለህ… ከቶ!
እኛስ እንዳለን አለነው፡፡ አንተን ያኽል ወንድም፤ አንተን ያኽል አጋር፤ ውጪ ሀገር የሚኖር ታላቅ፣ እጅግ ታላቅ፣ ሃብታም የናጠጠ፤ ጥሩ ስርፋ ደህና ቦታ ይዞ የተቆናጠጠ፤ ዘመድ ቢኖረንም ዛሬም አልጠገብንም፡፡ ዛሬም አልወዛንም፡፡ ዛሬም አልወፈርንም፡፡ እንዲሁ እንደቀጠን፣ እንዲሁ እንደራበን፣ አመድ እንደመሰልን አለን አባይ፡፡ እንዲሁ አለን፡፡

Wednesday, June 12, 2013

አባይ የፖለቲካ ግለት ማብረጃ ወይስ?


June 12, 2013
ጥላሁን ዛጋ
አባይ መነሻ ምንጩን ሰሜናዊ የኢትዮጵያን ክፍል በተለይም ጣና ሃይቅንና በዙሪያው ያሉ አፍላጋት አድርጎ ረጅም ጉዞውን ጣና ሃይቅ ላይ በሚፈጥረው ንብርብሮሽ የአለምን ህዝብ በሙሉ አስደምሞ ይጀምራል፣ እግረ መንገዱን ሌሎች ገባር ወንዞችን በጉያው ሸክፎ እስከሜዲትራኒያን ባህር ያለውን በማይልስ የሚቆጠረውን የርቀት ጉዞ ይቆርሰዋል፣ በ75᎖912 ስኩዌር ኪሎሜትር የተፋሰስ ስፋትና በ23᎐6 ቢሊየን ሜትርኪዩብ አመታዊ አማካይ የፍሰት መጠን ጋምቤላንና ሌሎች የኢትዮጵያን ሰሜናዊ ክፍሎች የሚያዳርሰው ባሮ ወንዝ እንዲሁም በ82᎖350 ስኩዌር ኪሎሜትር የተፋሰስ ስፋትና በ9.6 ቢሊየን  ሜትር ኪዩብ አመታዊ አማካይ የፍሰት መጠን ከላስታ ተራሮች ተነስቶ ወደምዕራብ በመፍሰስ እንደገና አቅጣጫ ቀይሮ ወደ ሰሜን የሚመለሰው የተከዜ ወንዝ በአባይ ጉያ የሚሸከፉ ዋናዎቹ ገባሮች ናቸው።
በመሆኑም አባይ ይህን የታላቅነት ግርማውን እንደያዘ ያለከልካይ ለዘመናት ሲፈስ የኖረና የህብረ-ኢትዮጵያዊነት መገለጫ እንዲሁም የሁሉንም ብሔር-ብሔረሰቦች ስሜት በአንድነት የሚነካ የኢትዮጵያ ወንዝ ነው። እንደየክፍለዘመኑ እንዲሁም  ማህበረሰባዊ የእውቀትና ብስለት ደረጃ ሁሉንም ኢትዮጵያዊ ያወያየ፣ ያነጋገረና ያከራከረ ስሜት ቀስቃሽና የሀገር ወዳድነትም መገለጫ ሆኖ ለዘመናት የዘለቀ ወንዝ ነው፣ በተመሳሳይም በሀገራችን በተለያዩ ጊዜያት የተነሱ መሪዎች ለፖለቲካቸው ውበት ማድመቂያ እንዲሁም ለኢትዮጵያዊነታቸው መሃላ ማህተም ሆኖላቸው ቆይቶአል።

Saturday, June 8, 2013

ኢህአዴግ ጣና በለስን ለምን አፈራረሰው?


"በሩ ይከፈት፣ በአባይ ጉዳይ አገራዊ አቋም እንያዝ"

BELES inlet
June 8, 2013 02:31 am By  Leave a Comment
በግብጽ ረዳትነት፣ በሱዳን መሪነት መንግስት ለመሆን የበቃው ህወሃት/ኢህአዴግ ግዙፉን የጣና በለስ ፕሮጀክትና ንብረቱ እንዲዘረፍ ያደረገበትን ምክንያት በማንሳት መከራከር እንደሚያስፈልግ ተጠቆመ። የግብጽ ፕሬዚዳንት ሙርሲ እንዳደረጉት በአገር ጉዳይ ሁሉንም ያሳተፈ ግልጽ አቋም እንዲያዝና አጋጣሚውን በመጠቀም ብሔራዊ ህብረት እንዲፈጠር ኢህአዴግ በሩን ሊከፍት እንደሚገባ ተገለጸ።

በተለያዩ ጉዳዮች ምክንያት ስማቸው እንዳይጠቀስ በማሳሰብ ለጎልጉል አስተያየት የሚሰጡት የኢህአዴግ ሰው እንዳሉት በርካታ ጉዶች ያሉበትን የአባይን ግድብ ተከትሎ ከግብጽ ጋር የተነሳው ውዝግብ አስቀድሞ የሚታወቅ የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ ስልትና ውጤት ነው።

አሁን ድረስ አገር እየመራ በነጻ አውጪ ስም የሚጠራው ህወሃት/ኢህአዴግ አዲስ አበባ ሲገባ “ዲሞክራሲ አመጣሁ” በማለት ኢትዮጵያን መምራት እንደጀመረ የሚያወሱት የኢህአዴግ ሰው፤ አቶ መለስ ብቻቸውን ይነዱት የነበረው ኢህአዴግ እንደፈለገ ቆዳውን እየቀያየረ የተጠቀመበትንና በእስስት በመመሰል “ከሽፏል የሚሉትን” ስልት ያብራራሉ።

በዲሞክራሲ ስም የተጀመረው የኢህአዴግ አገዛዝ ቆየት ብሎ “ልማታዊ ነኝ፣ ልማት ግቡን የሚመታው በአብዮታዊ ዲሞክራሲ ቀመር ነው” በማለት ፕሮፓጋንዳውን አሰፋ። የልማት ህልመኛነቱ ሲነቃበት “የትራንስፎርሜሽን ዘመቻ” በማለት አዲስ የፕሮፓጋንዳ እቅድ ነድፎ ህዝብና አገር ሲያታልል ቆየ። ይህም አላራምድና በህዝብ የመታመን ድል ሊያስገኝለት እንደማይችል ሲታመን “የህዳሴያችን ግድብ” ተብሎ አባይ አጀንዳ እንደተደረገ ያመለከቱት ዲፕሎማት፤ “ኢህአዴግ አገር ውስጥ የሚያምታታባቸው መንገዶች ሲጠናቀቁበት የፕሮፓጋንዳውን ዘመቻ አንድ ደረጃ ከፍ አደርገው” በማለት አሁን ከግብጽ ጋር ስለተጀመረው ውዝግብ አስተያየታቸውን ይጀምራሉ።

Thursday, June 6, 2013

በሰላማዊ ሠልፉ ሰማያዊ ፓርቲና መንግሥት እየተወዛገቡ ነው


selfegnoch
June 6, 2013 08:09 am By  Leave a Comment
ሰማያዊ ፓርቲ ከአንድ ወር በፊት በጠራውና ባለፈው እሑድ የተደረገውን ሰላማዊ ሠልፍ መንግሥት ሲያወግዝ፣ ሰላማዊ ፓርቲ ደግሞ የመንግሥት ውግዘት በተቃውሞ የተነሳውን ሕዝብ ከማሸማቀቅ ባለፈ የሕግ ድጋፍ እንደሌለው እየገለጸ ነው፡፡

ሰማያዊ ፓርቲ ሚያዝያ 29 ቀን 2005 ዓ.ም. ባስተላለፈው የሰላማዊ ሠልፍ ጥሪ፣ ግንቦት 25 ቀን 2005 ዓ.ም. በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጐች ወጥተው ተሰተውለዋል፡፡ አራት ኪሎ ቀበና አካባቢ ከሚገኘው የሰማያዊ ፓርቲ ጽሕፈት ቤት መነሻውን ያደረገው ሰላማዊ ሠልፉ በአራት ኪሎ፣ በፒያሳና በቸርችል ጐዳና አድርጐ ኢትዮ ኩባ የወዳጅነት መናፈሻ ደርሶ፣ እስከ ቀኑ ስምንት ሰዓት ድረስ የተለያዩ መፈክሮችንና ተቃውሞዎችን በመንግሥት፣ በመንግሥት መገናኛ ብዙኅንና በአንዳንድ የግል መገናኛ ብዙኅን ላይ አሰምተዋል፡፡

ሠልፈኞቹ ለመንግሥት ካቀረቧቸው ጥያቄዎችና መፈክሮች መካከል፣ ‹‹ዜጐችን ማፈናቀል የዘር ማጥፋት ወንጀል ነው፡፡ የህሊናና የፖለቲካ እስረኞች በአስቸኳይ ይፈቱ፣ የመደራጀት መብታችን ይረጋገጥ፣ በኑሮ ውድነት የጐበጠው ትከሻችን እረፍት ያስፈልገዋል፣ ሕገ መንግሥትን የሚፃረሩ አፋኝ አዋጆች ይሰረዙ፣ የመንግሥት በሃይማኖት ጣልቃ መግባትን አጥብቀን እንቃወማለን፣ የሙስሊም መፍትሔ አፈላላጊዎች በአስቸኳይ ይፈቱ፣ ለፍትሕና ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት መስፈን የሚታገሉ ጋዜጠኞች ይፈቱና አትነሳም ወይ አትነሳም ወይ . . . ወኔ የሌለው የአገረ ሸክም ነው፣ ውሸት ሰለቸን . . . ›› የሚጠቀሱ ናቸው፡፡

“ይህ መንግሥት አይመጥነንም”


የ“ምርቃና” መግለጫ ለኢህአዴግ ድንጋጤ

shemelis2-
June 6, 2013 08:17 am By  Leave a Comment
ሰሞኑን ኢትዮጵያ የዓለም መገናኛ አጀንዳ ሆናለች። ለዘመናት እጇን ኢትዮጵያ ላይ ተክላ የኖረችው ግብጽ የምትዝተው ዛቻና፣ በቅርቡ ተቋቁሞ ታላቅ ታሪክ በማስመዝገቡ የተረጋገጠለት ሰማያዊ ፓርቲ ያዘጋጀው ሰላማዊ ሰልፍ አጀንዳዎቹ ናቸው።

በወጣት አመራሮች የተገነባውና በርካታ ሴት አባላት እንዳሉት የሚነገርለት ሰማያዊ ፓርቲ በጠራው ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ በዋናነት የተገኘው ድል የፍርሃት ደመና መገፈፉ ነው። አቶ መለስ ባስተላለፉት ትዕዛዝ በ1997 ዓ.ም ዜጎች አልመው በሚተኩሱ የአጋዚና ታማኝ የህወሃት አባሎች ደረትና አናታቸው እየተወጋ እንዲገደሉ ከተደረገ በኋላ የተቃውሞ ሰልፍ የማይታሰብ ሆኖ ላላፉት ስምንት ዓመታት ቆይቶ ነበር።

ከዳር እስከዳር ድምጽ አልባ ሆኖ የተሸነፈው ኢህአዴግ በጠመንጃ ፣ በወቅቱ የነበሩት የቅንጅት አመራሮች ታሪካዊና ሊረሳ የማይችል ስህተት ተዳምረው የህዝቡን ቅስም የሰበረው የ1997 ዓ ም ምርጫ ጣጣውና ቆፈኑ እንዲሁ በቀላሉ የሚለቅ እንዳልሆነ በወቅቱ አስተያየት ተሰጥቶ ነበር።
“ሁለት አስርት ዓመታት ወደኋላ ተመልሰናል” ተብሎ የተዘጋውን በር የበረገደው ሰማያዊ ፓርቲ ከህዝብ ባገኘው ድጋፍ አዲስ አበባን የተቃውሞ ጎርፍ አጎረፈባት። ሰላማዊ ሰልፉ ሰላማዊና የተሳካ እንደነበር ኢህአዴግ ራሱ ተናገረ። ህዝብ ተቃውሞውን ገልጾ የሶስት ወር ጊዜ ከሰጠ በኋላ ወደ ቤቱ ተመለሰ።

አዲስ አበባ አንድ ለአምስት፣ የጎንዮሽ፣ የሽቅብ፣ የህቡዕ፣ የገሃድ፣ የዘር፤ የታማኞች፣ የበጣም ታማኞች፣ የልማት፣ የአነስተኛ ስራ ፈጠራ፣ የጾታ፣ የዘር፣ የእድሜ፣ የተፈጥሮ ሁኔታ፣ የጥቅም ወዘተ የፈጠረው አደረጃጀት አፈር ድሜ መብላቱ ያስጨነቀው ኢህአዴግ ሰልፉ ተበትኖ ሲያበቃ ላንቃውን አላቀቀ።

Monday, June 3, 2013

በህዝብ አቆጣጠር አሁን ጨዋታው ተጀመረ!


ወደ "ሻርኮቹ" ይቀጥል!! (ርዕሰአንቀጽ)

shark
June 3, 2013 08:34 am By  Leave a Comment
ሙስናው ላይ የተጀመረው ዘመቻ ሙስናን በስንጥር የሚያሰኝ ቢሆንም አቶ መለስ ያልደፈሩትን ሰፈር አቶ ሃይለማርያም ነክተውታልና በኢህአዴግ ታሪክ የሙስናን ሰፈር በማንኳኳት ግንባር ቀደሙ ሰው ያደርጋቸዋል። እኛም ጅምሩ መልካም ነው እንላለን። ግን ጥያቄም ማሳሰቢያም አለን። ለማንኛውም በህዝብ አቆጣጠር አሁን ጨዋታው የተጀመረ ይመስለናል።

በሙስና የተጠረጠሩ ነጋዴዎች፣ ደላሎች፣ አቀባባይ የተባሉና የመንግስት ሃላፊዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸው ከተሰማ ጀምሮ ህዝብ በስፋት እየተቸ ነው። ኢትዮጵያ ውስጥ የተደላደለውን ሙስና ህዝብ ጠንቅቆ ከነባለቤቶቹ ያውቃል። ይረዳል። ያሸታል። ባለፈ ባገደመ ቁጥር ለድህነቱ ማስታገሻ ያላምጣቸዋል።

ሙስና ሲባል ሙስና ነው። ወንጀል ሲባል ወንጀል ነው። ህግ መተላለፍ ያስጠይቃል። አሁን እንደሚታየው ግን የጸረ ሙስናው ዘመቻ ሰፈር የለየ ይመስላል። ዋናዎቹ “ሻርኮች” አልተነኩም። ዋናዎቹ “የማበስበሻው ባህር” ፊታውራሪዎች አሁንም እያገሱ ነው። እነዚህ አገር ወዳድ የሚመስሉ  የሙስና መፈልፈያ ማሽን አምራቾች ለምን ዝም ተባሉ? የህዝብ ጥያቄ ነው? የምስኪን ዜጎች ጥያቄ ነው። በተለይም “ጠቁሙኝ እርምጃ እወስዳለሁ” በማለት ለተናገሩት አዲሱ መሪ፡፡

ምርመራው ወደ አቃብያነህጉ ተዛወረ!


የሙስናው “ሻርኮች” በዒላማ ውስጥ?

berhane
June 3, 2013 08:40 am By  Leave a Comment
* “አዲስ ነገር የለም” ጸረ ሙስና ኮሚሽን
በተለያዩ ከፍተኛ ወንጀሎች በተጠረጠሩ ሰዎች ላይ የተከፈቱ ክሶችን በማፈንና በመመሪያ ፍትህ በማዛባትና በማቋረጥ ወንጀል የተጠረጠሩ አቃቤያነህግ ላይ ምርመራ መጀመሩ ከፍተኛ ድንጋጤ መፍጠሩ ተሰማ። በተለይም ከወንጀል ጋር ቁርኝት እንዳላቸው በህዝብ የሚታወቁ ክፍሎች ክፉኛ መደናገጣቸው ተሰምቷል።

በሙስና የተጠረጠሩት የጉምሩክ ባለስልጣናት፣ ተባባሪ ነጋዴዎችና ደላሎች መታሰራቸውን ተከትሎ ከተፈጠረው ስሜት በላይ ከፍተኛ መደናገጥ የፈጠረው ዜና አዲስ አድማስ ጋዜጣ ቅዳሜ እለት ለንባብ ያበቃው ዜና ነው።

በቅርቡ ከሃላፊነታቸው የተነሱት የፍትህ ሚኒስትር አቶ ብርሀነ ሃይሉና ከአስር በላይ አቃብያነህግ በተለያዩ ጉዳዮች የተመሰረቱ ክሶች እንዲቋረጡ አድርገዋል በሚል ተጠርጥረው መመርመራቸው በትክክል ከተሰራበት ዋንኛ የሚባሉትን የሙስና ወንጀል “ሻርኮች” በቁጥጥር ስር ለማዋል እንደሚያስችል ከፖሊስ ያገኘነው ጥቆማ ያመለክታል።

“የበርካታ ጉዳዮች ክስ እንዲቋረጥ መደረጉን እናውቃለን” በማለት ለጎልጉል ጥቆማ የሰጡት የፖሊስ አባላት “ይህ ጉዳይ ከተነሳና በትክክል ከተሰራበት የማይጎተት የለም” በማለት በትዕዛዝና በመመሪያ የተቋረጡ የምርመራና የክስ ፋይሎች በርካታ መሆናቸውን ያስረዳሉ።